ማክሰኞ:- ሚያዚያ 8 ቀን 2016 ዓ.ም
ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ተሞክሮ የማስፋት መድረክ ተካሄደ!!
በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን ቢሮ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ተሞክሮ የማስፋት መድረክ ተካሄደ፡፡
በቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን ቢሮ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዘርፍ በ4ቱ የድጋፍ አግባቦች ተጠቅመው ውጤታማ የሆኑ 2 ኢንተርፕራይዞች ላይ ተሞክሮ በመቀመር ሌሎች አንቀሳቃሾችም ልምዱን ተጋርተው ስኬታማ ይሆኑ ዘንድ ዛሬ ሚያዚያ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ከበርካታ ኢንተርፕራይዞች ለመጡ አንቀሳቃሾች ተሞክሮውን የማስፋት ስራ ተሰርቷል፡፡
ተሞክሮ የተቀመረባቸው 2ቱ ኢንተርፕራይዞች ዮዲት፣ ሳሙኤል እና ጓደኞቻቸው በቴራዞን ምርት የተሰማሩ እና ግዛቴ፣ ብርሃኔና ጓደኞቻቸው በብረታ ብረት ስራ ላይ የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ስር የሚገኙ 143 የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችና የክፍለ ከተማው ባለ ድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
በዚህ መድረክ ላይ የተገኙ አንቀሳቃሾችም በቀረበው ሰነድ እጅግ ተደስተው ቀጣይ እንደየ ስራ ዘርፋቸው ባህርይ በማጣጣም ይህንን ልምድ ለኢንተርፕራይዞቻቸው ለውጥ እንደሚጠቀሙበት ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የክህሎት ክፍተት አለብኝ ላሉ አንቀሳቃሾች በፍላጎታቸው መሰረት ከነገ ጀምሮ ልዩ ልዩ ስልጠና ለመስጠት እቅድ መያዙን ሰምተናል፡፡
ኮሌጁ በ3 ክፍለ ከተሞች ማለትም በአዲስ ከተማ፣ በጉለሌ እና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞች ከ500 በላይ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞች ልዩ ልዩ ድጋፎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ተሞክሮ የማስፋት መድረክ ተካሄደ!!
በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን ቢሮ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ተሞክሮ የማስፋት መድረክ ተካሄደ፡፡
በቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን ቢሮ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዘርፍ በ4ቱ የድጋፍ አግባቦች ተጠቅመው ውጤታማ የሆኑ 2 ኢንተርፕራይዞች ላይ ተሞክሮ በመቀመር ሌሎች አንቀሳቃሾችም ልምዱን ተጋርተው ስኬታማ ይሆኑ ዘንድ ዛሬ ሚያዚያ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ከበርካታ ኢንተርፕራይዞች ለመጡ አንቀሳቃሾች ተሞክሮውን የማስፋት ስራ ተሰርቷል፡፡
ተሞክሮ የተቀመረባቸው 2ቱ ኢንተርፕራይዞች ዮዲት፣ ሳሙኤል እና ጓደኞቻቸው በቴራዞን ምርት የተሰማሩ እና ግዛቴ፣ ብርሃኔና ጓደኞቻቸው በብረታ ብረት ስራ ላይ የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ስር የሚገኙ 143 የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችና የክፍለ ከተማው ባለ ድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
በዚህ መድረክ ላይ የተገኙ አንቀሳቃሾችም በቀረበው ሰነድ እጅግ ተደስተው ቀጣይ እንደየ ስራ ዘርፋቸው ባህርይ በማጣጣም ይህንን ልምድ ለኢንተርፕራይዞቻቸው ለውጥ እንደሚጠቀሙበት ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የክህሎት ክፍተት አለብኝ ላሉ አንቀሳቃሾች በፍላጎታቸው መሰረት ከነገ ጀምሮ ልዩ ልዩ ስልጠና ለመስጠት እቅድ መያዙን ሰምተናል፡፡
ኮሌጁ በ3 ክፍለ ከተሞች ማለትም በአዲስ ከተማ፣ በጉለሌ እና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞች ከ500 በላይ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞች ልዩ ልዩ ድጋፎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍6
ረቡዕ:- ሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም
ከተለያዩ የስራ ክፍል ለተውጣጡ ባለሙያዎች በግዢ ስርዓት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ከተለያዩ የስራ ክፍላት ለተውጣጡ ባለሙያዎች በግዢ ስርዓት ዙሪያ 5 ቀናት ቆይታ የተያዘለት ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህ ስልጠና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች፣ የወርክ ሾፕ ባለሙያዎች፣ የጨረታ እና የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት፣ የንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት፣ የዕቅድና በጀት፣ የፋይናንስ፣ የውስጥ ኦዲት ባለሙያዎች እንዲሁም ከግዢ ሂደት ጋር ተያያዥነት ስራ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡
