ቅዳሜ:- ሚያዚያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም
ለኮሌጁ እንሰሳት ተንከባካቢ ሰራተኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው!!
ለኮሌጁ የዶሮ እርባታ እና የወተት ላሞች እርባታ ጣቢያ ሰራተኞች በተቋሙ የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት አሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
ስልጠናው ከዶሮ እርባታ አንፃር፣ ከውተት ላሞች እንክብካቤ ረገድ እና ከእንሰሳት ጤና አጠባበቅ አኳያ ትኩረት ያደረገ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ስልጠናውን ያዘጋጀው የንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ሲሆን ስልጠናውን የሰጠው ደግሞ የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት ነው፡፡ ስልጠናው 15 ቀናት የተያዘለት ሲሆን 10ሩን በተግባራዊ ልምምድ የሚሸፈን እንደሆነ ተነግሯል፡፡
የስልጠናው አስፈላጊነት ምርታማነትን ለማሳደግ እና የእንሰሳቱን አካላዊ ጤና ለመጠበቅ ታቅዶ መዘጋጀቱን የንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ደረጀ ጨመዳ ገልፀውልናል፡፡
የእንሰሳቱን ጤና መጠበቅ እና ምርታማነትን ማሳደግ የእንሰሳት ተዋጽኦ ምርት አቅርቦቱን ለኮሌጁ ማህበረሰብ ከመጨመር ባሻገር የዲፓርትመንቱን የስልጠና ሂደት የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ይረዳል ያሉን ደግሞ የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት ኃላፊ አቶ ታሪኩ በቀለ ናቸው፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
ለኮሌጁ እንሰሳት ተንከባካቢ ሰራተኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው!!
ለኮሌጁ የዶሮ እርባታ እና የወተት ላሞች እርባታ ጣቢያ ሰራተኞች በተቋሙ የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት አሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
ስልጠናው ከዶሮ እርባታ አንፃር፣ ከውተት ላሞች እንክብካቤ ረገድ እና ከእንሰሳት ጤና አጠባበቅ አኳያ ትኩረት ያደረገ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ስልጠናውን ያዘጋጀው የንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ሲሆን ስልጠናውን የሰጠው ደግሞ የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት ነው፡፡ ስልጠናው 15 ቀናት የተያዘለት ሲሆን 10ሩን በተግባራዊ ልምምድ የሚሸፈን እንደሆነ ተነግሯል፡፡
የስልጠናው አስፈላጊነት ምርታማነትን ለማሳደግ እና የእንሰሳቱን አካላዊ ጤና ለመጠበቅ ታቅዶ መዘጋጀቱን የንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ደረጀ ጨመዳ ገልፀውልናል፡፡
የእንሰሳቱን ጤና መጠበቅ እና ምርታማነትን ማሳደግ የእንሰሳት ተዋጽኦ ምርት አቅርቦቱን ለኮሌጁ ማህበረሰብ ከመጨመር ባሻገር የዲፓርትመንቱን የስልጠና ሂደት የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ይረዳል ያሉን ደግሞ የከተማ ግብርና ዲፓርትመንት ኃላፊ አቶ ታሪኩ በቀለ ናቸው፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍12👎1
ቅዳሜ:- ሚያዚያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም
በኮሌጅ ደረጃ የክህሎት ውድድር ተካሄደ!!
