ወዳጆቼ ሴት ዓይነ ጥላ በወንዶች ላይ ስታደር ወንዶችን ለብዙ የሕይወት ቀውስ ትዳርጋቸዋለች፡፡ ሴት ዓይነ ጥላ ወንዶችንም ከማህጸን በመጠናወት፣ከልጅነት አብሮ በማደግ ወስጥ ውስጡን በባሕርይ ተመሳስላ በመኖር ሌላ ማንነት እንዲኖረን ታደርገናለች፡፡ የመጨንገፍ ሕይወትን በውስጣችን እያሳደገ፣ የማናውቃቸውን ነገሮች እየሰገሰገ መፍቻና መቋጠርያ፤ውል አልባ መንገድ ውስጥ ይከተናል፡፡ የመናፍስቱን የጥቃት ሕይወት ካላወቅንበት ከሞቱት በላይ ከሚኖሩት በታች በመሆን እንኳን ሥጋዊ ሕይወታችን መንፈሳዊ ሕይወታችን መዳረሻ እና መጨረሻ የሌለው የልፋት ሕይወት ይሆንብናል፡፡ የጸጋ መንገዱ ይጠፋናል፣የመንከራተትን ሕይወት ያሰርጽብናል፡፡
የዚህ ተከታታይ ትምህርት አንዱ ዓላማ ስለ መናፍስት የመፈተን ብቃት እና ገድላት ለመጻፍ ሳይሆን የውጊያ አውድማቸውን በማወቅ፣መንፈሳዊ የጦር ዕቃ የሆነውን ጾም፣ጸሎት፣ስግደት በመታጠቅ፣ተዋግቶ ከእነሱ እስራት መፈታት እና ነፃ መውጣት ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን አጋንንቱ በእኛ ስንፍናና ባለማወቅ እየተከለለ ያጠቃናል፡፡ የፈተናችንና የመከራችን አምጪ አጋንንቱ ሆኖ ሳለ እግዚአብሔር ነው ወደሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ውስጥ እንገባለን፡፡ ይህ እሳቤያችን ነው መንፈሳዊ ሕይወታችንን እያከበደው በእግዚአብሔር ላይ ተስፋ እንድንቆርጥና አጋንንቱ በእኛ ላይ እንዲፈነጭ ያደረገው፡፡ የሕይወት መረባችን በረኛ አልባ ስለሆነ አጋንንቱ የሚጠልዝብን የፈተና ኳስ፣ወደ ሕይወታችን መሰስ በማለት እየገባ ግብ አስቆጣሪው አጋንንቱ ሆኗል፡፡ በዚህም በመንፈሳዊ የሕይወት ልምምድ ስላላደረግን እኛ ተሸናፊ አጋንንቱ አሸናፊ ሆኗል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ደግሞም በጨዋታ የሚታገል ማንም ቢሆን፣እንደሚገባ አድርጎ ባይታገል የድሉን አክሊል አያገኝም›› ነው ያለው፡፡ /2ኛ ጢሞ 2÷5/ ዛሬ በአጋንንቱ የጨዋታ ብልጫ ተወስዶብን አክሊሉን/ዋንጫውን/ እየተነጠቅን ነው፡፡ በሚገባ ባለመታገላችን ድል እየተደረግን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራእዩ ‹‹ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጽንተህ ያዝ›› ብሎናል፡፡ /ራእ 3÷11/ ወዳጆቼ ብዙ የስኬት፣የገነ የመልካም ሕይወት አክሊላችንን በጸሎት አጽንተን ባለመያዛችን አጋንንት እየወሰደብን፣በራሱ የተንኮል መንገድ እየመራን፣ተስፋችንን የቀን ጨለማ አድርጎብናል፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ በወንዶች ላይ ስታደር ልክ እንደ ሴቶቹ ሁሉ በሴቷ ዓይነ ጥላ ምክንያት ወንዶቹ የራሳቸው ያልሆነ ወይም ተፈጥሮአቸው ያልሆነ መገለጫዎች አሉ፡፡ እነሱም ወንዶቹ ሴት ይፈራሉ፣ሴት ለማናገር ለእጮኝነት ለመጠየቅ ከመናገር አልፈው ይንቀጠቀጣሉ፣ላብ ዝፍቅ ያደርጋቸዋል፣ሲናገሩ ይንተባተባሉ፣ለመናገር አስበው የመጡበት ጉዳይ በፍርሃት ምክንያት ይጠፋቸውና ሌላ ነገር ዘብረቅ አድርገው ይናገራሉ፣ድምጻቸው ቁርጥ የሴት ይመስላል፣ሲናገሩ እንደ ሴት አክት እያደረጉ ነው/ውስጣቸውን ሴት ታደርጋለች/፡፡
የዛሬ አሥራ አምስት ዓመት ጻድቃኔ ማርያም ሴት ዓይነ ጥላ በወንዱ ላይ ስትለፈልፍ ስለ እውነት ነው የምላችሁ በልጁ ድምጽ እጅጉን ነው የደነገጥኩት፡፡ ልጁ ወንድ ሆኖ ሳለ ዓይነ ጥላዋ በሴት ድምጽ ነበር የምትለፈልፈው፡፡ ምናልባት ልጁ እራሱን ሲሆን በሴት ድምጽ ማውራት በፍጹም ላይችል ይችላል፡፡
ሴት ዓይነ ጥላዋ በአንዳንድ ወንዶች ላይ እራስዋን ስትገልጽ ወንዱ ተቅለስላሽ ይሆናል፡፡ አጅጉን ሲበዛ በራሳቸው አይተማመኑም፣ምንም ነገር ከማድረግ ቁጥቦች እና ፈሪዎች ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ላይ ደግሞ ሴት ዓይነ ጥላዋ ከወንድ ጋር ሳይሆን ከሴት ጋር ብቻ እንዲውሉ እንያወሩ ታደርጋለች፣ከሴት ጋር አውርተው አይጠግቡም፣እንደ ሴት ታጋጊጣቸዋለች፣ከሴት ጋር ስለሚውሉ ነገር ሥራቸው ሁሉ እንደ ሴት ይሆናል፡፡ ሴት ዓይነ ጥላ ያለችበት ወንድ ወሬኛ ነው፡፡ ምስጢር አይደብቅም ወሬ በማውራት በማመላለስ የተካነ ነው፡፡
ወዳጆቼ ሴት ዓይነ ጥላዋ ከላይ ባየናቸው መገለጫዎች በወንዶች ላይ የምትታየው የነገን ሕይወታቸው ለማበላሸት እና በሰው ዘንድ እንዲጠሉና በተለይም በሴቶቹ ዘንድ የተናቁና የተጠሉ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው፡፡ ሴት ዓይነ ጥላ ያለባቸው ትዳር ሞት እና ሲኦል መስሎ ይታያቸዋል፡፡ እጅጉን ትዳር ይፈራሉ፡፡ ቢያገቡም ከሚስታቸው ጋር በባሕርይ፣በሩካቤ ሥጋ አይስማሙም አይጣጣሙም፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ ቀናተኛ ስለሆነች ወንዶች ትዳር እንዲይዙ አትሻም፡፡ ይልቁንም መቆራኘትዋን ለማሳወቅ ወንዶችን ሌሊት በሕልም እየመጣች በአምሳለ ሩካቤ ትገናኛቸዋለች፡፡ የሚገርመው ሴት ዓይነ ጥላ ወንዶችን በሕልም ስትገናኛቸው የክፋትዋ ክፈት በእህት፣በአክስት፣በቅርብ በሚያውቋቸው ሴቶች እና ፈጽሞ አይተዋቸው በማያውቋቸው ሴቶች እየተመሰለች ሌሊት በሕልም ትገናኛቸዋለች፡፡ ዓይነ ጥላዋ በሕልም ስትመጣ በተኛንበት የመደበት እና የመፍዘዝ፣የመደንዘዝ ዓለም ውስጥ እንገባለን፡፡ በዚህን ጊዜ እራሳችንን ከአጋንንቷ ቁጥጥር ውጪ ለማድረግ እንቸገራለን፡፡ በስመ አብ ብለን ለማማተብ እንኳ ያቅተናል፡፡ ይህን ማድረግ የሚሳነን ዓይነ ጥላዋ በመጀመርያ እኛን ከመገናኘትዋ በፊት ጥላዋን በመጣል የማደንዘዝ ሥራ ስለምትሠራ ነው፡፡
ምናልባት የዓይነ ጥላዋን ተንኮል ያወቁት ወንዶች ከእሷ ለመላቀቅ ጸበል መጠመቅ ሲጀምሩ በሕልመ ሌሊት እየተመሰለች በመገናኘት ዘራቸውን በማፍሰስ ጸበል እንዳይጠመቁ ትዋጋቸዋለች፡፡ በተለይ ‹‹ነገ አስቀድሳለሁ፣ታቦት አነግሳለሁ፣እጠመቃለሁ›› ካሉ ሌሊት እየፈተነች ታስቀራቸዋለች፡፡ ሌሊት መጥታ በሴት አምሳል ተገናኝታቸው ዘራቸውን ስታስፈስስ ወንዶቹ ከፍተኛ የመደበት እና የራሳቸው ሰውነት የመክበድና የማስጠላት ስሜት ይሰማቸዋል፡፡ የቀን ውሎዋቸው ጤናማና ደስተኛ አይሆንም፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ ወንዶችን በሁለት መልኩ ነው የምትፈትነው፡፡ አንደኛው ውስጣችን አብራን ትኖርና ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ስንገባ ተንኮልዋን ውጊያዋን በገሃድ ትጀምራለች፡፡ ሁለተኛው ዓይነ ጥላዋ ውስጣችን ሳትገባ እንደ አየር አጋንንት በዙርያችን በማንዣበብ በተለይም ሌሊት በሕልማችን በመምጣት በተኛንበት በማነቅ፣በማስጨነቅ እና በመገኛኘት ትፈትነናለች፡፡
