አርብ:- ታህሳስ 26 ቀን 2015 ዓ.ም
ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ተካሄደ!!
መጪውን የገና /የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት/ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡
ኮሌጁ ከ400 ሺ ብር በላይ ወጪ አድርጎ ከ6ሺ ብር በታች ደመወዝ ለሚከፈላቸው 200 ሰራተኞች የዓይነት ስጦታ በማበርከት ለበዓሉ እንኳን አደረሳችሁ ብሏል፡፡
የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ በኑሮ ውድነቱ ምክንያት ጫና ላይ ላሉ የስራ ባልደረቦች የመተሳሰብ እና የመረዳዳት ባህል ለማጠናከር እና የአንዱን ችግር ሌላዉ እንዲጋራ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ኮሌጁ ከዚህም በፊት በነበሩ በዓላት አነስተኛ ደመወዝ ተከፋይ ለሆኑ ሰራተኞች የበዓል መዋያ ድጎማ ሲያደርግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ተካሄደ!!
መጪውን የገና /የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት/ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡
ኮሌጁ ከ400 ሺ ብር በላይ ወጪ አድርጎ ከ6ሺ ብር በታች ደመወዝ ለሚከፈላቸው 200 ሰራተኞች የዓይነት ስጦታ በማበርከት ለበዓሉ እንኳን አደረሳችሁ ብሏል፡፡
የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ በኑሮ ውድነቱ ምክንያት ጫና ላይ ላሉ የስራ ባልደረቦች የመተሳሰብ እና የመረዳዳት ባህል ለማጠናከር እና የአንዱን ችግር ሌላዉ እንዲጋራ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ኮሌጁ ከዚህም በፊት በነበሩ በዓላት አነስተኛ ደመወዝ ተከፋይ ለሆኑ ሰራተኞች የበዓል መዋያ ድጎማ ሲያደርግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
❤20👍9👏5👎1
አርብ:- ታህሳስ 26 ቀን 2015 ዓ.ም
የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዘርፍ የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ!!
የሁሉም ኮሌጆች የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዘርፍ የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዛሬ ታህሳስ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
የግምገማ መድረኩ ዝግጅት እና አስተባባሪ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ሲሆን በዕለቱ በሁሉም ኮሌጆች ያሉ የዘርፉ ምክትል ዲኖች እና የቢሮው የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በግምገማ መድረኩ ላይ የሁሉም ኮሌጆች የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲኖች እንደ ዘርፍ የተቋሞቻቸውን የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም አቅርበው ሀሳብ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም የዘርፉን ስራ አፈፃፀም በስራ ክፍሉ ም/ዲን በአቶ ደሜ መርሻ አማካኝነት ቀርቧል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዘርፍ የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ!!
የሁሉም ኮሌጆች የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዘርፍ የ6 ወር አፈፃፀም ግምገማ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዛሬ ታህሳስ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
የግምገማ መድረኩ ዝግጅት እና አስተባባሪ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ሲሆን በዕለቱ በሁሉም ኮሌጆች ያሉ የዘርፉ ምክትል ዲኖች እና የቢሮው የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በግምገማ መድረኩ ላይ የሁሉም ኮሌጆች የቴክኖሎጂ ልማት እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲኖች እንደ ዘርፍ የተቋሞቻቸውን የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም አቅርበው ሀሳብ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም የዘርፉን ስራ አፈፃፀም በስራ ክፍሉ ም/ዲን በአቶ ደሜ መርሻ አማካኝነት ቀርቧል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍9❤5
Forwarded from General Wingate Students Channel (✨E l i a z 🌙 ኤ ል ያ ዝ | Элиаз)
በጀነራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ የገና በዓልን በማስመልከት ለ2ተኛ ዙር የደም ልገሳ ፕርግራም ተካሄደ። ከኢትዮጵያ ደም ባንክ እና ከጀኔራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የሰልጣኝ ካውንስል ጋር በጋራ በመተባበር የተዘጋጀው የደም ልገሳ ፕሮግራም በኮሌጃችን ግቢ ውስጥ ያሉት የአስተዳደር ሰራተኞች ፣ ሰልጣኞች እንዲሁም በግቢ ውስጥ ያሉ ማህበረሰዎች ተሳትፈውበታል ። ይህ ፕሮግራም ቀጣይነት ያለው ስለሆነ ከዚህ በኋላ ላሉት ፕሮግራሞችም ድጋፋችሁ አይለየን በአሁኑ የደም ልገሳ የተሳተፋችሁ በሙሉ እናመሰግናለን። መልካም በዓል።
የሰልጣኝ ካውንስል
የሰልጣኝ ካውንስል
❤14👍6
ሐሙስ:- ጥር 2 ቀን 2016 ዓ.ም
የድርጅትንም ሆነ የሀገርን ሀብት ከሚያሳጡ አንዱና ዋናው ሙስና ነው፡፡ ከሙስና ጋር ተያይዞ የሚነሳው ደግሞ አንዱ የጥቅም ግጭት ነው፡፡
በዛሪው ሀተታችን ስለ ጥቅም ግጭት የተውሰነ እናውሳ፡፡ የጥቅም ግጭት ምንድነው?