ስልጠናው የተሰጠው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የግዢ ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች ሲሆን ስለ ግዢ ምንነት፣ የግዢ ስርዓት፣ የግዢ ሂደትና ዓይነት እንዲሁም በግዢ ዕቅድ ትግበራ ላይ የባለ ድርሻ አካላት ሚና ወዘተ በሚሉት ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የዚህ ስልጠና መሰረታዊ ዓላማ ቀጣይ በሚደረገው የግዢ ሂደት ከግዢ ፍላጎት አንስቶ ግዢው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ባለው የጊዜ ዑደት ጥራት ያለው የስልጠና ግብዓት በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳና በሚፈለገው መጠን እንዲፈፀም ባለድርሻ አካላቱ የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ ታስቦ መዘጋጀቱን የገለፁልን በኮሌጁ የግዢ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ኤርሚያስ ግርማ ናቸው፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም አሁን ላይ ከስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ጀምሮ በርካቶቹ አዲስ በመሆናቸው ይህ ስልጠና ለእነዚህ አካላት መሰጠቱ ቀጣይ የግዢ ስርዓቱ በታቀደለት የጊዜ ቀመር እንዲከወንና ከፍላጎት ጋር የተጣጣመ እንዲሆነ ምቹ ሂደት ይፈጥራል፡፡ ብለዋል፡፡
በኮሌጁ ከተመደበው አጠቃላይ በጀት ሶስት አራተኛው ወይም ወደ 75 ፐርሰንት የሚጠጋው ለልዩ ልዩ አገልግሎት በግዢ ስርዓት ወጪ የሚደረግ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ከተለያዩ የስራ ክፍል ለተውጣጡ ባለሙያዎች በግዢ ስርዓት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ከተለያዩ የስራ ክፍላት ለተውጣጡ ባለሙያዎች በግዢ ስርዓት ዙሪያ 5 ቀናት ቆይታ የተያዘለት ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህ ስልጠና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች፣ የወርክ ሾፕ ባለሙያዎች፣ የጨረታ እና የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት፣ የንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት፣ የዕቅድና በጀት፣ የፋይናንስ፣ የውስጥ ኦዲት ባለሙያዎች እንዲሁም ከግዢ ሂደት ጋር ተያያዥነት ስራ ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡
ስልጠናው የተሰጠው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የግዢ ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች ሲሆን ስለ ግዢ ምንነት፣ የግዢ ስርዓት፣ የግዢ ሂደትና ዓይነት እንዲሁም በግዢ ዕቅድ ትግበራ ላይ የባለ ድርሻ አካላት ሚና ወዘተ በሚሉት ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የዚህ ስልጠና መሰረታዊ ዓላማ ቀጣይ በሚደረገው የግዢ ሂደት ከግዢ ፍላጎት አንስቶ ግዢው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ባለው የጊዜ ዑደት ጥራት ያለው የስልጠና ግብዓት በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳና በሚፈለገው መጠን እንዲፈፀም ባለድርሻ አካላቱ የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ ታስቦ መዘጋጀቱን የገለፁልን በኮሌጁ የግዢ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ኤርሚያስ ግርማ ናቸው፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም አሁን ላይ ከስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ጀምሮ በርካቶቹ አዲስ በመሆናቸው ይህ ስልጠና ለእነዚህ አካላት መሰጠቱ ቀጣይ የግዢ ስርዓቱ በታቀደለት የጊዜ ቀመር እንዲከወንና ከፍላጎት ጋር የተጣጣመ እንዲሆነ ምቹ ሂደት ይፈጥራል፡፡ ብለዋል፡፡
በኮሌጁ ከተመደበው አጠቃላይ በጀት ሶስት አራተኛው ወይም ወደ 75 ፐርሰንት የሚጠጋው ለልዩ ልዩ አገልግሎት በግዢ ስርዓት ወጪ የሚደረግ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍4
ሐሙስ:- ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም
ለሴት ሰለጣኞች የተለያዩ የስልጠና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ!!
