General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.95K subscribers
3.35K photos
43 videos
204 files
196 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
On line Registration procedure
በዊንጌት ኮሌጅ ሰዓትና ቦታ ቀን ሳይገድቦ on line ለመመዝገብ ይሄን ሂደት ይከተሉ።
Location ለጠየቃቹ
ሐሙስ:- ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ∙ም

   በኮሌጃችን ሌላም አዲስ የምስራች ይዘን መጥተናል!!

ፋዌ ኢትዮጵያ ቻፕተር እና ፋዌ አፍሪካ ከማስተር ካርድ ፋውንደሽን ጋር በመተባበር በ2017 ዓ.ም ሃርድ ስኪል ስልጠና ላይ ለመከታተል ለተመዘገባችሁ አዳዲስ ሰልጣኞች የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲትሆኑ ጥሪ ቀርቦላችኋል፡፡

እንደ አዲስ አበባ የዕድሉ ተጠቃሚ ከሆኑ 2 ፖሊ ኮሌጆች መካከል ጀነራል ዊንጌት አንዱ ሲሆን ከፍተኛውን ዕድል ለሴቶች አድርጎ የሚተገበር ነው፡፡

ስለሆነም ከ15 እስከ 25 ዕድሜ የሆናችሁ፣ የስልጠና መግቢያውን መስፈርት የምታሟሉ፣ ሃርድ ስኪል ስልጠና ላይ ያመለከታችሁ ተጠቃሚዎች መሆን የምትችሉ ሲሆን የተጠቃሚዎች ስብጥር ደግሞ 80 ከመቶ ለሴቶች 20 ፐርሰንት ለወንዶች ይሆናል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ከ5 እስከ 10 ፐርሰንት ለአካል ጉዳተኛ ከ10 እስከ 15 ፐርሰንቱ ደግሞ ለተፈናቃይ መሆኑ ታውቋል፡፡

የማመልከቻ ጊዜ ከጥቅምት 22 እስከ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሆን ለተጨማሪ መረጃ 0911330024 ወይም 0902662688 መደወል ትችላላችሁ ተብላችኋል፡፡  

የድጋፉ ተጠቃሚ አካል ለመሆን መስፈርቱን የምታሟሉ አዳዲስ ሰልጣኞች በኮሌጁ አስተዳደር ህንፃ ግሪውንድ ላይ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን ቢሮ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ማመልከት እንደምትችሉ ተነግሯል።

"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
አርብ:- ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ∙ም

በኮሌጁ የአቻ ለአቻ ውይይትና የባህርይ ለውጥ ስልጠና ተሰጠ!!

በኮሌጁ ጤና ባሙያዎች ሁለት ቀናት ቆይታ የነበረው የአቻ ለአቻ ውይይትና የባህርይ ለውጥ ስልጠና ተሰጠ፡፡

በዚህ መድረክ የኮሌጁ ሰራተኞችና ከሰልጣኞች የተወከሉ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን ጥቅምት 21 እና 22 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡

በዚህ ቆይታ በህይወት ክህሎት፣ በስርዓተ ፆታ፣ በኤች አይ ቪ ሚኒስትሪሚንግና መሰል ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ተችሏል፡፡

"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"