የጥቅም ግጭት የመወሰን ስልጣን/ሃላፊነት/ ያለው ሰው የግል ጥቅም ከመንግስታዊ ስራ ወይም ኃላፊነት ጋር በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ የሚጋጭ ወይም ግጭት ሊፈጥር የሚችል ሁኔታ ነው፡፡
የጥቅም ግጭት በአንድ ተቋም ውስጥ ያለ ኃላፊነት በግል ህይዎት፣ ማህበራዊ ትስስር እና ጥቅም ላይ ባለ ፍላጎት ተፅዕኖ ዉስጥ የሚወድቅበት ሁኔታ ነው፡፡
ለጥቅም ግጭት መከሰት መንስኤው አንድ ግለሰብ ሁኔታውን እያወቀ ወይም እየተገነዘበ የመወሰን ስልጣኑን ለግል ወይም ለድርጅት ጥቅም ለመጠቀም እድል ሲኖረው ነው። ሙስና የሚፈጠረው ግለሰቡ ያገኘውን ዕድል ተጠቅሞ ቦታውን ለግል ጥቅም ሲጠቀምበት ነው።
የጥቅም ግጭት ሙስና እንዲከሰት መልካም አጋጣሚዎችን ወይም ለሙስና መከሰት ምቹ መንገድን የሚፈጥር ሲሆን፣ የጥቅም ግጭት በራሱ ሙስና አለመሆኑ ነዉ፡፡ ባጭሩ የጥቅም ግጭት ለሙስና መከሰት መንገድ ጠራጊ ነዉ፡፡
የጥቅም ግጭት አይነቶች
1. ተጨባጭ የጥቅም ግጭት /actual or real conflict of interest/፡- ተጨባጭ የጥቅም ግጭት የሚፈጠረዉ የመንግስት ባለስልጣን ኃላፊነቱን እየተወጣ ሳለ ያለ ተፅዕኖ ወይም ያለአድሎ የመወሰን ኃላፊነቱን የሚፈታተን ሁኔታ ወይም ክሰተት በተጨባጭ/በትክክል ሲያጋጥመዉ
2. . ተጋላጭ/እምቅ/ የጥቅም ግጭት/potential conflict of interest/፡- ተጋላጭ የጥቅም ግጭት በተጨባጭ ያላጋጠመ ነገር ግን ወደፊት ሊያጋጥም የሚችል እድል ያለዉ ሁኔታ ወይም ክስተት ነዉ፡፡
3. ተገማች/ተጠርጣሪ የጥቅም ግጭት /perceived conflict of interest/፡- ግንዛቤያዊ የጥቅም ግጭት የዉሳኔ አሰጣጦችን ከተጽዕኖ ነጻ መሆን የሚጋፉ ሁኔታዎች መኖራቸዉን ሃላፊነት የወለዳቸዉ ጥቅሞች ይኖራሉ የሚያስብል ጥርጣሬዎችን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች ናቸዉ፡፡
የጥቅም ግጭት ለመከላከል የተደነገገ/የወጣ አዋጅ /ፖሊሲ/ ደንብ
1987 የኢፌዴሪ ህገ መንግስት፣ አዋጅ ቁጥር 544/2007 የተባበሩት መንግስታት የፀረ ሙስና ኮንቬንሽን ማፅደቂያ አዋጅ፣ አዋጅ ቁጥር 545/2007 የአፍሪካ ህብረት የሙስና መከላከያ እና መዋጊያ ኮንቬንሽን ማፅደቂያ፣ አዋጅ ቁጥር 668/2002 የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ አዋጅ፣ አዋጅ ቁጥር 1236/2013 የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ እንደገና ማሻሻያ አዋጅ፣ በ1996 ዓ.ም ወጥቶ ስራ ላይ የዋለው የወንጀል ህግ፣ የተሻሻለው የሙስና ወንጀል ህግ አዋጅ/881
የጥቅም ግጭትን የመከላከልና የማስተዳደር ዘዴዎች ምንድን ናቸው?
