አርብ:- መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ላይ ትኩረት ያደረገ የ2 ቀን ስልጠና ተሰጠ፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት በስነምግባር ምንነትና አስፈላጊነት፣ በሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ ምንነትና ጥቅም እንዲሁም የብልሹ አሰራር ዓይነቶች፣ የመከላከያ መንገዶች እና ስነ ምግባር ከሰልጣኞች የስልጠና አሰጣጥ አንጻር ያለውን ትርጉም ወዘተ በተመለከተ መጋቢት 18 እና 19 ቀን 2016 ዓ.ም የ2 ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ለኮሌጁ ሰልጣኞች በተቋማዊ ስነ ምግባር ዙሪያ ላይ ትኩረት ያደረገ የ2 ቀን ስልጠና ተሰጠ፡፡
የኮሌጁ የስነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት በስነምግባር ምንነትና አስፈላጊነት፣ በሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ ምንነትና ጥቅም እንዲሁም የብልሹ አሰራር ዓይነቶች፣ የመከላከያ መንገዶች እና ስነ ምግባር ከሰልጣኞች የስልጠና አሰጣጥ አንጻር ያለውን ትርጉም ወዘተ በተመለከተ መጋቢት 18 እና 19 ቀን 2016 ዓ.ም የ2 ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍11❤5👎1
ቅዳሜ፦ መጋቢት 28 ቀን 2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለኮሌጁ አሰልጣኞች እና አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ
ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በወቅታዊ የፐብሊክ ሰርቪስ ስራ አተገባበር ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ስላለ በእለቱ ከጧቱ 2:30 ላይ አስተዳደር ህንጻ 4ኛ ፎቅ በሚገኘው አዲሱ አዳራሽ እንዲትገኙ እያሳሰብን ነገር ግን መደበኛው የስልጠና ሂደት መኖሩን እናሳውቃለን።
የኮሌጁ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
ማስታወቂያ
ለኮሌጁ አሰልጣኞች እና አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ
ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም በወቅታዊ የፐብሊክ ሰርቪስ ስራ አተገባበር ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ስላለ በእለቱ ከጧቱ 2:30 ላይ አስተዳደር ህንጻ 4ኛ ፎቅ በሚገኘው አዲሱ አዳራሽ እንዲትገኙ እያሳሰብን ነገር ግን መደበኛው የስልጠና ሂደት መኖሩን እናሳውቃለን።
የኮሌጁ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
👍8
ሰኞ:- መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም
አሻራ እንነካለን፣ አሻራችንንም እናስቀምጣለን!!
የኮሌጁ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በሰራተኞች ዲጂታል የሰዓት መቆጣጠሪያ አጠቃቀም እና አጠቃላይ የፐብሊክ ሰርቫንቱ መብት እና ግዴታዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ተደረገ፡፡
እንደ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ሰርቫንቱ መብት እና ግደታ የተደነገገባቸውን አዋጆች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች በማጣቀስ ለተሳታፊዎች በገለፃ ያቀረቡት የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ መቅደስ አባይ ናቸው፡፡