በኮሌጁ ለሚሰለጥኑ እና ከ4 ዲፓርትመንቶች ማለትም ከኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒከስ፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከሜታል ማኑፋክቸሪንግ እና ከአውቶሞቲቭ ዲፓርትመንቶች ለተውጣጡ 36 መደበኛ ሴት ሰለጣኞች በኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት ጽ/ቤት አማካኝነት ዛሬ ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የተለያዩ የስልጠና መገልገያ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገላቸው::
በዕለቱ የተሰጠው ድጋፍ የEASTRIP ፕሮጀክት የስርዓተ ፆታን ጉዳይ ለማስረፅ የሚያደርገው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ አካል እንዲሁም ሴት ሰልጣኞች ሃርድ ስኪል በሚባሉ ሙያዎች ያላቸውን ተሳትፎ ለማበረታታት የተደረገ የድጋፍ ስራ መሆኑ ተነግሯል፡፡
በድጋፍ መርሃ ግብር ላይ የEASTRIP ፕሮጀክት ሰራተኞች እና የኮሌጁ ምክትል ዲኖች ተገኝተው ስጦታውን አበርክተዋል፡፡ ሁሉም የመርሃ ግብሩ ታዳሚዎች ለሰልጣኞቹ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ቀጣይም ኮሌጁ እናንተን በማንኛውም መንገድ ለማበረታትት ዝግጁ ነው እናንተም ራሳችሁን እንደ ሌሎች ተምሳሌት የሆኑ ሴት ባለሙያዎች ራሳችሁን አብቁ ለኮሌጃችንም የወደ ፊት ሰልጣኞች አምባሳደር እንዲትሆኑ እናሳስባለን ያሉት የኮሌጁ የተቋማት ልማት እና አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ሰባሁዲን ናቸው፡፡ በሌላ በኩል በኮሌጁ የEASTRIP ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ጀማል ሀሰን በበኩላቸው ሃርድ ስኪል ስልጠና ለሴት ሰልጣኝ ከባድ ሙያ ነው የሚባለውን ዘርፍ በይቻላል መንፈስ መርጣችሁ ቀጣይ ራሳችሁ የስራ ባለቤት ለመሆን እና ሀገራችሁን በዘርፉ ለማገልገል በማቀዳችሁ በርቱ ለማለት ያዘጋጀነው ነው ብለዋል፡፡
በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተሰጡ የድጋፍ ዓይነቶች ለስልጠና አገልግሎት የሚውሉ ሲሆን እነሱም ቱታ፣ ገዋን፣ የጥንቃቄ ጫማ፣ የስራ መነጽር፣ ግላፍ፣ ሄልሜት እና የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ይገኙበታል፡፡
ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ከዚህ በፊትም ለሴት ሰልጣኞች ማበረታቻ እንዲሆን ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን እና የገንዘብ ድጋፎችን እንዳደረገ አይዘነጋም፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ለሴት ሰለጣኞች የተለያዩ የስልጠና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ!!
በኮሌጁ ለሚሰለጥኑ እና ከ4 ዲፓርትመንቶች ማለትም ከኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒከስ፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከሜታል ማኑፋክቸሪንግ እና ከአውቶሞቲቭ ዲፓርትመንቶች ለተውጣጡ 36 መደበኛ ሴት ሰለጣኞች በኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት ጽ/ቤት አማካኝነት ዛሬ ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የተለያዩ የስልጠና መገልገያ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደረገላቸው::
በዕለቱ የተሰጠው ድጋፍ የEASTRIP ፕሮጀክት የስርዓተ ፆታን ጉዳይ ለማስረፅ የሚያደርገው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ አካል እንዲሁም ሴት ሰልጣኞች ሃርድ ስኪል በሚባሉ ሙያዎች ያላቸውን ተሳትፎ ለማበረታታት የተደረገ የድጋፍ ስራ መሆኑ ተነግሯል፡፡
በድጋፍ መርሃ ግብር ላይ የEASTRIP ፕሮጀክት ሰራተኞች እና የኮሌጁ ምክትል ዲኖች ተገኝተው ስጦታውን አበርክተዋል፡፡ ሁሉም የመርሃ ግብሩ ታዳሚዎች ለሰልጣኞቹ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ቀጣይም ኮሌጁ እናንተን በማንኛውም መንገድ ለማበረታትት ዝግጁ ነው እናንተም ራሳችሁን እንደ ሌሎች ተምሳሌት የሆኑ ሴት ባለሙያዎች ራሳችሁን አብቁ ለኮሌጃችንም የወደ ፊት ሰልጣኞች አምባሳደር እንዲትሆኑ እናሳስባለን ያሉት የኮሌጁ የተቋማት ልማት እና አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ሰባሁዲን ናቸው፡፡ በሌላ በኩል በኮሌጁ የEASTRIP ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ጀማል ሀሰን በበኩላቸው ሃርድ ስኪል ስልጠና ለሴት ሰልጣኝ ከባድ ሙያ ነው የሚባለውን ዘርፍ በይቻላል መንፈስ መርጣችሁ ቀጣይ ራሳችሁ የስራ ባለቤት ለመሆን እና ሀገራችሁን በዘርፉ ለማገልገል በማቀዳችሁ በርቱ ለማለት ያዘጋጀነው ነው ብለዋል፡፡
በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተሰጡ የድጋፍ ዓይነቶች ለስልጠና አገልግሎት የሚውሉ ሲሆን እነሱም ቱታ፣ ገዋን፣ የጥንቃቄ ጫማ፣ የስራ መነጽር፣ ግላፍ፣ ሄልሜት እና የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ይገኙበታል፡፡
ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ከዚህ በፊትም ለሴት ሰልጣኞች ማበረታቻ እንዲሆን ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን እና የገንዘብ ድጋፎችን እንዳደረገ አይዘነጋም፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍8❤1
ሐሙስ:- ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም
በኮሌጁ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ ሊሰራ ነው!!