ግንዛቤ መፍጠር፣ ህግ ማውጣት/ማሻሻል/፣ የአደረጃጀት ለውጥ ማካሄድ፣ ተደራራቢ ስልጣኖችን ማስቀረት፣ የጥቅም ግጭት በተፈጠረባቸው ጉዳዮች ላይ ከተሳትፎ እንዲታገድ ማድረግ /restrict/) ፣ የጥቅም ግጭት ጉዳዮችን በገለልተኛ አካል እንዲታይ ማድረግ፣ መመሪያዎችን ማውጣት ወይም በሌሎች ደንቦችና መመሪያዎች ውስጥ በማካተት የጥቅም ግጭትን መቆጣጠር ናቸው፡፡ ምንጭ:- የፌደራል የስነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን
በኮሌጁ ስነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
የድርጅትንም ሆነ የሀገርን ሀብት ከሚያሳጡ አንዱና ዋናው ሙስና ነው፡፡ ከሙስና ጋር ተያይዞ የሚነሳው ደግሞ አንዱ የጥቅም ግጭት ነው፡፡
በዛሪው ሀተታችን ስለ ጥቅም ግጭት የተውሰነ እናውሳ፡፡ የጥቅም ግጭት ምንድነው?
የጥቅም ግጭት የመወሰን ስልጣን/ሃላፊነት/ ያለው ሰው የግል ጥቅም ከመንግስታዊ ስራ ወይም ኃላፊነት ጋር በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ የሚጋጭ ወይም ግጭት ሊፈጥር የሚችል ሁኔታ ነው፡፡
የጥቅም ግጭት በአንድ ተቋም ውስጥ ያለ ኃላፊነት በግል ህይዎት፣ ማህበራዊ ትስስር እና ጥቅም ላይ ባለ ፍላጎት ተፅዕኖ ዉስጥ የሚወድቅበት ሁኔታ ነው፡፡
ለጥቅም ግጭት መከሰት መንስኤው አንድ ግለሰብ ሁኔታውን እያወቀ ወይም እየተገነዘበ የመወሰን ስልጣኑን ለግል ወይም ለድርጅት ጥቅም ለመጠቀም እድል ሲኖረው ነው። ሙስና የሚፈጠረው ግለሰቡ ያገኘውን ዕድል ተጠቅሞ ቦታውን ለግል ጥቅም ሲጠቀምበት ነው።
የጥቅም ግጭት ሙስና እንዲከሰት መልካም አጋጣሚዎችን ወይም ለሙስና መከሰት ምቹ መንገድን የሚፈጥር ሲሆን፣ የጥቅም ግጭት በራሱ ሙስና አለመሆኑ ነዉ፡፡ ባጭሩ የጥቅም ግጭት ለሙስና መከሰት መንገድ ጠራጊ ነዉ፡፡
የጥቅም ግጭት አይነቶች
1. ተጨባጭ የጥቅም ግጭት /actual or real conflict of interest/፡- ተጨባጭ የጥቅም ግጭት የሚፈጠረዉ የመንግስት ባለስልጣን ኃላፊነቱን እየተወጣ ሳለ ያለ ተፅዕኖ ወይም ያለአድሎ የመወሰን ኃላፊነቱን የሚፈታተን ሁኔታ ወይም ክሰተት በተጨባጭ/በትክክል ሲያጋጥመዉ
2. . ተጋላጭ/እምቅ/ የጥቅም ግጭት/potential conflict of interest/፡- ተጋላጭ የጥቅም ግጭት በተጨባጭ ያላጋጠመ ነገር ግን ወደፊት ሊያጋጥም የሚችል እድል ያለዉ ሁኔታ ወይም ክስተት ነዉ፡፡
3. ተገማች/ተጠርጣሪ የጥቅም ግጭት /perceived conflict of interest/፡- ግንዛቤያዊ የጥቅም ግጭት የዉሳኔ አሰጣጦችን ከተጽዕኖ ነጻ መሆን የሚጋፉ ሁኔታዎች መኖራቸዉን ሃላፊነት የወለዳቸዉ ጥቅሞች ይኖራሉ የሚያስብል ጥርጣሬዎችን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች ናቸዉ፡፡
የጥቅም ግጭት ለመከላከል የተደነገገ/የወጣ አዋጅ /ፖሊሲ/ ደንብ
1987 የኢፌዴሪ ህገ መንግስት፣ አዋጅ ቁጥር 544/2007 የተባበሩት መንግስታት የፀረ ሙስና ኮንቬንሽን ማፅደቂያ አዋጅ፣ አዋጅ ቁጥር 545/2007 የአፍሪካ ህብረት የሙስና መከላከያ እና መዋጊያ ኮንቬንሽን ማፅደቂያ፣ አዋጅ ቁጥር 668/2002 የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ አዋጅ፣ አዋጅ ቁጥር 1236/2013 የኮሚሽኑ ማቋቋሚያ አዋጅ እንደገና ማሻሻያ አዋጅ፣ በ1996 ዓ.ም ወጥቶ ስራ ላይ የዋለው የወንጀል ህግ፣ የተሻሻለው የሙስና ወንጀል ህግ አዋጅ/881
የጥቅም ግጭትን የመከላከልና የማስተዳደር ዘዴዎች ምንድን ናቸው?
