Forwarded from K-Raj 🌍 AB
https://youtu.be/3KnstGeVto0
Students are not registering, I observe that, most of new trainees are thinking as the registration is done by only making Application form in last weeks,
So notifying them is good! may if it makes more clear more full detailed registration videos is here, it is good there them
Students are not registering, I observe that, most of new trainees are thinking as the registration is done by only making Application form in last weeks,
So notifying them is good! may if it makes more clear more full detailed registration videos is here, it is good there them
ሰኞ፡- ህዳር 2 ቀን 2017 ዓ.ም
ለአዲስ ተመዝጋቢ የቀን ሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብር ተካሄደ!!
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 2017 ዓ.ም ላይ ሙያዊ ስልጠናቸውን ለመከታተል ላመለከቱ አዳዲስ የቀን ሰልጣኞች በዛሬ ዕለት የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብር ተዘጋጀላቸው፡፡
በዚህ መድረክ ላይም በበጀት ዓመቱ በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናቸውን ለመከታተል ያመለከቱ አዳዲስ ሰልጣኞች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ የኮሌጁ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ አድማሱ በቀለ በቦታው በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ምክትል ዲኑ በመልዕክታቸው እኛን መርጣችሁ ስለመጣችሁ እናመሰግናለን፤ ኮሌጃችንንም በመምረጣችሁ ዕድለኞች ናችሁ፡፡ ተግታችሁ ከሰለጠናችሁ ደግሞ የስራ ገበያው ኢንዱስትሪዎች የምረቃ ቀናችሁን ሳይጠብቁ ቀድመው ሊወስዷችሁ በራቸው ክፍት ነው ብለዋቸዋል፡፡
የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብሩን ምክኒያት በማድረግ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ስሙ የጎላው ሰርከስ ዊንጌት ልዩ ልዩ አዝናኝ ትርኢቶችን በማቅረብ ታዳሚዎችን ያስደመመ ሲሆን ቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት ዲፓርትመንት ደግሞ በሰልጣኞች የተሰሩ የፋሽን ዲዛይኖችን መድረክ ላይ በማሳየት ስልጠናቸውን የማስተዋወቅ ስራ አከናውነዋል፡፡
አሁኑ ላይ በሶስቱም የስልጠና መርሃ ግብር ማለትም በቀን፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ 4045 የሚሆኑ አዳዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች በኮሌጁ ገብተው ለመሰልጠን ያመለከቱ ሲሆን በቀኑ የስልጠና ጊዜ ለመከታተል ያመለከቱ አዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም ላይ መደበኛ ስልጠናቸውን እንደሚጀምሩ ታውቋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ለአዲስ ተመዝጋቢ የቀን ሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብር ተካሄደ!!
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 2017 ዓ.ም ላይ ሙያዊ ስልጠናቸውን ለመከታተል ላመለከቱ አዳዲስ የቀን ሰልጣኞች በዛሬ ዕለት የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብር ተዘጋጀላቸው፡፡
በዚህ መድረክ ላይም በበጀት ዓመቱ በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናቸውን ለመከታተል ያመለከቱ አዳዲስ ሰልጣኞች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ የኮሌጁ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ አድማሱ በቀለ በቦታው በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ምክትል ዲኑ በመልዕክታቸው እኛን መርጣችሁ ስለመጣችሁ እናመሰግናለን፤ ኮሌጃችንንም በመምረጣችሁ ዕድለኞች ናችሁ፡፡ ተግታችሁ ከሰለጠናችሁ ደግሞ የስራ ገበያው ኢንዱስትሪዎች የምረቃ ቀናችሁን ሳይጠብቁ ቀድመው ሊወስዷችሁ በራቸው ክፍት ነው ብለዋቸዋል፡፡
የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብሩን ምክኒያት በማድረግ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ስሙ የጎላው ሰርከስ ዊንጌት ልዩ ልዩ አዝናኝ ትርኢቶችን በማቅረብ ታዳሚዎችን ያስደመመ ሲሆን ቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት ዲፓርትመንት ደግሞ በሰልጣኞች የተሰሩ የፋሽን ዲዛይኖችን መድረክ ላይ በማሳየት ስልጠናቸውን የማስተዋወቅ ስራ አከናውነዋል፡፡
አሁኑ ላይ በሶስቱም የስልጠና መርሃ ግብር ማለትም በቀን፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ 4045 የሚሆኑ አዳዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች በኮሌጁ ገብተው ለመሰልጠን ያመለከቱ ሲሆን በቀኑ የስልጠና ጊዜ ለመከታተል ያመለከቱ አዲስ ተመዝጋቢ ሰልጣኞች ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም ላይ መደበኛ ስልጠናቸውን እንደሚጀምሩ ታውቋል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
https://youtu.be/3KnstGeVto0
Students are not registering, I observe that, most of new trainees are thinking as the registration is done by only making Application form in last weeks,
So notifying them is good! may if it makes more clear more full detailed registration videos is here, it is good there them
Students are not registering, I observe that, most of new trainees are thinking as the registration is done by only making Application form in last weeks,
So notifying them is good! may if it makes more clear more full detailed registration videos is here, it is good there them
በዚህ ሳምንት
አርብ፡- ህዳር 6 ቀን 2017 ዓ.ም
ከሀገረ ጀርመን የመጡ ልዑካን ቡድን በኮሌጁ ጉብኘት አደረጉ!!
