የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ትምህርቶች የሚተላለፉበት Aba Gebrekidan sibket
6.46K subscribers
179 photos
7 videos
862 links
የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ትምህርቶች
Download Telegram
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ዱ አምላክ ዘለዓለም ሥላሴ።

በኢትዮጵያና በመላው ዓለም ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች፣ የጉባኤ ቤታችን ቤተሰቦች በሙሉ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን እንደምን ሰነበታችሁ? እኛ አምላከ አበው እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን።
የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት የምስክር ት/ቤት በእሳት እንደተቃጠለ በማኅበራዊ መገናኛ መረቦች እየተላለፈ እንደሆነ ብዙዎቻችሁ ተጨንቃችሁ ደውላችሁልናል።
በመሆኑም ከጉባኤ ቤቱ ሐሙስ ግንቦት ሰባት ቀን እሳት ከቤት ተነሥቶ ለደቀ መዛሙርቱ ተሠርቶ የነበረ ቆርቆሮ በቆርቆሮ ጊዚያዊ መጠለያና የግማሾቹ ደቀ መዛሙርት ልብስና መጻሕፍቶቻቸው ተቃጥለዋል። ነገር ግን በሰማዕቱ በቅዱስ ቂርቆስና በእመቤታችን ጸሎት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጠብቆን ጉባኤ ቤታችንና መጻሕፍቶቻችን ደኅና ናቸው።

እኛም ደቀመዛሙርቱና ዋናው ጉባኤ ቤት፣ እንዲሁም ገዳማችን ደኅና ስለሆነ፣ ጊዜው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የተጀመረበት በመሆኑ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ተጨማሪ ርእሰ ጉዳይ ላለመጨመር ለሚዲያ ሳንገልጽ ቆይተናል።በመሆኑም አሁን ግን ስለወጣ ይህንን መግለጫ ለተጨነቃችሁ ወገኖቻችን ልንገልጽ ፍቅር ያገብረናል።

ለጉባኤ ቤቱ የሚያስፈልጉን ጉዳዮች ቢኖሩ እኛ በፈወስ መንፈሳዉ የጉባኤ ቤታችን ሚዲያ በምስል የምንገልጽ መሆናችንን እየገለጽን ፣ ለተጨነቃችሁልን፣ለጸለያችሁልን፣ላሰባችሁልን፣ለረዳችሁን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ የጉባኤ አምላክ በምሕረቱ ያስብልን።

አምላከ ጉባኤ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያናችንንና ሀገራችንን ይጠብቅ።
40🙏16👍4😱2
የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ  የአባቶችና እናቶች አንድነት ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር ቤተ ጉባኤ
ግንቦት፳፫-፳፻፲፯ ዓም
31🙏7🥰1
“አቤቱ ድውይ ነኝና ፈውሰኝ” መዝ ፮፥፪
በሚል መሪ ቃል
ፈውስ መንፈሳዊ ዘጣና ቅዱስ ቂርቆስ
በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።

ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት

TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET

1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ

ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።
14👍1