አርብ፡- ታህሳስ 4 ቀን 2017 ዓ.ም
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ለሚሰጡ አሰልጣኛኞች ስልጠና ተሰጠ!!
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አገልግሎት ለሚሰጡ የኮሌጁ አሰልጣኛኞች የ5 ቀናት ስልጠና ተሰጠ::
በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ልማትና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲን ቢሮ በኩል 40 ለሚሆኑ አሰልጣኞች ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ትግበራ ጋር በተያያዘ ስልጠና ተሰጥቷል።
ስልጠናው ከህዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ዛሬ የተጠናቀቀ ሲሆን ይዘቱም ድጋፍ ከሚሰጥባቸው ማዕቀፎች መካከል በኢንተርፕርነርና በካይዘን ትግበራ ዙሪያ መሆኑን ሰምተናል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ለሚሰጡ አሰልጣኛኞች ስልጠና ተሰጠ!!
የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አገልግሎት ለሚሰጡ የኮሌጁ አሰልጣኛኞች የ5 ቀናት ስልጠና ተሰጠ::
በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ልማትና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ም/ዲን ቢሮ በኩል 40 ለሚሆኑ አሰልጣኞች ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ትግበራ ጋር በተያያዘ ስልጠና ተሰጥቷል።
ስልጠናው ከህዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ዛሬ የተጠናቀቀ ሲሆን ይዘቱም ድጋፍ ከሚሰጥባቸው ማዕቀፎች መካከል በኢንተርፕርነርና በካይዘን ትግበራ ዙሪያ መሆኑን ሰምተናል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ማክሰኞ:- ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓ.ም
በስነ ምግባርና መልካም አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን በመጡ ባለሙያዎች በስነ ምግባርና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ለኮሌጁ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
ስልጠናው ትናንት ጀምሮ ሁለት ቀናት የፈጀ ሲሆን በስነ ምግባርና በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በሙስና መከላከል ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ነው።
የስልጠናው ዓላማ ከሙስናና ከብልሹ ተግባር ነጻ የሆነ ዜጋ መፍጠር እንዲሁም መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ከብልሹ አሰራር የፀዳ ፍትሀዊ አገልግሎት ለሁሉም ዜጎች በእኩል ደረጃ ለመስጠት ነው ተብሏል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
በስነ ምግባርና መልካም አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ!!
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን በመጡ ባለሙያዎች በስነ ምግባርና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ለኮሌጁ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
ስልጠናው ትናንት ጀምሮ ሁለት ቀናት የፈጀ ሲሆን በስነ ምግባርና በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በሙስና መከላከል ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ነው።
የስልጠናው ዓላማ ከሙስናና ከብልሹ ተግባር ነጻ የሆነ ዜጋ መፍጠር እንዲሁም መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ከብልሹ አሰራር የፀዳ ፍትሀዊ አገልግሎት ለሁሉም ዜጎች በእኩል ደረጃ ለመስጠት ነው ተብሏል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ማክሰኞ:- ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓ.ም
ሁለተኛው የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት ጀመረ!!
በኮሌጁ ዋና በር መግቢያ ላይ የሚገኘውና በተለምዶ ትንሹ የእግር ኳስ ሜዳ እየተባለ በሚጠራው ቦታ ደረጃውን የጠበቀ አራት ዘመናዊ የእግር ኳስ ማዘውተሪያ ሜዳ ለማሰራት ታቅዶ ወደ ስራ ከተገባ በኋላ የሁለተኛዋው ሜዳ ስራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
የማህበረሰብ የግል አጋርነት ተሳትፎ /Public Private Partnership participation/ በሚለው መርህ መሰረት ፉት ፒች ኃላ/የተ/የግ ድርጅት በተሰኘ የግል ኩባንያ ግንባታው እየተሰራ የሚገኘው የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳ አሁን ላይ ከ4ቱ ውስጥ 2ቱ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት ሲገቡ ሁለቱ ደግሞ እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡
በትንሹ ወደ 20 ሚሊዮን ብር ወጪ ይጠይቃል የተባለለትን ይህን ፕሮጀክት ኮሌጁ የግል አልሚዎችን በመጋበዝ መተግበሩ በማህበረስብ አገልገሎት ዘርፍ የአካባቢው ወጣቶች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጊዜያቸውን እንዲያሳልፉ፣ የኮሌጁ ተቋማዊ ገጽታ ማራኪ እንዲሆን፣ የኮሌጁ የውስጥ ገቢ እንዲያድግ፣ ለተለያዩ የጤና ስፖርት ቡድኖችና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ስፖርታዊ እንቀስቃሴ እንዲያደርጉ ያገለግላል ተብሏል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ሁለተኛው የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት ጀመረ!!