በገለፃው ላይ የዲጂታል የሰዓት መቆጣጠሪያ ስርዓት /የጣት አሻራ/ አጠቃቀም ዙሪያ በስፋት ተነስቷል፡፡ እንደ ኮሌጅ ከማኑዋል ወደ ወረቀት አልባ ዲጂታል ስርዓት መሻጋገራችን ግድ ይለናል ምክኒያቱም የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች መፈልፈያ ቋት ሆነን ለሌሎች ስናሸጋገር የእኛ የቴክሎጂ አጠቃቀማችን መዘግየት የለበትም ያሉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡ ዋና ዲኑ አክለውም ኮሌጃችንን በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ለማድረግ የያዝነው ራዕይ እውን የሚሆነው የጊዜ አጠቃቀማችን ውጤታማ ሲሆን ነው ነገር ግን የተዘረጋው ስርዓት ከተቋሙ የስራ ባህርይ እና ከሰራተኛው የስራ ጠባይ ጋር ቅን ተዛምዶ እንዲኖረው ይደረጋል ብለዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የተቋሙን የውስጥ ገቢ በማሳደግ ኮሌጁ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመንና ሰራተኛውን ለመደጎም ሁሉም ዲፓርትመንቶች ባቀረቡት የምርትና የአገልግሎት ፕሮፖዛል መሰረት በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ አቅጣጫ የተሰጠ ሲሆን የተወሰኑ ዘርፎች ወደ ገበያው መቀላቀላቸው ተገልጿል፡፡
በመጨረሻም የስራ ሰዓታችንን ለመከታተል የጣት አሻራ እንነካለን፣ ኮሌጃችንን የሚመጥን ስራ በመስራት ለቀጣይ ትውልድ አሻራችንን እናስቀምጣለን በሚለው ገዢ ሀሳብ ማጠቃለያ ተስጥቶ ተጠናቋል፡፡
ለኮሌጁ አሰልጣኞች ብቻ የሰዓት መከታተያያ ስርዓቱ ወደ ዲጂታል ከተቀየረ አንድ ዓመት ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
አሻራ እንነካለን፣ አሻራችንንም እናስቀምጣለን!!
የኮሌጁ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በሰራተኞች ዲጂታል የሰዓት መቆጣጠሪያ አጠቃቀም እና አጠቃላይ የፐብሊክ ሰርቫንቱ መብት እና ግዴታዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ተደረገ፡፡
እንደ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ሰርቫንቱ መብት እና ግደታ የተደነገገባቸውን አዋጆች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች በማጣቀስ ለተሳታፊዎች በገለፃ ያቀረቡት የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ መቅደስ አባይ ናቸው፡፡
በገለፃው ላይ የዲጂታል የሰዓት መቆጣጠሪያ ስርዓት /የጣት አሻራ/ አጠቃቀም ዙሪያ በስፋት ተነስቷል፡፡ እንደ ኮሌጅ ከማኑዋል ወደ ወረቀት አልባ ዲጂታል ስርዓት መሻጋገራችን ግድ ይለናል ምክኒያቱም የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች መፈልፈያ ቋት ሆነን ለሌሎች ስናሸጋገር የእኛ የቴክሎጂ አጠቃቀማችን መዘግየት የለበትም ያሉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ መለሰ ይግዛው ናቸው፡፡ ዋና ዲኑ አክለውም ኮሌጃችንን በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ለማድረግ የያዝነው ራዕይ እውን የሚሆነው የጊዜ አጠቃቀማችን ውጤታማ ሲሆን ነው ነገር ግን የተዘረጋው ስርዓት ከተቋሙ የስራ ባህርይ እና ከሰራተኛው የስራ ጠባይ ጋር ቅን ተዛምዶ እንዲኖረው ይደረጋል ብለዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የተቋሙን የውስጥ ገቢ በማሳደግ ኮሌጁ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመንና ሰራተኛውን ለመደጎም ሁሉም ዲፓርትመንቶች ባቀረቡት የምርትና የአገልግሎት ፕሮፖዛል መሰረት በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ አቅጣጫ የተሰጠ ሲሆን የተወሰኑ ዘርፎች ወደ ገበያው መቀላቀላቸው ተገልጿል፡፡
በመጨረሻም የስራ ሰዓታችንን ለመከታተል የጣት አሻራ እንነካለን፣ ኮሌጃችንን የሚመጥን ስራ በመስራት ለቀጣይ ትውልድ አሻራችንን እናስቀምጣለን በሚለው ገዢ ሀሳብ ማጠቃለያ ተስጥቶ ተጠናቋል፡፡
ለኮሌጁ አሰልጣኞች ብቻ የሰዓት መከታተያያ ስርዓቱ ወደ ዲጂታል ከተቀየረ አንድ ዓመት ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍11❤1👎1