ሴት ዓይነ ጥላዋ በውጭ ሆና ስትፈትነን ትልቁ ሥራዋ መገርገር ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ወንድ ለትዳር የምትሆነውን እጮኛ ይዛለሁ ብሎ በማሰብ ልቡ የወደዳትን፣ ሰውነቱ የደነገጠባትን ሴት ለእጮኝነት ቢጠይቃት ዓይነ ጥላዋ በሴትዋ ላይ በመሆን ወንዱን ለሴትዋ ገልብጣ በማሳየት እንድትጠላው ታደርጋለች፡፡ ትሁቱን ወንድ ኃይለኛ፣ትግስተኛው ነገረኛ፣መልከኛውን የማያምር፣ሩሕሩሁን ጨካኝ፣ታማኙን ሴት አውል አድርጋ በማሳየት፣በማሳሰብ በሴት መጠላትን ታመጣበታለች፡፡ አንዳንዶቹንማ ሴት የተባሉ እንዳይቀርቡት በሴቶች ዘንድ ያለ ምንም ምክንያት እንዲጠላ ታደርጋለች፡፡ ሌሎቹን ደግሞ በፍጹም ከሴቶች ጋር አታግባባውም፡፡ ሴቶቹ እንኳን ሰብዕናውን ንግግሩን እንዲጠሉ፣ እንዱጨክኑበት ታደርጋለች፡፡
ዛሬ የምናያቸው አንዳንድ ወንዶች ወይሥጋን ከትዳር አልያም ከምነና ሳይሆኑ ትዳር እና ሴት በመጥላት የሚኖሩት ወደው አይደለም፡፡ በሴት ዓይነ ጥላ ተይዘው እንጂ፡፡ ቤተሰብ ‹‹ኸረ አግባ›› ሲሉት ትዳርን እንደ እስር ቤት በማሰብ ይፈራሉ፡፡ አጋንንቷ ስለምትቀና ትዳር አታሲዛቸውም፡፡ ትዳር ቢይዙም በስንፈተ ሩካቤ እየተመሰለች ሩካቤን ትከለክላለች፡፡ በዚህም ታፋታለች፡፡
ሴት ዓይነ ጥላዋ ወንዶች ሴት እንዲጠሉ ስለምታደርጋቸው የተቃራኒ ጾታ ነገርን አታሳስባቸውም፡፡ አንዳንዶችን ሴት ዓይነ ጥላዋ ግለ ወሲብን በማጠናወት ግለ ወሲብን እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕጋዊ ሩካቤን እ
የዚህ ተከታታይ ትምህርት አንዱ ዓላማ ስለ መናፍስት የመፈተን ብቃት እና ገድላት ለመጻፍ ሳይሆን የውጊያ አውድማቸውን በማወቅ፣መንፈሳዊ የጦር ዕቃ የሆነውን ጾም፣ጸሎት፣ስግደት በመታጠቅ፣ተዋግቶ ከእነሱ እስራት መፈታት እና ነፃ መውጣት ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን አጋንንቱ በእኛ ስንፍናና ባለማወቅ እየተከለለ ያጠቃናል፡፡ የፈተናችንና የመከራችን አምጪ አጋንንቱ ሆኖ ሳለ እግዚአብሔር ነው ወደሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ውስጥ እንገባለን፡፡ ይህ እሳቤያችን ነው መንፈሳዊ ሕይወታችንን እያከበደው በእግዚአብሔር ላይ ተስፋ እንድንቆርጥና አጋንንቱ በእኛ ላይ እንዲፈነጭ ያደረገው፡፡ የሕይወት መረባችን በረኛ አልባ ስለሆነ አጋንንቱ የሚጠልዝብን የፈተና ኳስ፣ወደ ሕይወታችን መሰስ በማለት እየገባ ግብ አስቆጣሪው አጋንንቱ ሆኗል፡፡ በዚህም በመንፈሳዊ የሕይወት ልምምድ ስላላደረግን እኛ ተሸናፊ አጋንንቱ አሸናፊ ሆኗል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ደግሞም በጨዋታ የሚታገል ማንም ቢሆን፣እንደሚገባ አድርጎ ባይታገል የድሉን አክሊል አያገኝም›› ነው ያለው፡፡ /2ኛ ጢሞ 2÷5/ ዛሬ በአጋንንቱ የጨዋታ ብልጫ ተወስዶብን አክሊሉን/ዋንጫውን/ እየተነጠቅን ነው፡፡ በሚገባ ባለመታገላችን ድል እየተደረግን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራእዩ ‹‹ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጽንተህ ያዝ›› ብሎናል፡፡ /ራእ 3÷11/ ወዳጆቼ ብዙ የስኬት፣የገነ የመልካም ሕይወት አክሊላችንን በጸሎት አጽንተን ባለመያዛችን አጋንንት እየወሰደብን፣በራሱ የተንኮል መንገድ እየመራን፣ተስፋችንን የቀን ጨለማ አድርጎብናል፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ በወንዶች ላይ ስታደር ልክ እንደ ሴቶቹ ሁሉ በሴቷ ዓይነ ጥላ ምክንያት ወንዶቹ የራሳቸው ያልሆነ ወይም ተፈጥሮአቸው ያልሆነ መገለጫዎች አሉ፡፡ እነሱም ወንዶቹ ሴት ይፈራሉ፣ሴት ለማናገር ለእጮኝነት ለመጠየቅ ከመናገር አልፈው ይንቀጠቀጣሉ፣ላብ ዝፍቅ ያደርጋቸዋል፣ሲናገሩ ይንተባተባሉ፣ለመናገር አስበው የመጡበት ጉዳይ በፍርሃት ምክንያት ይጠፋቸውና ሌላ ነገር ዘብረቅ አድርገው ይናገራሉ፣ድምጻቸው ቁርጥ የሴት ይመስላል፣ሲናገሩ እንደ ሴት አክት እያደረጉ ነው/ውስጣቸውን ሴት ታደርጋለች/፡፡
የዛሬ አሥራ አምስት ዓመት ጻድቃኔ ማርያም ሴት ዓይነ ጥላ በወንዱ ላይ ስትለፈልፍ ስለ እውነት ነው የምላችሁ በልጁ ድምጽ እጅጉን ነው የደነገጥኩት፡፡ ልጁ ወንድ ሆኖ ሳለ ዓይነ ጥላዋ በሴት ድምጽ ነበር የምትለፈልፈው፡፡ ምናልባት ልጁ እራሱን ሲሆን በሴት ድምጽ ማውራት በፍጹም ላይችል ይችላል፡፡
ሴት ዓይነ ጥላዋ በአንዳንድ ወንዶች ላይ እራስዋን ስትገልጽ ወንዱ ተቅለስላሽ ይሆናል፡፡ አጅጉን ሲበዛ በራሳቸው አይተማመኑም፣ምንም ነገር ከማድረግ ቁጥቦች እና ፈሪዎች ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ላይ ደግሞ ሴት ዓይነ ጥላዋ ከወንድ ጋር ሳይሆን ከሴት ጋር ብቻ እንዲውሉ እንያወሩ ታደርጋለች፣ከሴት ጋር አውርተው አይጠግቡም፣እንደ ሴት ታጋጊጣቸዋለች፣ከሴት ጋር ስለሚውሉ ነገር ሥራቸው ሁሉ እንደ ሴት ይሆናል፡፡ ሴት ዓይነ ጥላ ያለችበት ወንድ ወሬኛ ነው፡፡ ምስጢር አይደብቅም ወሬ በማውራት በማመላለስ የተካነ ነው፡፡
ወዳጆቼ ሴት ዓይነ ጥላዋ ከላይ ባየናቸው መገለጫዎች በወንዶች ላይ የምትታየው የነገን ሕይወታቸው ለማበላሸት እና በሰው ዘንድ እንዲጠሉና በተለይም በሴቶቹ ዘንድ የተናቁና የተጠሉ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው፡፡ ሴት ዓይነ ጥላ ያለባቸው ትዳር ሞት እና ሲኦል መስሎ ይታያቸዋል፡፡ እጅጉን ትዳር ይፈራሉ፡፡ ቢያገቡም ከሚስታቸው ጋር በባሕርይ፣በሩካቤ ሥጋ አይስማሙም አይጣጣሙም፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ ቀናተኛ ስለሆነች ወንዶች ትዳር እንዲይዙ አትሻም፡፡ ይልቁንም መቆራኘትዋን ለማሳወቅ ወንዶችን ሌሊት በሕልም እየመጣች በአምሳለ ሩካቤ ትገናኛቸዋለች፡፡ የሚገርመው ሴት ዓይነ ጥላ ወንዶችን በሕልም ስትገናኛቸው የክፋትዋ ክፈት በእህት፣በአክስት፣በቅርብ በሚያውቋቸው ሴቶች እና ፈጽሞ አይተዋቸው በማያውቋቸው ሴቶች እየተመሰለች ሌሊት በሕልም ትገናኛቸዋለች፡፡ ዓይነ ጥላዋ በሕልም ስትመጣ በተኛንበት የመደበት እና የመፍዘዝ፣የመደንዘዝ ዓለም ውስጥ እንገባለን፡፡ በዚህን ጊዜ እራሳችንን ከአጋንንቷ ቁጥጥር ውጪ ለማድረግ እንቸገራለን፡፡ በስመ አብ ብለን ለማማተብ እንኳ ያቅተናል፡፡ ይህን ማድረግ የሚሳነን ዓይነ ጥላዋ በመጀመርያ እኛን ከመገናኘትዋ በፊት ጥላዋን በመጣል የማደንዘዝ ሥራ ስለምትሠራ ነው፡፡
ምናልባት የዓይነ ጥላዋን ተንኮል ያወቁት ወንዶች ከእሷ ለመላቀቅ ጸበል መጠመቅ ሲጀምሩ በሕልመ ሌሊት እየተመሰለች በመገናኘት ዘራቸውን በማፍሰስ ጸበል እንዳይጠመቁ ትዋጋቸዋለች፡፡ በተለይ ‹‹ነገ አስቀድሳለሁ፣ታቦት አነግሳለሁ፣እጠመቃለሁ›› ካሉ ሌሊት እየፈተነች ታስቀራቸዋለች፡፡ ሌሊት መጥታ በሴት አምሳል ተገናኝታቸው ዘራቸውን ስታስፈስስ ወንዶቹ ከፍተኛ የመደበት እና የራሳቸው ሰውነት የመክበድና የማስጠላት ስሜት ይሰማቸዋል፡፡ የቀን ውሎዋቸው ጤናማና ደስተኛ አይሆንም፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ ወንዶችን በሁለት መልኩ ነው የምትፈትነው፡፡ አንደኛው ውስጣችን አብራን ትኖርና ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ስንገባ ተንኮልዋን ውጊያዋን በገሃድ ትጀምራለች፡፡ ሁለተኛው ዓይነ ጥላዋ ውስጣችን ሳትገባ እንደ አየር አጋንንት በዙርያችን በማንዣበብ በተለይም ሌሊት በሕልማችን በመምጣት በተኛንበት በማነቅ፣በማስጨነቅ እና በመገኛኘት ትፈትነናለች፡፡