በኮሌጅ ደረጃ የአሰልጣኞች፣ የሰልጣኞች እና የአንቀሳቃሾች ክህሎት ውድድር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ተካሄደ።
የክህሎት ውድድር የተደረገባቸው ዲፓርንመንቶች ኮንስትራክሽን፣ ኤሌክትሪክሲቲ እና ኤሌክትሮኒክስ፣ ቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት፣ ሜታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ፣ ኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ እና ውድ ወርክ ቴክኖሎጂ ናቸው፡፡
በዚህ ውድድር 23 አሰልጣኞች በ14 ሙያዎች፣ 32 ሰልጣኞች በ9 ዘርፎች እና 1 አንቀሳቃሽ ደግሞ በ1 የሙያ መስክ በኮሌጅ ደረጃ የክህሎት ውድድር ተካሂዷል፡፡
ውድድሩ የያዛቸው ሙያዎች ከሜታል ቴክኖሎጂ በመካኒክስ፣ በማሽኒንግና በዌልዲንግ፤ ከኤሌክትሪክሲቲ እና ኤሌክትሮኒክስ በቢውልዲንግ ኤሌክትሪካል ኢንስታሌሽና በኢንዱስትሪያል ኤሌክትረካል ማሽን ዲራይቭ፤ ከኮንስትራክሽን በሳኒተሪ ኢንስታሌሽንና በታይሊንግ፤ ከቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት በአድቫንስድ አፓረል ፕሮዳክሽን፣ በቴክስታይል ኬሚካል ፕሮዳክሽንና በሌዘር ፕሮዳክሽን፤ ከውድ ወርክ ቴክኖሎጂ በፈርኒቸር ሚኪንግ፤ ከአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ በአውቶ ኤሌክትረካል ወርክና በአውቶ ኢንጂን ሰርቪስ እና ከኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ደግሞ በዳታ ቤዝ አድሚኒስትሬሽን እና በሃርድ ዌርና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ነው፡፡
ውድድሩ በትናንት ዕለት የሰልጣኞች እና የአንቀሳቃሾች ሲካሄድ ዛሬ ደግሞ የአሰልጣኞቹ ተደርጓል፡፡ ከሁሉም ዘርፎች 1ኛ ደረጃን ይዘው ያጠናቀቁ ተወዳዳሪዎች ቀጣይ በክላስተር ደረጃ በሚደረገው ፊልሚያ ይሳተፋሉ፡፡
አሰልጣኞች የሚወዳደሩት በደረጃ 4 ሲሆን ሰልጣኞች እና አንቀሳቃሾች ደግሞ በደጃ 3 እንደሚመዘኑ ታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
በኮሌጅ ደረጃ የክህሎት ውድድር ተካሄደ!!
በኮሌጅ ደረጃ የአሰልጣኞች፣ የሰልጣኞች እና የአንቀሳቃሾች ክህሎት ውድድር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ተካሄደ።
የክህሎት ውድድር የተደረገባቸው ዲፓርንመንቶች ኮንስትራክሽን፣ ኤሌክትሪክሲቲ እና ኤሌክትሮኒክስ፣ ቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት፣ ሜታል ቴክኖሎጂ፣ አውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ፣ ኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ እና ውድ ወርክ ቴክኖሎጂ ናቸው፡፡
በዚህ ውድድር 23 አሰልጣኞች በ14 ሙያዎች፣ 32 ሰልጣኞች በ9 ዘርፎች እና 1 አንቀሳቃሽ ደግሞ በ1 የሙያ መስክ በኮሌጅ ደረጃ የክህሎት ውድድር ተካሂዷል፡፡
ውድድሩ የያዛቸው ሙያዎች ከሜታል ቴክኖሎጂ በመካኒክስ፣ በማሽኒንግና በዌልዲንግ፤ ከኤሌክትሪክሲቲ እና ኤሌክትሮኒክስ በቢውልዲንግ ኤሌክትሪካል ኢንስታሌሽና በኢንዱስትሪያል ኤሌክትረካል ማሽን ዲራይቭ፤ ከኮንስትራክሽን በሳኒተሪ ኢንስታሌሽንና በታይሊንግ፤ ከቴክስታይል ሌዘር ጋርመንት በአድቫንስድ አፓረል ፕሮዳክሽን፣ በቴክስታይል ኬሚካል ፕሮዳክሽንና በሌዘር ፕሮዳክሽን፤ ከውድ ወርክ ቴክኖሎጂ በፈርኒቸር ሚኪንግ፤ ከአውቶሞቲቭ ቴክኖሎጂ በአውቶ ኤሌክትረካል ወርክና በአውቶ ኢንጂን ሰርቪስ እና ከኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ደግሞ በዳታ ቤዝ አድሚኒስትሬሽን እና በሃርድ ዌርና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ነው፡፡
ውድድሩ በትናንት ዕለት የሰልጣኞች እና የአንቀሳቃሾች ሲካሄድ ዛሬ ደግሞ የአሰልጣኞቹ ተደርጓል፡፡ ከሁሉም ዘርፎች 1ኛ ደረጃን ይዘው ያጠናቀቁ ተወዳዳሪዎች ቀጣይ በክላስተር ደረጃ በሚደረገው ፊልሚያ ይሳተፋሉ፡፡
አሰልጣኞች የሚወዳደሩት በደረጃ 4 ሲሆን ሰልጣኞች እና አንቀሳቃሾች ደግሞ በደጃ 3 እንደሚመዘኑ ታውቋል፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍6
ቤት በመደራጀት ለመገንባት ለተመዘገባቹ አሰልጣኞች
ነገ መክሰኞ(08/08/16) ከሰዓት 8:00 አዲሱ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
ነገ መክሰኞ(08/08/16) ከሰዓት 8:00 አዲሱ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን።
👍2