ግንዛቤ መፍጠር፣ ህግ ማውጣት/ማሻሻል/፣ የአደረጃጀት ለውጥ ማካሄድ፣ ተደራራቢ ስልጣኖችን ማስቀረት፣ የጥቅም ግጭት በተፈጠረባቸው ጉዳዮች ላይ ከተሳትፎ እንዲታገድ ማድረግ /restrict/) ፣ የጥቅም ግጭት ጉዳዮችን በገለልተኛ አካል እንዲታይ ማድረግ፣ መመሪያዎችን ማውጣት ወይም በሌሎች ደንቦችና መመሪያዎች ውስጥ በማካተት የጥቅም ግጭትን መቆጣጠር ናቸው፡፡ ምንጭ:- የፌደራል የስነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን
በኮሌጁ ስነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
👍9❤3👎1
ሐሙስ፡- ጥር 2 ቀን 2016 ዓ.ም
የ2016 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ጥር 2 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት የግማሽ ዓመቱን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በሁሉም ዳይሬክተሮች የራሳቸውን የስራ ክፍል አፈፃፀም ለታዳሚዎች አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ሪፖርት መረጃ መሰረት በግማሽ ዓመቱ ልዩ ልዩ ግብዓቶችን ከማሟላት አንፃር፣ የተቋሙን መሰረተ ልማት ከማስተካከል አኳያ እና ሁሉም አካል በየዘርፉ ተነሳሽነት እና ቅንጅት ፈጥሮ ስራዎችን ከመከወን ረገድ እምርታዊ ለውጥ ያሳዬ እና ስኬታማ እንደነበር ተገልጿል፡፡
በእቅድ አፈፃፀም ውይይቱ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎችም በቀሪው ግማሽ ዓመት ከስልጠና ሂደት፣ ከግብዓት አቅርቦት፣ ከውስጥ አሰራር፣ ከተቋማዊ ልማት እና ከማህበራዊ አግልግሎት አንፃር ቢስተካከሉ ያሏቸውን ገንቢ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የ2016 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ዛሬ ጥር 2 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሄደ፡፡
ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት የግማሽ ዓመቱን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በሁሉም ዳይሬክተሮች የራሳቸውን የስራ ክፍል አፈፃፀም ለታዳሚዎች አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ሪፖርት መረጃ መሰረት በግማሽ ዓመቱ ልዩ ልዩ ግብዓቶችን ከማሟላት አንፃር፣ የተቋሙን መሰረተ ልማት ከማስተካከል አኳያ እና ሁሉም አካል በየዘርፉ ተነሳሽነት እና ቅንጅት ፈጥሮ ስራዎችን ከመከወን ረገድ እምርታዊ ለውጥ ያሳዬ እና ስኬታማ እንደነበር ተገልጿል፡፡
በእቅድ አፈፃፀም ውይይቱ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎችም በቀሪው ግማሽ ዓመት ከስልጠና ሂደት፣ ከግብዓት አቅርቦት፣ ከውስጥ አሰራር፣ ከተቋማዊ ልማት እና ከማህበራዊ አግልግሎት አንፃር ቢስተካከሉ ያሏቸውን ገንቢ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍7❤3👏1👌1