ሴት ዓይነ ጥላዋ በውጭ ሆና ስትፈትነን ትልቁ ሥራዋ መገርገር ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ወንድ ለትዳር የምትሆነውን እጮኛ ይዛለሁ ብሎ በማሰብ ልቡ የወደዳትን፣ ሰውነቱ የደነገጠባትን ሴት ለእጮኝነት ቢጠይቃት ዓይነ ጥላዋ በሴትዋ ላይ በመሆን ወንዱን ለሴትዋ ገልብጣ በማሳየት እንድትጠላው ታደርጋለች፡፡ ትሁቱን ወንድ ኃይለኛ፣ትግስተኛው ነገረኛ፣መልከኛውን የማያምር፣ሩሕሩሁን ጨካኝ፣ታማኙን ሴት አውል አድርጋ በማሳየት፣በማሳሰብ በሴት መጠላትን ታመጣበታለች፡፡ አንዳንዶቹንማ ሴት የተባሉ እንዳይቀርቡት በሴቶች ዘንድ ያለ ምንም ምክንያት እንዲጠላ ታደርጋለች፡፡ ሌሎቹን ደግሞ በፍጹም ከሴቶች ጋር አታግባባውም፡፡ ሴቶቹ እንኳን ሰብዕናውን ንግግሩን እንዲጠሉ፣ እንዱጨክኑበት ታደርጋለች፡፡
ዛሬ የምናያቸው አንዳንድ ወንዶች ወይሥጋን ከትዳር አልያም ከምነና ሳይሆኑ ትዳር እና ሴት በመጥላት የሚኖሩት ወደው አይደለም፡፡ በሴት ዓይነ ጥላ ተይዘው እንጂ፡፡ ቤተሰብ ‹‹ኸረ አግባ›› ሲሉት ትዳርን እንደ እስር ቤት በማሰብ ይፈራሉ፡፡ አጋንንቷ ስለምትቀና ትዳር አታሲዛቸውም፡፡ ትዳር ቢይዙም በስንፈተ ሩካቤ እየተመሰለች ሩካቤን ትከለክላለች፡፡ በዚህም ታፋታለች፡፡
ሴት ዓይነ ጥላዋ ወንዶች ሴት እንዲጠሉ ስለምታደርጋቸው የተቃራኒ ጾታ ነገርን አታሳስባቸውም፡፡ አንዳንዶችን ሴት ዓይነ ጥላዋ ግለ ወሲብን በማጠናወት ግለ ወሲብን እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕጋዊ ሩካቤን እ
ንዲጠሉ ታደርጋቸዋለች፡፡ አጋንንቷ የሚያውቃትን ሴት በሕሊናው በማሳየት፣ በማሳሰብ ግለ ወሲብን የዘውትር ተግባሩ ታደርግባቸዋለች፡፡ በሴት ዓይነ ጥላ ግለ ወሲብን የለመዱ ወንዶች ግለ ወሲብን ለመተው እጅጉን ይቸገራሉ፡፡ ይህም የሚሆነው አጋንንቷ ከሥጋ፣ከደም ጋር በመዋሃድ የቁጥጥር የበላይነት ስለሚኖራት ነው፡፡
የሴት ዓይነ ጥላ ዋና ዓላማዋ ከቃራኒ ጾታ ጋር ፍቅርን ትዳርን መከልከል ነው፡፡ አጋንንቷ ሴተ ጠል ስለሆነች ወንዶችን ለግብረ ሰዶም ትጋባዛለች፡፡ ግብረ ሰዶም የሚፈጽሙ ወንዶች አንዱ ችግራቸው በሴት ዓይነ ጥላ ስለሚጠቁ ነው፡፡ ከተቃራኒ ጾታ ጋር ሩካቤ ሥጋን ለመፈጸም መሞከር ቀርቶ አያስቡትም፡፡ ይህ አጋንንቱ ተጠቂውን ከተፈጥሮ መንገድ አስፈንጦ፣ከእግዚአብሔር አቆራርጦ ለማኖር ይጠቀምበታል፡፡ ይህን ያላወቀ ትውልድ በአጋንንት የሰዶም ርዝራዥ ይሆናል፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ በወንዶች ላይ ስታድር ሴቶችን ስለምትጠላ ወንዶቹ ከአንድ ሴት ጋር ረግተው እንዲኖሩ አታደርግም፡፡ሰውነት እጮኛና ትዳርን በማሰልቸት ወደ ሌላ ሴት እንዲያማትሩና እንዲሄዱ ታደርጋቸዋለች፡፡ ነገራቸውም ላይጣፍጡ ወጡ፣ ጉልቻ ቢለዋውጡ ይሆናል፡፡ የተሻለ ሕይወት ላያገኙ ታንከራትታቸዋለች፡፡
ጾም ጾሎት ስግደት የማያውቅ የአጋንት ወደብ ነው የሚሆነው፡፡ አጋንንቱ የሚፈልገውን የተንኮል መልህቅ ሁሉ በሰውዬው ላይ በማራገፍ፣መልሶ የማያገኘውን ውድ ሕይወት በማጨናገፍ፣ባዶ ሰው ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ይህችን ክፉ ዓይነ ጥላ ለመዋጋት እና ከቁርኝቷ ለመለያየት መታከት መሰልቸት የሌለበት ጸሎት፣አቅምን ያገናዘበ ግን ያልተቋረጠ ስግደት፣ፈተናና መሰልቸት ቢበዛውም ያልተመቸን በሚመቸን ሰዓት፣የሚመቸን አዘውትረን ጸበል በመጠመቅ ልንዋጋት እና ከእኛ ልናርቃት ይገባል፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የበረታችሁ ደግሞ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል ሰውነታችሁን የእሷ ሳይሆን የእሳተ መለኮት ማደርያ በማድረግ መቀመጫ በማሳጣት ማራቅ ይቻላል፡፡ ግን ይህን ሁል ለማድረግ ቆራጥነት እና ዓላማ ብሎ መነሳት ያስፈልጋል፡፡ ለበረታ ላልታከተ ሰው ሠልፉ የጌዴዎን ድሉ የእግዚአብሔር ነው፡፡
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ?›› ት.ኢሳ 53÷8
የሴት ዓይነ ጥላ ዋና ዓላማዋ ከቃራኒ ጾታ ጋር ፍቅርን ትዳርን መከልከል ነው፡፡ አጋንንቷ ሴተ ጠል ስለሆነች ወንዶችን ለግብረ ሰዶም ትጋባዛለች፡፡ ግብረ ሰዶም የሚፈጽሙ ወንዶች አንዱ ችግራቸው በሴት ዓይነ ጥላ ስለሚጠቁ ነው፡፡ ከተቃራኒ ጾታ ጋር ሩካቤ ሥጋን ለመፈጸም መሞከር ቀርቶ አያስቡትም፡፡ ይህ አጋንንቱ ተጠቂውን ከተፈጥሮ መንገድ አስፈንጦ፣ከእግዚአብሔር አቆራርጦ ለማኖር ይጠቀምበታል፡፡ ይህን ያላወቀ ትውልድ በአጋንንት የሰዶም ርዝራዥ ይሆናል፡፡
ሴት ዓይነ ጥላ በወንዶች ላይ ስታድር ሴቶችን ስለምትጠላ ወንዶቹ ከአንድ ሴት ጋር ረግተው እንዲኖሩ አታደርግም፡፡ሰውነት እጮኛና ትዳርን በማሰልቸት ወደ ሌላ ሴት እንዲያማትሩና እንዲሄዱ ታደርጋቸዋለች፡፡ ነገራቸውም ላይጣፍጡ ወጡ፣ ጉልቻ ቢለዋውጡ ይሆናል፡፡ የተሻለ ሕይወት ላያገኙ ታንከራትታቸዋለች፡፡
ጾም ጾሎት ስግደት የማያውቅ የአጋንት ወደብ ነው የሚሆነው፡፡ አጋንንቱ የሚፈልገውን የተንኮል መልህቅ ሁሉ በሰውዬው ላይ በማራገፍ፣መልሶ የማያገኘውን ውድ ሕይወት በማጨናገፍ፣ባዶ ሰው ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ይህችን ክፉ ዓይነ ጥላ ለመዋጋት እና ከቁርኝቷ ለመለያየት መታከት መሰልቸት የሌለበት ጸሎት፣አቅምን ያገናዘበ ግን ያልተቋረጠ ስግደት፣ፈተናና መሰልቸት ቢበዛውም ያልተመቸን በሚመቸን ሰዓት፣የሚመቸን አዘውትረን ጸበል በመጠመቅ ልንዋጋት እና ከእኛ ልናርቃት ይገባል፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የበረታችሁ ደግሞ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል ሰውነታችሁን የእሷ ሳይሆን የእሳተ መለኮት ማደርያ በማድረግ መቀመጫ በማሳጣት ማራቅ ይቻላል፡፡ ግን ይህን ሁል ለማድረግ ቆራጥነት እና ዓላማ ብሎ መነሳት ያስፈልጋል፡፡ ለበረታ ላልታከተ ሰው ሠልፉ የጌዴዎን ድሉ የእግዚአብሔር ነው፡፡
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ?›› ት.ኢሳ 53÷8
ክፍል አስራ አንድ
ወንድ ዓይነ ጥላ በሴቶች ላይ
/ብዙ እህቶቻችንን የሚያሰቃይ አደገኛ እና ቀኒታው ዓይነ ጥላ/
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ወዳጆቼ የዓይነ ጥላ መንፈስ ምን ያህል በሕይወታችን ጣልቃ በመግባት ለምስቅልቅል ሕይወት እንደሚዳርገን፣በነገሮች ሁሉ እንቅፋት እንደሚሆንብን በተለይም በእጮኝነት እና በትዳር ላይ የጭቃ ውስጥ እሾክ በመሆን ውስጥ ወስጡን በስውር በመውጋት፣የፈተናን ገፈት እንድንቀምስ እንደሚያደርገን በስፋት አይተናል፡፡