በኮሌጁ ዋና በር መግቢያ ላይ የሚገኘውና በተለምዶ ትንሹ የእግር ኳስ ሜዳ እየተባለ በሚጠራው ቦታ ደረጃውን የጠበቀ አራት ዘመናዊ የእግር ኳስ ማዘውተሪያ ሜዳ ለማሰራት ታቅዶ ወደ ስራ ከተገባ በኋላ የሁለተኛዋው ሜዳ ስራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
የማህበረሰብ የግል አጋርነት ተሳትፎ /Public Private Partnership participation/ በሚለው መርህ መሰረት ፉት ፒች ኃላ/የተ/የግ ድርጅት በተሰኘ የግል ኩባንያ ግንባታው እየተሰራ የሚገኘው የእግር ኳስ መለማመጃ ሜዳ አሁን ላይ ከ4ቱ ውስጥ 2ቱ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት ሲገቡ ሁለቱ ደግሞ እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡
በትንሹ ወደ 20 ሚሊዮን ብር ወጪ ይጠይቃል የተባለለትን ይህን ፕሮጀክት ኮሌጁ የግል አልሚዎችን በመጋበዝ መተግበሩ በማህበረስብ አገልገሎት ዘርፍ የአካባቢው ወጣቶች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጊዜያቸውን እንዲያሳልፉ፣ የኮሌጁ ተቋማዊ ገጽታ ማራኪ እንዲሆን፣ የኮሌጁ የውስጥ ገቢ እንዲያድግ፣ ለተለያዩ የጤና ስፖርት ቡድኖችና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ስፖርታዊ እንቀስቃሴ እንዲያደርጉ ያገለግላል ተብሏል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
አርብ:- ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
ኮሌጁ በመደበኛ ኢንስፔክሽን ምዘና እንደ ከተማ አንደኛ ወጣ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተደረገው መደበኛ የኢንስፔክሽን ምዘና ውጤት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ከሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ አንደኛ ደረጃ ወጣ፡፡
ምዘናውን ያካሄደው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሲሆን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በ2016 በጀት ዓመት ባደረገው የተቋማት ብቃት ልኬት መሰረት ነው፡፡
በዚህም ኮሌጁ ባለው የስልጠና ወርክ ሾፕ እና የሰው ኃይል ግብዓት መጠንና ጥራት፣ በስልጠና ሂደቱ ያለው አተገባበር እና በተቋማዊ አፈፃፀም ብቃት፣ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪ ለመሆን እያደረገው ያለው ትጋት እንዲሁም በተቋማዊ አመራር እና አደረጃጀት ስርዓት ተመዝኖ የስታንዳርዱን ከፍተኛ ውጤት በማምጣቱ ከባለ ስልጣን መስሪያ ቤቱ የዋንጫ እና የሰርተፊኬት ሸልማት ተበርክቶለታል፡፡
በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ ለመሆን ራዕይን ሰንቆ በስኬት እየተጓዘ የሚገኘው ኮሌጃችን አሁን ላይ በሀገሪቱ ለሚገኙ አቻ ተቋማት በብዙ አዳዲስ ተግባራቱ አርአያ ሆኖ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡
ለዚህ ዘርፈ ብዙ ውጤት መገኘት የእያንዳንዱ የኮሌጁ ማህበረሰብ ትጋት ድምር ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን ታሪካዊና ቀዳማዊ በሆነው የብቁ ዜጎች ማፍሪያ ተቋም ቀጣይም አሻራችሁን በማይደበዝዝ ቀለም በማስቀመጥ አበርክቷችሁን አብልጣችሁ እንዲትቀጥሉበት እንገልጻለን፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ኮሌጁ በመደበኛ ኢንስፔክሽን ምዘና እንደ ከተማ አንደኛ ወጣ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተደረገው መደበኛ የኢንስፔክሽን ምዘና ውጤት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ከሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ አንደኛ ደረጃ ወጣ፡፡
ምዘናውን ያካሄደው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሲሆን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በ2016 በጀት ዓመት ባደረገው የተቋማት ብቃት ልኬት መሰረት ነው፡፡
በዚህም ኮሌጁ ባለው የስልጠና ወርክ ሾፕ እና የሰው ኃይል ግብዓት መጠንና ጥራት፣ በስልጠና ሂደቱ ያለው አተገባበር እና በተቋማዊ አፈፃፀም ብቃት፣ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪ ለመሆን እያደረገው ያለው ትጋት እንዲሁም በተቋማዊ አመራር እና አደረጃጀት ስርዓት ተመዝኖ የስታንዳርዱን ከፍተኛ ውጤት በማምጣቱ ከባለ ስልጣን መስሪያ ቤቱ የዋንጫ እና የሰርተፊኬት ሸልማት ተበርክቶለታል፡፡
በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ ለመሆን ራዕይን ሰንቆ በስኬት እየተጓዘ የሚገኘው ኮሌጃችን አሁን ላይ በሀገሪቱ ለሚገኙ አቻ ተቋማት በብዙ አዳዲስ ተግባራቱ አርአያ ሆኖ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡
ለዚህ ዘርፈ ብዙ ውጤት መገኘት የእያንዳንዱ የኮሌጁ ማህበረሰብ ትጋት ድምር ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን ታሪካዊና ቀዳማዊ በሆነው የብቁ ዜጎች ማፍሪያ ተቋም ቀጣይም አሻራችሁን በማይደበዝዝ ቀለም በማስቀመጥ አበርክቷችሁን አብልጣችሁ እንዲትቀጥሉበት እንገልጻለን፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ማክሰኞ:- ታህሳስ 15 ቀን 2017 ዓ∙ም
በኮሌጁ የተሰሩ ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች ተመረቁ!!
