ረቡዕ:- መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም
የመስከረም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ የሚሰጠውን የሙያ ስልጠና ምልከታ አደረጉ!!
በአራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘው መስከረም የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ 135 የሚሆኑ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የተለያዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ አሁን ላይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፉ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ በተጓዳኝነት የሚሰጥ በመሆኑ ስለሙያ ስልጠና አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው፡፡
ተማሪዎቹ እየተማሯቸው የሚገኙትን የሙያ ዘርፍ ስልጠና ወርክሾፖች የተመለከቱ ሲሆን እነሱም ኮንስትራክሽን፣ ጋርመንት /ልብስ ስፌት/፣ ከተማ ግብርና እና ሆቴል / ምግብ ዝግጅት/ የተግባር ስልጠና መስጫዎችን ተመልክተዋል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡
ሰሞኑን የአዲስ ከተማ እና የጀ/ ታደሰ ብሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተማሪዎች በተመሳሳይ በተቋሙ ትምህርታዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን የሙያ ስልጠና ሂደት የተለያዩ ት/ቤቶች ጉብኝት እንዲያደርጉ የሚያስተባብረው በኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ ስር የስራ ትስስርና ካውንስሊንግ የስራ ክፍል ነው፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የመስከረም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ የሚሰጠውን የሙያ ስልጠና ምልከታ አደረጉ!!
በአራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘው መስከረም የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ 135 የሚሆኑ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የተለያዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ አሁን ላይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፉ የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ በተጓዳኝነት የሚሰጥ በመሆኑ ስለሙያ ስልጠና አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው፡፡
ተማሪዎቹ እየተማሯቸው የሚገኙትን የሙያ ዘርፍ ስልጠና ወርክሾፖች የተመለከቱ ሲሆን እነሱም ኮንስትራክሽን፣ ጋርመንት /ልብስ ስፌት/፣ ከተማ ግብርና እና ሆቴል / ምግብ ዝግጅት/ የተግባር ስልጠና መስጫዎችን ተመልክተዋል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡
ሰሞኑን የአዲስ ከተማ እና የጀ/ ታደሰ ብሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተማሪዎች በተመሳሳይ በተቋሙ ትምህርታዊ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን የሙያ ስልጠና ሂደት የተለያዩ ት/ቤቶች ጉብኝት እንዲያደርጉ የሚያስተባብረው በኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን ቢሮ ስር የስራ ትስስርና ካውንስሊንግ የስራ ክፍል ነው፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
አርብ:- መጋቢት 19 ቀን 2017 ዓ.ም
በኮሌጁ አሰልጣኞች የተሰራ ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ቀረበ!!
ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በቡድን የሰሩ አሰልጣኞች የጥናት ውጤት ሰነዳቸውን በትናንትናው ዕለት ለውውድር አቀረቡ።
በዚህ ውድድር 5 የጥናትና ምርምር ሰነዶች ለባለሙያዎች ቀርበው ምዘና የተደረገባቸው ሲሆን በሁሉም ዘርፎች የተሰሩ የምርምር ተግባራት የኮሌጁን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ይረዳሉ ተብሏል።
የተግባራዊ ጥናትና ምርምሩ ዓላማ እንደ ተቋም የራስን ችግር በራስ አቅም ለመፍታት ያቀደ ሲሆን ሁሉም ጥናቶች የተነሱበትን ክፍተቶች ለመሙላት የሚችሉ ናቸው ተብሏል።
በውድድሩ ርዕሰ ጉዳዩ አንገብጋቢ ችግር መሆኑ፣ ከችግሩ ጋር የተሰናሰለ ዓላማ መቀረጹ፣ ችግሩን ለመፍታት የተደረገው ርቀት፣ በምርምር ሂደቱ የተገኙ ውጤቶች፣ ወዘተ የሚሉ መስፈርቶች ተካተዋል።
እንደ ተቋም 9 ተግባራዊ ጥናትና ምርምር እየተሰራ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለግምገማ የቀረቡት 5ቱ ናቸው።
አሸናፊው ሰነድ እንደ ከተማ በቴክኒክና ሙያ ሳምንት ከአቻ ተቋማት ስራ ጋር ውድድር የሚጠብቀው ሲሆን ባለፈው ዓመት በኮሌጁ የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በከተማ ደረጃ አንደኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
በኮሌጁ አሰልጣኞች የተሰራ ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ቀረበ!!
ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በቡድን የሰሩ አሰልጣኞች የጥናት ውጤት ሰነዳቸውን በትናንትናው ዕለት ለውውድር አቀረቡ።
በዚህ ውድድር 5 የጥናትና ምርምር ሰነዶች ለባለሙያዎች ቀርበው ምዘና የተደረገባቸው ሲሆን በሁሉም ዘርፎች የተሰሩ የምርምር ተግባራት የኮሌጁን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ይረዳሉ ተብሏል።
የተግባራዊ ጥናትና ምርምሩ ዓላማ እንደ ተቋም የራስን ችግር በራስ አቅም ለመፍታት ያቀደ ሲሆን ሁሉም ጥናቶች የተነሱበትን ክፍተቶች ለመሙላት የሚችሉ ናቸው ተብሏል።
በውድድሩ ርዕሰ ጉዳዩ አንገብጋቢ ችግር መሆኑ፣ ከችግሩ ጋር የተሰናሰለ ዓላማ መቀረጹ፣ ችግሩን ለመፍታት የተደረገው ርቀት፣ በምርምር ሂደቱ የተገኙ ውጤቶች፣ ወዘተ የሚሉ መስፈርቶች ተካተዋል።
እንደ ተቋም 9 ተግባራዊ ጥናትና ምርምር እየተሰራ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለግምገማ የቀረቡት 5ቱ ናቸው።
አሸናፊው ሰነድ እንደ ከተማ በቴክኒክና ሙያ ሳምንት ከአቻ ተቋማት ስራ ጋር ውድድር የሚጠብቀው ሲሆን ባለፈው ዓመት በኮሌጁ የተሰራው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በከተማ ደረጃ አንደኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ረቡዕ:- መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም
በክላስተር ደረጃ የክህሎት ውድድር ተካሄደ!!
በክላስተር ደረጃ የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ተካሄደ።
እንደ ሀገር ለ4ኛ እንደ ከተማ አስተዳደር ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ የሚካሄደው የዘንድሮው የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት የበቁ ዜጎች!" በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
እንደ ክላስተር በ14 ሙያዎች የክህሎት ውድድር የተደረገ ሲሆን ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ12 የመወዳደሪያ መስኮች ላይ 12 ሰልጣኞችን አሳፏል፡፡ አብዛኛዎቹ ውድድሮች በኮሌጁ የተደረጉ ሲሆን የተወሰኑት ደግሞ በዊንጌት ክላስተር ስር በሚገኙ ኮሌጆች ነው፡፡
የክህሎት ውድድር የተደረገባቸው ዲፓርንመንቶች ኮንስትራክሽን፣ ኤሌክትሪክሲቲና ኤሌክትሮኒክስ፣ ቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት፣ ሜታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ፣ ኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ሆቴልና ሆስፒታሊቲ እና ውድ ወርክ ቴክኖሎጂ ሲሆኑ በውድድሩ ተሳታፊ የሆኑት በኮሌጅ ደረጃ በነበረው ፋክክር በየዘርፉ ቀዳሚ የነበሩት ናቸው፡፡
በኮሌጅ ደረጃ ውድድር የተደረገው ከሁለት ሳምንት በፊት ሲሆን በዚህ ዓመት የአሰልጣኞች እና የአንቀሳቃሾች ክህሎት ውድድር እንደማይደረግ መግለፃችን ይታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
በክላስተር ደረጃ የክህሎት ውድድር ተካሄደ!!
በክላስተር ደረጃ የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ተካሄደ።
እንደ ሀገር ለ4ኛ እንደ ከተማ አስተዳደር ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ የሚካሄደው የዘንድሮው የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት የበቁ ዜጎች!" በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
እንደ ክላስተር በ14 ሙያዎች የክህሎት ውድድር የተደረገ ሲሆን ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ12 የመወዳደሪያ መስኮች ላይ 12 ሰልጣኞችን አሳፏል፡፡ አብዛኛዎቹ ውድድሮች በኮሌጁ የተደረጉ ሲሆን የተወሰኑት ደግሞ በዊንጌት ክላስተር ስር በሚገኙ ኮሌጆች ነው፡፡
የክህሎት ውድድር የተደረገባቸው ዲፓርንመንቶች ኮንስትራክሽን፣ ኤሌክትሪክሲቲና ኤሌክትሮኒክስ፣ ቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት፣ ሜታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ፣ ኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ሆቴልና ሆስፒታሊቲ እና ውድ ወርክ ቴክኖሎጂ ሲሆኑ በውድድሩ ተሳታፊ የሆኑት በኮሌጅ ደረጃ በነበረው ፋክክር በየዘርፉ ቀዳሚ የነበሩት ናቸው፡፡
በኮሌጅ ደረጃ ውድድር የተደረገው ከሁለት ሳምንት በፊት ሲሆን በዚህ ዓመት የአሰልጣኞች እና የአንቀሳቃሾች ክህሎት ውድድር እንደማይደረግ መግለፃችን ይታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"