ሥጋ ለበስ ወይም ልቡሳነ ሥጋ ከሚባሉት አጋንንቶች ውጪ አጋንንት ጾታ የለውም፡፡ ግን ጾታን ተመስሎ ይጠናወተናል፡፡ ወንዱን በሴት፣ሴቱን በወንድ እየተመሰለ ይፈትናል፡፡ ሥጋ ለበስ አጋንንት ስለሚባሉት ተጋብተው ስለሚዋለዱት፣ከሰው ጋር ግንኙነት ስለሚያደርጉት፤እንደ ሰው ኖረው ስለሚሞቱት፣ሥጋ ለበስ አጋንንት በሌላ ክፍል በሰፊው ይዤላችሁ እቀርባለሁ፡፡ እነዚህ አጋንንቶች ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር እስከመተኛት፤ሴቶቹ ሥጋ ለበስ አጋንንቶች ከወንዶች ጋር እስከመተኛት ይደረሳሉ፡፡ ከልቡሳነ ሥጋ አጋንንት ጋር ሩካቤ የፈጸመ ሰው ይሴስናል፡፡ እንዴት ሴሰኛ እንደሚያደርጉት፣ከሥጋ ለበስ አጋንንት ጋር የተገኛኙ ሰዎች ከሰው ጋር ግንኙነት ሲያደርጉ የዝሙት መንፈስ እንዴት እንደሚሰርጽባቸው በቅርቡ በዝርዝር እናያለን/
ወንድ ዓይነ ጥላ ሴቶች እህቶቻችንን ላይ ከማህጸን፣ከጊዜ በኃላ በመጠናወት አብሮ ያድጋል፡፡ አብሮን ሲያድግ ዓይነ ጥላው በራሱ መንገድ ይቃኘናል፡፡ ይህ ደግሞ ባሕርያችንና አንዳንድ የራሳችን የሆነ መገለጫዎች ለእኛ፣ለቤተሰባችን፣ለሚያውቁን ሰዎች የራሳችን ጠባይ ይመስላቸዋል፡፡ በዚህ መደበቅና መሸፈን ውስጥ ያለው ዓይነ ጥላ በጊዜ ሂደት በእኛ ላይ እራሱን መግለጥ ይጀምራል፡፡ ያኔ ነው ለራሳችንና ለሰዎች ግራ የምንሆነው፡፡
ወዳጆቼ ለምሳሌ አንድ ሴት ወንድ ዓይነ ጥላ ሲኖርባት እነዚህን መገለጫዎች በእሷ ላይ ይታያሉ፡፡ እጮኛና ትዳር ትጠላለች፣እጮኛ ብትይዝም ወደ ትዳር በትገባም ብዙም አትቆይም፣እንደ ወንድ አክት ታደርጋለች፣ጮክ ብላ ትናገራለች፣ሌሊት የማታውቀው ሰው እየመጣ ይገናኛታል፣እንደ ወንድ ትደባደባለች፣ሰው የሚላትን በፍጹም አትሰማም፣እጅጉን ሲበዛ ኃይለኛ ነች፣ድምጽዋ የወንድ ይመስላል፣አነጋገርዋ አካሄድዋ፣አበላልዋ እንደ ወንድ ነው፣ውሎዋ ከወንድ ጋር ነው፣ከሴቶች ይልቅ ከወንዶች ጋር ነው የምትግባባው፣ሴት ትጠላለች፣ለጠብ የቀረበች ናት፣እርቅ አትወድም፣ይቅርታ አታውቅም/አታደርግም፣ቂመኛ እና በቀለኛ ናት፣መጠጥ ትጠጣለች ትሰክራለች፣ከወንድ ጋር ሩካቤ ብትፈጽምም አትደሰትም፣ወንድ ትንቃለች፣የሚበልጧትን አትወድም፣በጣም ቅናተኛ ናት፣ሰው ማክበር እና ማድነቅ አትወድም፣ማጥላላት፣ማማት ሥራዋ ነው፣እፍረት የለባትም፣ይሉኝታ አታውቅም፡፡
ተወዳጆች ሆይ ዓይነ ጥላው ሴቶችን በወንድ አምሳል ሲጠናወታቸው ከላይ የዘረዘርኳቸው ባሕርያት መገለጫቸው ነው፡፡ ይህም ዓይነ ጥላው በሰውና በማሕበረሰብ ውስጥ እንዲጠሉ እንዳይፈለጉ ለማድረግ የሚጠቀምበት ስልት ነው፡፡ ለትዳር ሲፈለጉ በሰዎች ዘንድ ከኃይለኝነታው የተነሳ ይፈራሉ፡፡ ለትዳር ቢጠየቁም ‹‹እሷን ልታገባ›› እየተባሉ ከትዳር ዓለም ይገለላሉ፡፡
ዓይነ ጥላው የራሳቸው በመሰለ ጠባይ ተዋህዷቸው ስለሚኖር ሰው አይረዳቸውም፡፡ ዓይነ ጥላው በራሱ የተንኮል ባሕርይ እንዲጠሉ ያደርጋቸዋል፡፡ የሚያሳዝነው ወንድ ዓይነ ጥላ ያለባቸው እህቶቻችን ምናልባት ትዳር ቢይዙም ከባላቸው ጋር አይስማሙም፡፡ ይጨቃጨቃሉ፡፡ ዓይነ ጥላቸው በወንድ አምሳል ስለገባ ሩካቤ ያስጠላቸዋል፡፡ ግን በተኙበት የሚገናኛቸው አለ፡፡
በሴቶች ላይ በወንድ አምሳል ዓይነ ጥላው ሲያድርባቸው ነውጠኛ ነው የሚሆኑት፡፡ እነሱ ያሉበት ክርክር፣ጠብ መብረጃ የለውም፡፡ ዓይነ ጥላው በቅጽበት ስለሚቀይራቸው የሚናገሩትን፣የሚያደርጉትን አያውቁም ቢያውቁም እራሳቸውን መቆጣጠር አይችሉም፡፡ በዚህም ለሰው አስቸጋሪ ናቸው፡፡
ሴቶች ላይ ወንድ ዓይነ ጥላው ሌሊት በተኙበት እየመጣ በገሃድ በሚመስል መልኩ ይገናኛቸዋል፡፡ ሲገናኛቸው አንዳንዱን በማስገደድ በሚመስል መልኩ ነው፡፡ ሌሎችን ደግሞ አስለምዷቸው መደበኛ እስኪመስል ድረስ ነው፡፡ ግን በየትኛውም መልኩ ይሁን ወንድ ዓይነ ጥላ ሴቶችን በተኙበት ሲገናኛቸው ጠዋት ከእንቅልፋቸው ሲነሱ የመደበት፣እራስ ምታት ይሰማቸዋል፡፡ ቀኑን ሙሉ አስጠልቷቸው ነው የሚውሉት፡፡
እዚህ ላይ አንዳ ለረጅም ዓመታት ስለማውቃች ወዳጄ ላጫውታችሁ፡፡ እንጦጦ ማርያም የማውቃት ልጅ አለች፡፡ ይቺ ልጅ ይህ በጣም መልከኛ ናት፡፡ ያያት ወንድ በቀላሉ ይሰናከልባታል፡፡ ከመንፈሳዊ ሰብእናዊ በተጨማሪ በመልኳና በቁመናዋ ለትዳር የማይጠይቃት ሰው የለም፡፡ እኔም ለምን በቤተክርስትያን ሥርዓት እንደማታገባ ስጠይቃት አስገራመ ነገር ነገረችኝ፡፡
እንጦጦ ማርያም ለጸበል የመጣቸው ሌሊት እየመጣ በሥርዓት እየተገናኛት በሚሔደው ሰው መሰል አጋንንት ነው፡፡ አጋንንቱ እንደ ተኛች ይመጣል፡፡ ሲመጣ አንዳች የሚከብድ እና ለመነሳት ኃይል እስክታጣ ሰውነቷን ማዘዝ ወደማትችልበት ሁኔታ ውስጥ ትገባች፡፡ አጋንንቱን በገሃድ በሚመስል ሩካቤ ተገናኝቷት ይሄዳል፡፡ ይህ ለዘመናት የለመደችው ግን ለሰው ያላማከረችው ብታማክርም ከሰው መፍትሔ አላገኝም ብላ የምትሰቃይበት ነገር ነው፡፡
ልጅቷ አንድ ወንድ ለጓደኝነት ከጠየቃት የዛን ቀን ሌሊት ስትሰቃይ ታድራለች፡፡ አንድ ወንድ ለጋብቻ እንደሚፈልጋት ከነገራች አጋንንቱ ሌሊት መጥቶ ‹‹ባልሽ እኔነ ነኝ እኔን የት ትተሸ ነው የምታገቢው›› እያለ ያስፈራራታል ይገናኛታል፡፡ በዚህም የወንድ ጓደኛ ከያዘች ‹‹ያስጠሉኛል፣ የወደድኩትን ሰው አግኝቼ ለማውራ ጭንቅ ይለኛል፣ሳያቸው ደስ አይሉኝም፣ይሰለቹኛል›› ትለኛለች፡፡
ቤተሰብ የልጅቷን ችግር ሊረዳላት አልቻለም፡፡ ይቺ ልጅ ሰው በማያውቅላት፣በማይረዳት ችግር ብዙ ስትፈተን ከርማ ከአምስት ዓመት ከጸበል፣ከጾም፣ከጸሎት ትግል በኃላ በራስዋ ጥረት እና በእመቤታችን ጸሎት ከዚህ ችግር ተላቃ በአሁን ጊዜ አግብታለች፡፡ ስለ እውነት ነው የምላችሁ ከችግሩ ተላቃ ጓደኛ እንደ ያዘች እና በቅርቡም ሊጋቡ መሆኑን የነገረችኝ ቀን ምን ያህል እንደተደሰትኩ እኔ ነኝ የማውቀው፡፡ ሌሊት እየመጣ የሚገናኝትም ወንድ ዓይነ ጥላ ድራሹ ጠፍቶላት አሁን ከባልዋ ጋር በሰላም መኖርዋ የእሷ ብቻ ሳይሆን የእኔም ደስታ ነበር፡፡ ወንድ ዓይነ ጥላ ስለማያፍር ባል እና ሚስት ተኝተው ሚስትን ተገናኝቷት ሊሔድ ይችላል፡፡
ወዳጆቼ ይህ ሌሊት እየመጣ ሴቶችን የሚገናኝ ዓይነ ጥላ ዋናው ዓላማ ሴቶችን ትዳር እንዳይዙ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም እንዲመቸው ለትዳር የሚመጡትን ወንዶች ሁሉ ምክንያት በሚመስል ነገሮች እንዲጠሉዋቸው ያደርጋል፡፡ ሴቶቹም የራሳቸው ሐሳብና ፍላጎት እየመሰላቸው በወንዱ ላይ አቃቂር እያወጡ ይንቃሉ ይጠላሉ፡፡
ወንድ ዓይነ ጥላ ያለባቸው ሴቶች አንዳንዶቹ የሩካቤ ሥጋ ፍላጎት እና ጉጉት በፍጹም የለባቸውም፡፡ ሩካቤን እንኳን ሊፈጽሙት ስለ ሩካቤ ሲወራ ያስጠላቸዋል፡፡ ቤተሰብም ልጃቸው ከወንድ በመራቅዋ፣ትዳር ባለመያዝዋ እንደ ጨዋ ያይዋታል፡፡ ግን የትዳር ሕይወትዋን ዓይነ ጥላው
ወንድ ዓይነ ጥላ በሴቶች ላይ
/ብዙ እህቶቻችንን የሚያሰቃይ አደገኛ እና ቀኒታው ዓይነ ጥላ/
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ወዳጆቼ የዓይነ ጥላ መንፈስ ምን ያህል በሕይወታችን ጣልቃ በመግባት ለምስቅልቅል ሕይወት እንደሚዳርገን፣በነገሮች ሁሉ እንቅፋት እንደሚሆንብን በተለይም በእጮኝነት እና በትዳር ላይ የጭቃ ውስጥ እሾክ በመሆን ውስጥ ወስጡን በስውር በመውጋት፣የፈተናን ገፈት እንድንቀምስ እንደሚያደርገን በስፋት አይተናል፡፡
