ቄድሮን • qedron
449 subscribers
264 photos
32 videos
3 files
497 links
ተሽከርካሪ፡በስልክ፡መከታተያ፡እና፡መቆጣጠሪያ።
Tracking and security for your vehicles.
Download Telegram
የፐርፐዝ ብላክ አካውንቶች ታገዱ።

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንቶች በመንግስት ታግደዋል።

ድርጅቱ አካውንት ሲታገድብኝ ይህ በዓመት ለ3ኛ ጊዜ ነው ብሏል።

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጰያ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ዶክተር ፍስሐ እሸቱ ፥ የድርጅቱ አካውንቶች ለምን እንደታገዱ ምክንያቱን እንደማያውቁት ገልጸዋል።

በአመት ውስጥ ምክንያቱ  ሳይታወቅ ለሶስት ጊዜ አካውንታቸው መታገዱን አመልክተዋል።

ስለ ጉዳዩ " ደብዳቤ እንኳን አልደረሰንም " ብለዋል።

መታደጉን የሰሙትም ከባንኮች እንደሆነ ከነሱ አገኘን ባሉት ደብደቤ ከ ' ፍትህ ሚኒስቴር ' በተጻፈ ደብዳቤ መታገዱን እንደሚልጽ አስረድተዋል።

ከድርጅቱ አካውንቶች በተጨማሪም #የራሳቸው የስራ አስፈጻሚው ዶ/ር ፍስሐ እሸቱ የባንክ አካውንትም ታግዷል።

ዶ/ር ፍስሐ እሸቱ ፥ " አሁን ላይ ለሰራቸኞቻችን ደሞዝ መክፈል ፤ አስፈላጊ ወጪ መሸፈን የማንችልበት ሁኔታ ላይ ነን " ብለዋል።

በአካውንቶች መታገድ ምክንያት የቤት ኪራይ ክፍያ እና የፕሮጀክት ስራዎች መቆማቸውንም አሳውቀዋል።

አሁን በተፈጠረው ችግር የድርጅቱ የቀጣይነት አደጋ ከተጋረጠ ፐርፐዝ ብላክ ተጠያቂ እንደማይሆን " ለባለአክሲዮኖቹ መግለጽ እንፈልጋለን " ብለዋል።

እግዱ ህጋዊ መንገድ ያልተከተለ በመሆኑ መንግሥት መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
👍1