በኮሌጁ የተሰሩ ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች በክቡር አቶ ጥራቱ በየነ አማካኝነት ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2017 ዓ∙ም ተመረቁ፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ በሆኑት ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የተመራ ልዑካን ቡድን በኮሌጁ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በተቋሙ ተሰርተው የተጠናቀቁ የማሰልጠኛ እና የውስጥ ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።
በዕለቱ የቢሮው የስራ ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተሞችና የወረዳዎች ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራ እና ክህሎት ጽ/ቤቶች ኃላፊዎች እና በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ዋና ዲኖች ተገኝተው ጎብኝተዋል፡፡
የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሪፎርም ስራዎችን በመጀመር እንዲሁም የISO 9001፡2015 ዓለም አቀፍ የጥራት ስራ አመራር ባለቤት በመሆን ፈር ቀዳጅ ነው ያሉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ናቸው፡፡ ኃላፊው አክለውም ይህ እንዲሳካ ላደረጉ ለኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ምስጋና ይገባቸዋል፤ ሌሎች ተቋማትም ይህንን አርአያነት ወስደው ተቋማቸውን ምቹና ማራኪ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው ዕለት በተካሄደው መድረክ ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች የርክክብ ስነ- ስርዓት ተካሂዷል፡፡
በዚህም ለተቋማዊ ሪፎርም ይረዳ ዘንድ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተገዙ እና 47 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው ላፕቶፓች፣ ደስክ ቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ፕሪንተሮች እና ፕሮጀክተሮች ለተወሰኑ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ለሚገኙ የስራና ክህሎት ጽ/ቤቶች እና ኮሌጆች ተበርክቷል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
በኮሌጁ የተሰሩ ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች ተመረቁ!!
በኮሌጁ የተሰሩ ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች በክቡር አቶ ጥራቱ በየነ አማካኝነት ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2017 ዓ∙ም ተመረቁ፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ በሆኑት ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የተመራ ልዑካን ቡድን በኮሌጁ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በተቋሙ ተሰርተው የተጠናቀቁ የማሰልጠኛ እና የውስጥ ገቢ ማስገኛ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።
በዕለቱ የቢሮው የስራ ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተሞችና የወረዳዎች ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራ እና ክህሎት ጽ/ቤቶች ኃላፊዎች እና በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ዋና ዲኖች ተገኝተው ጎብኝተዋል፡፡
የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሪፎርም ስራዎችን በመጀመር እንዲሁም የISO 9001፡2015 ዓለም አቀፍ የጥራት ስራ አመራር ባለቤት በመሆን ፈር ቀዳጅ ነው ያሉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ናቸው፡፡ ኃላፊው አክለውም ይህ እንዲሳካ ላደረጉ ለኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ምስጋና ይገባቸዋል፤ ሌሎች ተቋማትም ይህንን አርአያነት ወስደው ተቋማቸውን ምቹና ማራኪ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው ዕለት በተካሄደው መድረክ ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች የርክክብ ስነ- ስርዓት ተካሂዷል፡፡
በዚህም ለተቋማዊ ሪፎርም ይረዳ ዘንድ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተገዙ እና 47 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው ላፕቶፓች፣ ደስክ ቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ፕሪንተሮች እና ፕሮጀክተሮች ለተወሰኑ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ለሚገኙ የስራና ክህሎት ጽ/ቤቶች እና ኮሌጆች ተበርክቷል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"