ሥጋ ለበስ ወይም ልቡሳነ ሥጋ ከሚባሉት አጋንንቶች ውጪ አጋንንት ጾታ የለውም፡፡ ግን ጾታን ተመስሎ ይጠናወተናል፡፡ ወንዱን በሴት፣ሴቱን በወንድ እየተመሰለ ይፈትናል፡፡ ሥጋ ለበስ አጋንንት ስለሚባሉት ተጋብተው ስለሚዋለዱት፣ከሰው ጋር ግንኙነት ስለሚያደርጉት፤እንደ ሰው ኖረው ስለሚሞቱት፣ሥጋ ለበስ አጋንንት በሌላ ክፍል በሰፊው ይዤላችሁ እቀርባለሁ፡፡ እነዚህ አጋንንቶች ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር እስከመተኛት፤ሴቶቹ ሥጋ ለበስ አጋንንቶች ከወንዶች ጋር እስከመተኛት ይደረሳሉ፡፡ ከልቡሳነ ሥጋ አጋንንት ጋር ሩካቤ የፈጸመ ሰው ይሴስናል፡፡ እንዴት ሴሰኛ እንደሚያደርጉት፣ከሥጋ ለበስ አጋንንት ጋር የተገኛኙ ሰዎች ከሰው ጋር ግንኙነት ሲያደርጉ የዝሙት መንፈስ እንዴት እንደሚሰርጽባቸው በቅርቡ በዝርዝር እናያለን/
ወንድ ዓይነ ጥላ ሴቶች እህቶቻችንን ላይ ከማህጸን፣ከጊዜ በኃላ በመጠናወት አብሮ ያድጋል፡፡ አብሮን ሲያድግ ዓይነ ጥላው በራሱ መንገድ ይቃኘናል፡፡ ይህ ደግሞ ባሕርያችንና አንዳንድ የራሳችን የሆነ መገለጫዎች ለእኛ፣ለቤተሰባችን፣ለሚያውቁን ሰዎች የራሳችን ጠባይ ይመስላቸዋል፡፡ በዚህ መደበቅና መሸፈን ውስጥ ያለው ዓይነ ጥላ በጊዜ ሂደት በእኛ ላይ እራሱን መግለጥ ይጀምራል፡፡ ያኔ ነው ለራሳችንና ለሰዎች ግራ የምንሆነው፡፡
ወዳጆቼ ለምሳሌ አንድ ሴት ወንድ ዓይነ ጥላ ሲኖርባት እነዚህን መገለጫዎች በእሷ ላይ ይታያሉ፡፡ እጮኛና ትዳር ትጠላለች፣እጮኛ ብትይዝም ወደ ትዳር በትገባም ብዙም አትቆይም፣እንደ ወንድ አክት ታደርጋለች፣ጮክ ብላ ትናገራለች፣ሌሊት የማታውቀው ሰው እየመጣ ይገናኛታል፣እንደ ወንድ ትደባደባለች፣ሰው የሚላትን በፍጹም አትሰማም፣እጅጉን ሲበዛ ኃይለኛ ነች፣ድምጽዋ የወንድ ይመስላል፣አነጋገርዋ አካሄድዋ፣አበላልዋ እንደ ወንድ ነው፣ውሎዋ ከወንድ ጋር ነው፣ከሴቶች ይልቅ ከወንዶች ጋር ነው የምትግባባው፣ሴት ትጠላለች፣ለጠብ የቀረበች ናት፣እርቅ አትወድም፣ይቅርታ አታውቅም/አታደርግም፣ቂመኛ እና በቀለኛ ናት፣መጠጥ ትጠጣለች ትሰክራለች፣ከወንድ ጋር ሩካቤ ብትፈጽምም አትደሰትም፣ወንድ ትንቃለች፣የሚበልጧትን አትወድም፣በጣም ቅናተኛ ናት፣ሰው ማክበር እና ማድነቅ አትወድም፣ማጥላላት፣ማማት ሥራዋ ነው፣እፍረት የለባትም፣ይሉኝታ አታውቅም፡፡
ተወዳጆች ሆይ ዓይነ ጥላው ሴቶችን በወንድ አምሳል ሲጠናወታቸው ከላይ የዘረዘርኳቸው ባሕርያት መገለጫቸው ነው፡፡ ይህም ዓይነ ጥላው በሰውና በማሕበረሰብ ውስጥ እንዲጠሉ እንዳይፈለጉ ለማድረግ የሚጠቀምበት ስልት ነው፡፡ ለትዳር ሲፈለጉ በሰዎች ዘንድ ከኃይለኝነታው የተነሳ ይፈራሉ፡፡ ለትዳር ቢጠየቁም ‹‹እሷን ልታገባ›› እየተባሉ ከትዳር ዓለም ይገለላሉ፡፡
ዓይነ ጥላው የራሳቸው በመሰለ ጠባይ ተዋህዷቸው ስለሚኖር ሰው አይረዳቸውም፡፡ ዓይነ ጥላው በራሱ የተንኮል ባሕርይ እንዲጠሉ ያደርጋቸዋል፡፡ የሚያሳዝነው ወንድ ዓይነ ጥላ ያለባቸው እህቶቻችን ምናልባት ትዳር ቢይዙም ከባላቸው ጋር አይስማሙም፡፡ ይጨቃጨቃሉ፡፡ ዓይነ ጥላቸው በወንድ አምሳል ስለገባ ሩካቤ ያስጠላቸዋል፡፡ ግን በተኙበት የሚገናኛቸው አለ፡፡
በሴቶች ላይ በወንድ አምሳል ዓይነ ጥላው ሲያድርባቸው ነውጠኛ ነው የሚሆኑት፡፡ እነሱ ያሉበት ክርክር፣ጠብ መብረጃ የለውም፡፡ ዓይነ ጥላው በቅጽበት ስለሚቀይራቸው የሚናገሩትን፣የሚያደርጉትን አያውቁም ቢያውቁም እራሳቸውን መቆጣጠር አይችሉም፡፡ በዚህም ለሰው አስቸጋሪ ናቸው፡፡
ሴቶች ላይ ወንድ ዓይነ ጥላው ሌሊት በተኙበት እየመጣ በገሃድ በሚመስል መልኩ ይገናኛቸዋል፡፡ ሲገናኛቸው አንዳንዱን በማስገደድ በሚመስል መልኩ ነው፡፡ ሌሎችን ደግሞ አስለምዷቸው መደበኛ እስኪመስል ድረስ ነው፡፡ ግን በየትኛውም መልኩ ይሁን ወንድ ዓይነ ጥላ ሴቶችን በተኙበት ሲገናኛቸው ጠዋት ከእንቅልፋቸው ሲነሱ የመደበት፣እራስ ምታት ይሰማቸዋል፡፡ ቀኑን ሙሉ አስጠልቷቸው ነው የሚውሉት፡፡
እዚህ ላይ አንዳ ለረጅም ዓመታት ስለማውቃች ወዳጄ ላጫውታችሁ፡፡ እንጦጦ ማርያም የማውቃት ልጅ አለች፡፡ ይቺ ልጅ ይህ በጣም መልከኛ ናት፡፡ ያያት ወንድ በቀላሉ ይሰናከልባታል፡፡ ከመንፈሳዊ ሰብእናዊ በተጨማሪ በመልኳና በቁመናዋ ለትዳር የማይጠይቃት ሰው የለም፡፡ እኔም ለምን በቤተክርስትያን ሥርዓት እንደማታገባ ስጠይቃት አስገራመ ነገር ነገረችኝ፡፡
እንጦጦ ማርያም ለጸበል የመጣቸው ሌሊት እየመጣ በሥርዓት እየተገናኛት በሚሔደው ሰው መሰል አጋንንት ነው፡፡ አጋንንቱ እንደ ተኛች ይመጣል፡፡ ሲመጣ አንዳች የሚከብድ እና ለመነሳት ኃይል እስክታጣ ሰውነቷን ማዘዝ ወደማትችልበት ሁኔታ ውስጥ ትገባች፡፡ አጋንንቱን በገሃድ በሚመስል ሩካቤ ተገናኝቷት ይሄዳል፡፡ ይህ ለዘመናት የለመደችው ግን ለሰው ያላማከረችው ብታማክርም ከሰው መፍትሔ አላገኝም ብላ የምትሰቃይበት ነገር ነው፡፡
ልጅቷ አንድ ወንድ ለጓደኝነት ከጠየቃት የዛን ቀን ሌሊት ስትሰቃይ ታድራለች፡፡ አንድ ወንድ ለጋብቻ እንደሚፈልጋት ከነገራች አጋንንቱ ሌሊት መጥቶ ‹‹ባልሽ እኔነ ነኝ እኔን የት ትተሸ ነው የምታገቢው›› እያለ ያስፈራራታል ይገናኛታል፡፡ በዚህም የወንድ ጓደኛ ከያዘች ‹‹ያስጠሉኛል፣ የወደድኩትን ሰው አግኝቼ ለማውራ ጭንቅ ይለኛል፣ሳያቸው ደስ አይሉኝም፣ይሰለቹኛል›› ትለኛለች፡፡
ቤተሰብ የልጅቷን ችግር ሊረዳላት አልቻለም፡፡ ይቺ ልጅ ሰው በማያውቅላት፣በማይረዳት ችግር ብዙ ስትፈተን ከርማ ከአምስት ዓመት ከጸበል፣ከጾም፣ከጸሎት ትግል በኃላ በራስዋ ጥረት እና በእመቤታችን ጸሎት ከዚህ ችግር ተላቃ በአሁን ጊዜ አግብታለች፡፡ ስለ እውነት ነው የምላችሁ ከችግሩ ተላቃ ጓደኛ እንደ ያዘች እና በቅርቡም ሊጋቡ መሆኑን የነገረችኝ ቀን ምን ያህል እንደተደሰትኩ እኔ ነኝ የማውቀው፡፡ ሌሊት እየመጣ የሚገናኝትም ወንድ ዓይነ ጥላ ድራሹ ጠፍቶላት አሁን ከባልዋ ጋር በሰላም መኖርዋ የእሷ ብቻ ሳይሆን የእኔም ደስታ ነበር፡፡ ወንድ ዓይነ ጥላ ስለማያፍር ባል እና ሚስት ተኝተው ሚስትን ተገናኝቷት ሊሔድ ይችላል፡፡
ወዳጆቼ ይህ ሌሊት እየመጣ ሴቶችን የሚገናኝ ዓይነ ጥላ ዋናው ዓላማ ሴቶችን ትዳር እንዳይዙ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም እንዲመቸው ለትዳር የሚመጡትን ወንዶች ሁሉ ምክንያት በሚመስል ነገሮች እንዲጠሉዋቸው ያደርጋል፡፡ ሴቶቹም የራሳቸው ሐሳብና ፍላጎት እየመሰላቸው በወንዱ ላይ አቃቂር እያወጡ ይንቃሉ ይጠላሉ፡፡
ወንድ ዓይነ ጥላ ያለባቸው ሴቶች አንዳንዶቹ የሩካቤ ሥጋ ፍላጎት እና ጉጉት በፍጹም የለባቸውም፡፡ ሩካቤን እንኳን ሊፈጽሙት ስለ ሩካቤ ሲወራ ያስጠላቸዋል፡፡ ቤተሰብም ልጃቸው ከወንድ በመራቅዋ፣ትዳር ባለመያዝዋ እንደ ጨዋ ያይዋታል፡፡ ግን የትዳር ሕይወትዋን ዓይነ ጥላው
በመገርገር፣የሚመጡትን ወንዶች በማባረር በስውር እንደ ሚዋጋት አያውቁም፡፡