በሀገረ ጀርመን የኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ዘርፍ ላይ የሚሰሩ የልዑካን ቡድን አባላት ከትናነት በስተያ በኮሌጁ ጉብኘት አድርገዋል።
የልዑካኑ ጉብኝት መሰረታዊ ዓላማ ጀርመን በአሁኑ ሰዓት በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ ባጋጠማት የሰለጠነ የሰው ሃበት እጥረት ምክኒያት በሙያው ብቁ የሆኑ ዜጎችን ከሀገራችን በመመልመል ለመቅጠር እቅድ በመያዟ ኮሌጃችን እንደ አንድና ዋነኛ ብቁ የሰው ሃይል መገኛ ተቋም በመያዙ ነው።
በዚህም በመጀመሪያው ዙር ምልከታና ውይይት ኮሌጁ ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደረጃና የአስተሳሰብ ምጥቀት ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ያለው ቁሳዊና ሰብዓዊ ግብዓት ምን ይመስላል የሚለውን ማሳየትና ማስጎብኘት ተችሏል።
ይህ እቅድ ስምምምነት ላይ ተደርሶ ወደ ትግበራ ከተገባ የጀርመንና የኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት ከማጠናከር ባሻገር ቀጣይ ዓለማቀፋዊ የስራ ትስስር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሰው ሃብት ልማት ትብብር እና መሰል ሀገራዊ ትሩፋቶች ላይ የሚኖረው ዕድል ላቅ ያለ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
ቀጣይ በዚሁ ዙሪያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ንግግሮችና የመግባቢያ ስምምነቶች እንደሚኖሩ የሚጠበቅ ሲሆን ወደ ትግበራ ሲገባ ለሰልጣኞች ቋንቋን ጨምሮ ከጀርመን ሀገር የስራ ባህል ነባራዊ ሁኒታ ጋር የሚያያዙ የተለያዩ ስልጠናዎች እንደሚሰጣቸውም ይጠበቃል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
አርብ፡- ህዳር 6 ቀን 2017 ዓ.ም
ከሀገረ ጀርመን የመጡ ልዑካን ቡድን በኮሌጁ ጉብኘት አደረጉ!!
በሀገረ ጀርመን የኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ዘርፍ ላይ የሚሰሩ የልዑካን ቡድን አባላት ከትናነት በስተያ በኮሌጁ ጉብኘት አድርገዋል።
የልዑካኑ ጉብኝት መሰረታዊ ዓላማ ጀርመን በአሁኑ ሰዓት በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ ባጋጠማት የሰለጠነ የሰው ሃበት እጥረት ምክኒያት በሙያው ብቁ የሆኑ ዜጎችን ከሀገራችን በመመልመል ለመቅጠር እቅድ በመያዟ ኮሌጃችን እንደ አንድና ዋነኛ ብቁ የሰው ሃይል መገኛ ተቋም በመያዙ ነው።
በዚህም በመጀመሪያው ዙር ምልከታና ውይይት ኮሌጁ ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደረጃና የአስተሳሰብ ምጥቀት ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ያለው ቁሳዊና ሰብዓዊ ግብዓት ምን ይመስላል የሚለውን ማሳየትና ማስጎብኘት ተችሏል።
ይህ እቅድ ስምምምነት ላይ ተደርሶ ወደ ትግበራ ከተገባ የጀርመንና የኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት ከማጠናከር ባሻገር ቀጣይ ዓለማቀፋዊ የስራ ትስስር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሰው ሃብት ልማት ትብብር እና መሰል ሀገራዊ ትሩፋቶች ላይ የሚኖረው ዕድል ላቅ ያለ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
ቀጣይ በዚሁ ዙሪያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ንግግሮችና የመግባቢያ ስምምነቶች እንደሚኖሩ የሚጠበቅ ሲሆን ወደ ትግበራ ሲገባ ለሰልጣኞች ቋንቋን ጨምሮ ከጀርመን ሀገር የስራ ባህል ነባራዊ ሁኒታ ጋር የሚያያዙ የተለያዩ ስልጠናዎች እንደሚሰጣቸውም ይጠበቃል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"