በኮሌጁ ዋና በር መግቢያ ላይ የሚገኘው ትንሹ የእግር ኳስ ሜዳ ጊዜውን የመጠነና ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የእግር ኳስ ማዘውተሪያ ሊገነባ ነው::
ግንባታው ፉት ፒች ሃላ/የተ/የግ ድርጅት በተሰኘ ኩባንያ የሚፈጸም ሲሆን የስራው አጠቃላይ ወጪ 20 ሚሊዮን ብር ታቅዶለታል። ማህበረሰባዊ የግል አጋሮች ተሳትፎ /Public Private Partnership participation/ በሚለው መርህ መሰረት ኮሌጁ ከግል አልሚዎች ጋር በመተባበር ይህንን መሰረተ ልማት ለመገንባት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ስራው 4 ዘመናዊ የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳ እንዲሆን ታስቦ ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን ሙሉ ፋሲሊቲዎች የተሟሉለት ማዘውተሪያ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ይደረጋል መባሉን ሰምተናል።
ሜዳው አርቲፊሻል ሳር ማልበስን ጨምሮ ልዩ ልዩ ግብዓትን በማሟላት የተቋሙን አጠቃላይ ገጽታ የሚቀይር ስራ እንደሚሰራ ከስምምነት ሰንዱ ማረጋግጥ ችለናል።
ስራው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በማህበረስብ አገልገሎት ዘርፍ የአካባቢው ወጣቶች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጊዜያቸውን እንዲያሳልፉ፣ የኮሌጁ ተቋማዊ ገጽታ ማራኪ እንዲሆን፣ የኮሌጁ የውስጥ ገቢ እንዲያድግ፣ ለተለያዩ የጤና ስፖርት ቡድኖችና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ስፖርታዊ እንቀስቃሴ እንዲያደርጉ ወዘተ ያገለግላል ያሉን በኮሌጁ የተቋማት ልማትና አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ሰባሁዲን ሁሴን ናቸው።
የመጀመሪያው ሜዳ በ2 ወራት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን ወደ ስራ ለመግባት ዛሬ ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመግባቢያ ስምምነቱ ተፈርሟል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
በኮሌጁ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ ሊሰራ ነው!!
በኮሌጁ ዋና በር መግቢያ ላይ የሚገኘው ትንሹ የእግር ኳስ ሜዳ ጊዜውን የመጠነና ደረጃውን የጠበቀ ዘመናዊ የእግር ኳስ ማዘውተሪያ ሊገነባ ነው::
ግንባታው ፉት ፒች ሃላ/የተ/የግ ድርጅት በተሰኘ ኩባንያ የሚፈጸም ሲሆን የስራው አጠቃላይ ወጪ 20 ሚሊዮን ብር ታቅዶለታል። ማህበረሰባዊ የግል አጋሮች ተሳትፎ /Public Private Partnership participation/ በሚለው መርህ መሰረት ኮሌጁ ከግል አልሚዎች ጋር በመተባበር ይህንን መሰረተ ልማት ለመገንባት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ስራው 4 ዘመናዊ የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳ እንዲሆን ታስቦ ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን ሙሉ ፋሲሊቲዎች የተሟሉለት ማዘውተሪያ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ይደረጋል መባሉን ሰምተናል።
ሜዳው አርቲፊሻል ሳር ማልበስን ጨምሮ ልዩ ልዩ ግብዓትን በማሟላት የተቋሙን አጠቃላይ ገጽታ የሚቀይር ስራ እንደሚሰራ ከስምምነት ሰንዱ ማረጋግጥ ችለናል።
ስራው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በማህበረስብ አገልገሎት ዘርፍ የአካባቢው ወጣቶች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጊዜያቸውን እንዲያሳልፉ፣ የኮሌጁ ተቋማዊ ገጽታ ማራኪ እንዲሆን፣ የኮሌጁ የውስጥ ገቢ እንዲያድግ፣ ለተለያዩ የጤና ስፖርት ቡድኖችና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ስፖርታዊ እንቀስቃሴ እንዲያደርጉ ወዘተ ያገለግላል ያሉን በኮሌጁ የተቋማት ልማትና አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ሰባሁዲን ሁሴን ናቸው።
የመጀመሪያው ሜዳ በ2 ወራት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን ወደ ስራ ለመግባት ዛሬ ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የመግባቢያ ስምምነቱ ተፈርሟል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍8👏4