የዚህ ዓይነ ጥላ አንዱና ክፉ መገለጫው ሴቶችን በጊዜያቸው ወይም በወጣትነታቸው እድሜ ትዳር እንዳይዙ ሲከላከል ይኖርና እነሱ ‹‹እድሜዬ እየሄደ ነው›› ብለው ማሰብ ሲጀምሩ ጭራሽ ወንድ እያራቀባቸው ተስፋ የመቁረጥ ሕይወት ውስጥ ይከታቸዋል፡፡ ይህም ዓይነ ጥላው እግዚአብሔር እንደተዋቸው፣እንደማያያቸው በማሳሰብ በሥጋዊ ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ሕይወትም በተስፋ መቁረጥ ይዋጋቸዋል፡፡
ወንድ ዓይነ ጥላ ያለባቸው ሴቶች ለግለ ወሲብ እጅጉን የተጋለጡ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ከተመሳሳይ ጾታ ጋር ግለ ወሲብ የሚፈጽሙት ‹‹ሌዝቢያን›› የሚባሉት የወንድ ዓይነ ጥላ ውጤቶች ናቸው፡፡ ዓይነ ጥላው በፍጹም ከወንድ ጋር ግንኙነት አይፈልግም፡፡ በራሳቸው ደግሞ ግለ ወሲብን የሚፈጽሙትም የወንድ ዓይነ ጥላው ግፊት ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ሴት ከወንድ ጋር ግንኙነት ማድረግ ትጠላለት ግን የምታውቀውን ወይም የማታውቀውን ሰው በህሊናዋ እየሳለች ልክ ከእሱ ጋር በሚመስል ነገር ግለ ወሲብ ትፈጽማለች፡፡ ይህም ወንዱ ዓይነ ጥላ ወንዶችን እንድታስብ በማድረግ በግለ ወሲብ ይጠምዳታል፡፡ ይህን ክፉ ልማድ ካላመዳት በኃላ ከዚህ ሕይወት ለመውጣት ያስቸግራታል፡፡
ወንድ ዓይነ ጥላ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው በርታ ያሉትንም ይፈትናቸዋል፡፡ በተለይ ንግስ መሄድ፣ቅዱስ ቁርባን መቀበል፣ጸበል መጠመቅ ሲያስቡ በሕልመ ሌሊት እየተመሰለ ሌሊት ይገናኛቸዋል፡፡ በዚህም በመንፈሳዊ ተግባራቸው እንቅፋት እና መሰናክል ይሆንባቸዋል፡፡ እህቶቼ እስኪ ልብ በሉ ብዙ ጊዜ ‹‹ነገ ቤተክርስትያን እሄዳለሁ፣እንዲህ አደርጋለሁ›› ያላችሁ ቀን ዓይነ ጥላው በሕልመ ሌሊት በመፈተን መሰናክል ይሆንባችኃል፡፡
ይህ ዓይነ ጥላ የራሳችንን ነገር በመንጠቅ፣የራሱን ከእኛ ጋር በመደባለቅ ሌላ ሰው ስለሚያደርገን ከዚህ መንፈስ ለመላቀቅ በጾም፣በጸሎቱ፣በስግደቱ በጸበሉ መታገል ያስፈልገናል፡፡
የዚህ ዓይነ ጥላ አንዱና ክፉ መገለጫው ሴቶችን በጊዜያቸው ወይም በወጣትነታቸው እድሜ ትዳር እንዳይዙ ሲከላከል ይኖርና እነሱ ‹‹እድሜዬ እየሄደ ነው›› ብለው ማሰብ ሲጀምሩ ጭራሽ ወንድ እያራቀባቸው ተስፋ የመቁረጥ ሕይወት ውስጥ ይከታቸዋል፡፡ ይህም ዓይነ ጥላው እግዚአብሔር እንደተዋቸው፣እንደማያያቸው በማሳሰብ በሥጋዊ ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ሕይወትም በተስፋ መቁረጥ ይዋጋቸዋል፡፡
ወንድ ዓይነ ጥላ ያለባቸው ሴቶች ለግለ ወሲብ እጅጉን የተጋለጡ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ከተመሳሳይ ጾታ ጋር ግለ ወሲብ የሚፈጽሙት ‹‹ሌዝቢያን›› የሚባሉት የወንድ ዓይነ ጥላ ውጤቶች ናቸው፡፡ ዓይነ ጥላው በፍጹም ከወንድ ጋር ግንኙነት አይፈልግም፡፡ በራሳቸው ደግሞ ግለ ወሲብን የሚፈጽሙትም የወንድ ዓይነ ጥላው ግፊት ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ሴት ከወንድ ጋር ግንኙነት ማድረግ ትጠላለት ግን የምታውቀውን ወይም የማታውቀውን ሰው በህሊናዋ እየሳለች ልክ ከእሱ ጋር በሚመስል ነገር ግለ ወሲብ ትፈጽማለች፡፡ ይህም ወንዱ ዓይነ ጥላ ወንዶችን እንድታስብ በማድረግ በግለ ወሲብ ይጠምዳታል፡፡ ይህን ክፉ ልማድ ካላመዳት በኃላ ከዚህ ሕይወት ለመውጣት ያስቸግራታል፡፡
ወንድ ዓይነ ጥላ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው በርታ ያሉትንም ይፈትናቸዋል፡፡ በተለይ ንግስ መሄድ፣ቅዱስ ቁርባን መቀበል፣ጸበል መጠመቅ ሲያስቡ በሕልመ ሌሊት እየተመሰለ ሌሊት ይገናኛቸዋል፡፡ በዚህም በመንፈሳዊ ተግባራቸው እንቅፋት እና መሰናክል ይሆንባቸዋል፡፡ እህቶቼ እስኪ ልብ በሉ ብዙ ጊዜ ‹‹ነገ ቤተክርስትያን እሄዳለሁ፣እንዲህ አደርጋለሁ›› ያላችሁ ቀን ዓይነ ጥላው በሕልመ ሌሊት በመፈተን መሰናክል ይሆንባችኃል፡፡
ይህ ዓይነ ጥላ የራሳችንን ነገር በመንጠቅ፣የራሱን ከእኛ ጋር በመደባለቅ ሌላ ሰው ስለሚያደርገን ከዚህ መንፈስ ለመላቀቅ በጾም፣በጸሎቱ፣በስግደቱ በጸበሉ መታገል ያስፈልገናል፡፡
“ማግባት ለሚሹ”
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡
ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ፦ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡
አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡
እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡
እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡
እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡
ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ፦ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡
አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡
እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡
እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡
እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
ወደ ኣባታችን መምህር ግርማ ወይም ወደ ጠበል የምትሄዱ ወንድምች እህቶች ከመሄዳችሁ በፊት ማድረግ ያለባችሁ ጥቂት ነገር ኣለ ፡፡ እሱም በቤታችን ትንሽ የፀሎት ቤት ማዘጋጀት ኣለብንን ፡፡ የፀሎት ቤት ስናዘጋጅ በትንሹ በኣባቶች የተባረከ የስላሴ ወይም የማርያም ወይም የሚካኤል ወይም ያለንን ስእለ ኣድህኖ መቁጠርያና ውዳሴ ማርያም ካለን ለመጀመር በቂ ነው ፡፡ ከዛ ምንፀልይበት ፊታችን ወደ ምስራቅ ኣቅጣጫ የፀሎት እቃዎቻችን ማስቀመጥ ኣለብን ፡፡ ከዛ ፀሎት ስንጀምር "አአትብ ገፅየ" የሚለውን ፀሎት ጀመርን ብኃላ እግዚአብሔር ማመስገን እንጀምራለን ፡ ጧት ከሆነ እግዚአብሔር ጨለማውን ኣሳልፎ ብርሃን ስለኣሳየን ፡ ሌሊቱን ኣሳልፎ የጥዋትን ፀሃይ ስላሳየን እናመሰግነዋለን ፡፡ ማታ ከሆነ ደግሞ ቀኑን ኣሳልፎ የእረፍት ሰዓት ስለደረሰን ቀኑን ኣልፈን ጨለማውን ስለኣየነው የጊዜ ባለቤት የሆነውን እግዚአብሔር እናመሰግነዋለን ፡ ለኣዳም ልጆች ማገልገያ ብሎ ስለፈጠራቸው ሰለ ስነ ፍጥረቱ እናደንቀዋለን እናመሰግነዋለን ፡፡ ከዛ የዘወትር ፀሎትና የእለቱ ውዳሴ ማርያም ጊዜ ካለንም እስከቻልነው መፀለይ ፡፡ ከዛ ቡኃላ መቁርያውን በእጃችን በመያዝ ሶስት ጊዜ እስትንፋሳችን እፍ ካልንበት ብኃላ#በህያው_እግዚአብሔር_ብሩክ_እግዚአብሔር_ምስጉን_እግዚአብሔር_ቅዱሰ_እግዚአብሔር_ቸር_እግዚአብሔር_ከሃሊ_እግዚአብሔር_ይቅርባይ_እግዚአብሔር_እፁብ_እግዚአብሔር_በድንቅ_እግዚአብሔር_ስም #ኣዶናይ_ኤልሻዳይ_ፀባኦት_ያህዌ_ኣልፋ_ኦሜጋ_ቅዱስ_ቅዱስ_ቅዱስ_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ኣማኑኤል በማለት መቁጠርያው ላይ እስትንፋሳችን ሶስት ጊዜ እፍ እንልበታለን ፡፡ ከዛ ቡኃላ የሚዋጉንን ጠላቶች ቡዳ ፡ ዓይነ ጥላ ፡ ዛር ፡ መስተፋቅር ፡ መተት ስማቾው የተጠራም ያልተጠራም ቤትም ያሉ በውጪም ያሉ የጨለማ መንፈሶች የሲኦል መንፈሶች በሙሉ በኣምላካችን በጌታችን
በመድሓኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በድንግል ማርያም ስም በሚካኤል ስም በስላሴ ስም በሌሎችም በፃድቃና ስም በመላእክት ስም በሃዋርያት ስም በመቁጠርያው ቀስ እያደረግን ሰውነታችን እየመታን የሌሉትን እንዳይቀርቡን ያሉትን ደግሞ
ጉዳት እንዳያደርሱና ወደ ፀበል ስንሄድ ቤት ውስጥ ወይም መንገድ ላይ እንዳይቀሩ በማውገዝ በፅኑ ቃል በእግዚአብሔር ቃል ማሰር ኣለብን ፡፡ እንዲሁም በማህበራዊ ኑሮኣችን ጉዳት እንዳያደርሱም በየቀኑ ጠላቶቻችን እግዚአብሔር እንዲያስራቸው መለመን ኣለብን ፡፡ ወደሰርግ ፣ ወደ ግብዣ ወደ ኣስፈላጊ ቀጠሮ ፣ ወደ ትምህርትና ፈተና ፣ ወደ ፍርድ ቤት ወይም ጉዞ ስንሄድ የምንፀልየው ፀሎት ሲሆን ምንም እንኳ ሊሳካልን ላይሳካልን በእግዚአብሔር ፈቃድ ቢሆንም በየመንገዳችን እየቀደሙ ጉዳያችን ሊያበላሹብን የነበሩ ጠለቶች ግን በእርግጠኝነት በእግዚአብሔር ቃል በመላእክትእጅ ይታሰራሉ ፡፡ እንግዲህ እዚጋ ዋና መድሓኒት ፀሎትና መቁጠርያ ነው ማለት ነው ፡፡ እግዚአብሔር ከፈቀደልን ስለ መቁጠርያ ጥቅም ከብዙ የምስራች ጋር እንመለሰዋለን ፡፡ ለኣሁን ግን በጥቂቱ ይህችን #መቁጠርያ በመጠቀም ፀሎት በመፀለይ ንስሃ በመግባት ከተቻለ ቅዱስ ቁርባን በመውሰድ ካልተቻለ የተቀየምነውን ይቅር በማለት ፡
ልባችንን ንፁህ በማድረግ ለዘመናት ያሰቃየንን ፣ ዘመናችን ሲያጨልም የነበረውን ጠላት ፀሎትና መቁጠርያን በመጠቀም ምርር ስልችት እስኪለው ድረስ መዋጋት ፡ ኣባታችን ጋር ወይም ወደ ፀበል ስትሄዱ ይህ የመጀመረያ እርምጃ ሲሆን መንፈሱ ተቀጥቅጦና ታስሮ ከኛ ጋር መሄድ ኣለበት ፡፡ እንግዲህ ፀበል ቤት ኣልያም ኣባታችን ፊት ስትሄዱ መንፈሱ ይፈነዳል ፡፡ በዚዚህ ኣጋጣሚ ኣንዳንዶቹ ቢደበቁም ኣንዳንዶቹ ቢገለጡም በጥቂቱ ዓይነ-ጥላ ወይም ቡዳ ወይም ዛር የሌለው ሰው የለም ፡፡ ስለዚ እናንተም በፀሎት ኣዳክማችሁት ፀበል ሲነካው ወይም ኣባታችን ፊት ስትሆኑ በቃ ይሄ መቋቋም ስለማይችል ራሱን ገልጦ ምስጢሩን እንዳለ ዘክዝኮ መሰናበት ይፈልጋል ፡ ይህ በጥቂቱ ብዙ ምስጢር ምታዩበት ብዙ ፀጋ ምታገኙበት የተደበቀ እውነት ምታውቁበት ስስለሆነ መበርታት ኣለባችሁ ፡ ስለዚህ ምትሄዱት ጠንቋይ ቤት ኣይደለምና ወደ እግዚአብሔር ቤት ነውና ይሄንን በንፁህ ልቦና ተጠቀሙበት ፡፡ ብን ብላላችሁ ተነስታችሁ ኣትሂዱ ፡፡ እንግዲህ ይህ ከጀመራችሁት እጅግ ጣፋጭ ሲሆን የተበቀለንን ድያብሎስ እኛም እሱን በእግዚአብሔር ቃል ኣስረን በየቀኑ ምርር እስኪለው የምንበቀልበት ሲሆን በየቀኑ የመንገዳችሁና የኣዲስ ሂወታችሁ የመጀመርያና ኣንደኛ እርምጃ ነው ፡፡ ይቀጥላል ፧ ለሌሎችም share ኣድርገት
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለሰጣቸው ፀጋ እናመሰግነዋለን
ክርስቶሰ በቸርነቱ ያስበን
በመድሓኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በድንግል ማርያም ስም በሚካኤል ስም በስላሴ ስም በሌሎችም በፃድቃና ስም በመላእክት ስም በሃዋርያት ስም በመቁጠርያው ቀስ እያደረግን ሰውነታችን እየመታን የሌሉትን እንዳይቀርቡን ያሉትን ደግሞ
ጉዳት እንዳያደርሱና ወደ ፀበል ስንሄድ ቤት ውስጥ ወይም መንገድ ላይ እንዳይቀሩ በማውገዝ በፅኑ ቃል በእግዚአብሔር ቃል ማሰር ኣለብን ፡፡ እንዲሁም በማህበራዊ ኑሮኣችን ጉዳት እንዳያደርሱም በየቀኑ ጠላቶቻችን እግዚአብሔር እንዲያስራቸው መለመን ኣለብን ፡፡ ወደሰርግ ፣ ወደ ግብዣ ወደ ኣስፈላጊ ቀጠሮ ፣ ወደ ትምህርትና ፈተና ፣ ወደ ፍርድ ቤት ወይም ጉዞ ስንሄድ የምንፀልየው ፀሎት ሲሆን ምንም እንኳ ሊሳካልን ላይሳካልን በእግዚአብሔር ፈቃድ ቢሆንም በየመንገዳችን እየቀደሙ ጉዳያችን ሊያበላሹብን የነበሩ ጠለቶች ግን በእርግጠኝነት በእግዚአብሔር ቃል በመላእክትእጅ ይታሰራሉ ፡፡ እንግዲህ እዚጋ ዋና መድሓኒት ፀሎትና መቁጠርያ ነው ማለት ነው ፡፡ እግዚአብሔር ከፈቀደልን ስለ መቁጠርያ ጥቅም ከብዙ የምስራች ጋር እንመለሰዋለን ፡፡ ለኣሁን ግን በጥቂቱ ይህችን #መቁጠርያ በመጠቀም ፀሎት በመፀለይ ንስሃ በመግባት ከተቻለ ቅዱስ ቁርባን በመውሰድ ካልተቻለ የተቀየምነውን ይቅር በማለት ፡
ልባችንን ንፁህ በማድረግ ለዘመናት ያሰቃየንን ፣ ዘመናችን ሲያጨልም የነበረውን ጠላት ፀሎትና መቁጠርያን በመጠቀም ምርር ስልችት እስኪለው ድረስ መዋጋት ፡ ኣባታችን ጋር ወይም ወደ ፀበል ስትሄዱ ይህ የመጀመረያ እርምጃ ሲሆን መንፈሱ ተቀጥቅጦና ታስሮ ከኛ ጋር መሄድ ኣለበት ፡፡ እንግዲህ ፀበል ቤት ኣልያም ኣባታችን ፊት ስትሄዱ መንፈሱ ይፈነዳል ፡፡ በዚዚህ ኣጋጣሚ ኣንዳንዶቹ ቢደበቁም ኣንዳንዶቹ ቢገለጡም በጥቂቱ ዓይነ-ጥላ ወይም ቡዳ ወይም ዛር የሌለው ሰው የለም ፡፡ ስለዚ እናንተም በፀሎት ኣዳክማችሁት ፀበል ሲነካው ወይም ኣባታችን ፊት ስትሆኑ በቃ ይሄ መቋቋም ስለማይችል ራሱን ገልጦ ምስጢሩን እንዳለ ዘክዝኮ መሰናበት ይፈልጋል ፡ ይህ በጥቂቱ ብዙ ምስጢር ምታዩበት ብዙ ፀጋ ምታገኙበት የተደበቀ እውነት ምታውቁበት ስስለሆነ መበርታት ኣለባችሁ ፡ ስለዚህ ምትሄዱት ጠንቋይ ቤት ኣይደለምና ወደ እግዚአብሔር ቤት ነውና ይሄንን በንፁህ ልቦና ተጠቀሙበት ፡፡ ብን ብላላችሁ ተነስታችሁ ኣትሂዱ ፡፡ እንግዲህ ይህ ከጀመራችሁት እጅግ ጣፋጭ ሲሆን የተበቀለንን ድያብሎስ እኛም እሱን በእግዚአብሔር ቃል ኣስረን በየቀኑ ምርር እስኪለው የምንበቀልበት ሲሆን በየቀኑ የመንገዳችሁና የኣዲስ ሂወታችሁ የመጀመርያና ኣንደኛ እርምጃ ነው ፡፡ ይቀጥላል ፧ ለሌሎችም share ኣድርገት
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለሰጣቸው ፀጋ እናመሰግነዋለን
ክርስቶሰ በቸርነቱ ያስበን
ዓይነ ጥላ እና ግለ ወሲብ በወንዶች እና በሴቶች ላይ
/ኃጢአተ አውናን/
ዓይነ ጥላ እግዚአብሔር በሰጠን ሳይሆን እራሱ በቀደደልን የክፋት እና የጨለማ መንገድን በመምራት ብሎም ሕይወትን በማበላሸት ተወዳዳሪ የለውም፡፡ የዚህ መንፈስ አንዱ ጠባዩ አፈንጋጭነቱ ነው፡፡ ይህንን የማፈንገጥ ጠባይ በእኛ ሕይወት ውስጥ በማስለጥ ኢ-ሩካቤ እና ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ማወሰቦችን ያለማምደናል፡፡ ከዚህ ቀደም እንዳየነው ዓይነ ጥላ ከማሕፀን፣ከአራስነት እና ከጊዜ ቦኃላ ወደ ሕይወታችን በመግባት በራሱ ተንኮል በመቃኘት፣ከተፈጥሮ ያፈነገጠ ሕይወት እንዲኖረን ያደርገናል፡፡ በዚህ ጠባዩ የእሱን መርገም፣በእኛ ሕይወት በመድገም የእርግማን ትውልድ ያደርገናል፡፡ ከሁሉም የሚከፋው በመናፍስቱ የሚመጣ ግለ ወሲብ ነው፡፡ ምክንያቱም መልሶ በማገርሸት ይጠምደናል፡፡
ግለ ወሲብ በሰው ልጆች ሕይወት ጥንታዊ ኃጢአት ከሆነው አንዱ ነው፡፡ ግለ ወሲብ በሰው ልጆች ዘንድ መቼ እንደተጀመረ ጥንታዊ የታሪክ ዳራውን ስናይ ቀደምት ጀማሪዎቹ ሮማዎች ናቸው፡፡ ዘመኑም ከክርስቶስ ልደት በፊት በ4000 ዓመተ ዓለም ገደማ ነው፡፡ ግለ ወሲብ በሮማ ኢምፓየር በዓለም ላይ እጅጉን እንደተስፋፋ የታሪክ መዛግብት ይነግረናል፡፡ ከሮማ በመቀጠል ግብጾች ከክርስቶስ ልደት በፊት በ3000 ዓመተ ዓለም እንደ ጀመሩ ተመዝግቧል፡፡ ጥንታውያን ሮማዎችም ሆኖ ግብጾች ግለ ወሲብን ከማህበራዊ እድገታቸው ጋር በማያያዝ ለፍትወት ማብረጃ እና ለወሊድ መቆጣጠሪያ ይጠቀሙበት ነበር፡፡ ይህንን ያወቀው ቅዱሳ ጳውሎስ በሮም ለሚኖሩ ክርስትያኖች እንዲማሩበት እንዲጠነቀቁበት ‹‹ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የማይገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባ ለወጡ፤ወንዶቹ ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታው ተቃጠሉ›› በማለት ጽፎላቸዋል፡፡ /ሮሜ 1÷26-27/ ልብ ካልን ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን መልእክት የጻፈው ከጥንት ጀምሮ በሮም ግለ ወሲብና ግብረ ሰዶም ስለ ተስፋፋ ክርስትያኖች ከዚህ ጸያፍ ድርጊት እንዲታቀቡ ለማሳሰብ እንደ ሆነ ግልጽ ነው፡፡
ወዳጆቼ ግለ ወሲብን ጠላት ሰይጣን ገና የሰው ልጆች ተፈጥረው በአግባቡ መብዛት ባልጀመሩበት ዘመን ነው ወደ ሕይወታው ያሰረጸው፡፡ በዚህ መልኩ ሰይጣን ያመጣውን፣ለሰዎች ያስለመደውን ግለ ወሲብ በዘመናችን በማስፋፋት ዛሬ ላይ አድርሶታል፣ብዙዎችን አሰቃይቶበታል እያሰቃየም ነው፡፡
ተወዳጆች ሆይ ግለ ወሲብ ማለት ተፈጥሮአችን ባልሆነ መልኩና መንገድ እርካታን ለማግኘት የምንጠቀምበትሁለተኛው የሰይጣን ወጥመድ ነው፡፡ ድርጊቱም የራስን አካል በራስ አካል ማርካት ነው፡፡ ግለ ወሲብ በወንዶችም በሴቶችም ላይ ይጸናል፡፡ ግለ ወሲብ በሁለት መንገድ ወደኛ ይመጣል፡፡ አንደኛው በርኩሳን መናፍስት እንደ ዓይነ ጥላና እንደ ዝሙት መንፈስ ባሉ ይመጣል፡፡ በፊልም በምናያቸው፣በምናነባቸውና ዘልማድ በምናደርጋቸው ትእይንቶች ይመጣሉ፡፡
ግለ ወሲብ ከልጅነት እስከ ወጣትነት ባለ እድሜ ውስጥ የሚጠናወት አስከፊወሲብን ተግባር ነው፡፡ ልዩ ልክፍትም ነው፡፡ ምክንያቱም ግለ ወሲብን ወንዶቹም ሴቶቹም ከለመዱት በቀላሉ ለመላቀቅ ይቸገራሉ፡፡ ለብዙዎች ግለ ለመተው ሺሻን መተው ይቀላቸዋል፡፡ መንፈሳዊ ነን የሚሉትም በዚህ ችግር ክፉኛ ይጠቃሉ፡፡ ይህ ድርጊት እግዚአብሔር ቆርጦ ካልጣለልን በስተቀር አንዳንዱቹ በምክር፣ በንስሐ፣በጸበል መተው ይቸገራሉ፡፡ ድርጊቱም እንደ ኮሶ ሲጣባ፣ግራ የሚያጋባ ሕይወት ውስጥ ይከተናል፡፡ ሌላ ችግሩ ግለ ወሲብን በእጁ መፈጸም የጀመረ ሰው ምናልባት ትቶት ወደ ትዳር ዓለም ውስጥ ሲገባ ትልቅ ችግር ይገጥመዋል፡፡ እራስን በራስ ማወሰብ ለምዶ የተፈጥሮ የሆነው ሕጋዊ ሩካቤ እምብዛም ላያስደስተው ይችላል፡፡
ብዙ ወንዶችና ሴቶች በእጅ የሚፈጸም ግለ ወሲብን ከትዳር በፊት ይፈጽሙታል፡፡ ይህም በተግባር የሚፈጸመውን ሩካቤ በመፍራት፣በራሳቸው ሕይወት የግላቸውን ይፈጽማሉ፡፡ የግለ ወሲብ አንዱ ችግር ዘርን ያለ አግባብ ያለቦታው በማፍሰስ በኃጢአት ላይ ኃጢአትን መጨመር ነው፡፡ ወዳጄ ስንት ለአገርና ለወግን ለቤተ ክርስትያን የሚጠቅሙ ዘሮች ያለ ቦታቸው ወድቀዋል፡፡ አንተ ያለ ቦታው የምታፈሰው ዘር ምናልባት ባለ ትዳሮች ልጃቸው አንዲሆን የሚመኙት ነው፡፡ ይህን መጨረሻው ላይ በዝርዝር እናያለን፡፡
ሴቶች ደንግልናቸውን ከመጠበቅና ደፍረውም ተፈጥሮአዊ ሩካቤን ለመፈጸም ከመፍራት አንጻር ግለ ወሲብን በአልጋቸው ላይ ይፈጽማሉ፡፡ ግን በእነዚህ ሁሉ ድርጊቶች የዝሙት መንፈስ ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡ ዝሙትንሥራ አልፈጽምም ብለን የሥጋ ንጽህናችንን ብትጠብቅም በግለ ውሲብ በመፈተን ንጽህናችንን እናጎድላለን ‹‹ሴቶቻቸውም ለባሕሪያቸው የሚገባውን ለባሕሪያቸው በማይገባው ለወጡ›› የተባለው ይሄም ነው፡፡ /ሮሜ 1÷26/ ሰይጣን መናልባትም ኃጢአት እስከ ማይመስል ድረስ እየመከረ፣በግለ ወሲብ እያሰከረ ትውልዱን ይጫወትበታል፡፡ ይህንን ድርጊት የሚፈጽሙትን ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹እናንተ ከአባታችሁ ከዲያቢሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ›› በማለት በእጅጉ ይገስጸናል፡፡ ዮሐ 8÷44
ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ እኛን በግለ ወሲብ በመጥመዱ በማስለመዱ ሁለት ጥቅም ያገኛል፡፡ በተለይ ሰውን ከተፈጥሮ ውጭ ዓይን አፋር የሚያደርግ ዓይነ ጥላ ግለ ወሲብን ያስለምዳል፡፡ አንደኛው ተፈጥሮአችን ባልሆነና በማይስማማን መልኩ እርካታን እያገኘን ግለ ወሲብን በማቆራኘት ከተፈጥሮ ሩካቤ ማስወጣት ሲሆን ሁለተኛው በግለ ወሲብ ምክንያት የኃጢአታችንን ሒሳብ ከፍ በማድረግ ከፈጣሪ ማጣለት እና መቆራረጥ ነው፡፡ ሰይጣን በግለ ወሲብ እነዚህን ሰይጣናዊበፊልም ጥቅም ስለሚያገኝ ነው ግለ ወሲብን ለመተው ከባድ የሚሆንብን፡፡
ሁለተኛው በምናያቸው፣በምናነባቸውና ዘልማድ በምናደርጋቸው ትእይንቶች የሚመጣው ግለ ወሲብ የብዙ ሰው ልማድ ሆኗል፡፡ ይህ ክፉ ሰይጣናዊ ልማድ በአሁን ሰዓት ያልታወቀበት ግን ብዙ ወጣቶች የሚሰቀዩበት ወረርሽኝ ሆኗል፡፡ ወዳጆቼ ከኃጢአት ሁሉ ክፉ ኃጢአት አንድ ድርጊት ልማድ ሲሆን ነው፡፡ ልማድ ከሆነ ንስሐ፣ምክር፣ትምህርት በቀላሉ ላያላቅቁን ይችላሉ፡፡ ልማድ ከሆነ ደግሞ ድፍረት ይሆንና የድፍረት ኃጢአት ሆኖ ስንተገብረው ምንም ላይመስለን ይችላል፡፡ እንደ ዳዊት ‹‹የድፍረት ኃጢአት እንዳይገዛኛ ባሪያህን ጠብቅ፤የዚያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ፣ከታላቅም ኃጢአት እነጻለሁ›› ብለን ልንጸልይ ይገባል፡፡ /መዝ 19÷13/
ግለ ወሲብን ከአፈጻጸሙ አንጻር በአራት ከፍለን እናያቸዋልን፡፡ አንደኛ የደናግል ግለ ወሲብ ነው፡፡ ከላይ እንዳየነው በውስጣችን ያለው ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ ሩካቤ ብንፈጽም ድንግልናየን አጣለሁ ግን ደግሞ በፍትወት እሰቃያለሁ የሚሉትን ሰዎችን የሚያጠቃ ነው፡፡ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ለድንግልናቸው እንጂ ለቅድስናቸው ካለመጠንቀቅ ይፈጽሙታል፡፡ ይህም አንዳንዴ ሴቶቹ ግለ ወሲብን ለብቻቸው፣አልጋቸው ውስጥ በመሆን በእጃቸው አፍረታቸውንና የስሜት አካላቸውን በመነካካት ይፈጽሙታል፡፡
ወንዶቹ ደግሞ የከበረ እጃቸውን በመጠቀም ግለ ወሲብን ይፈጽማሉ፡፡ በዚህ ድርጊት ቅድስና እና ንጽሕና ይጠፋል፡፡ ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ ይህንን ጠባይ ከልጅነታቸው ጊዜ ጀምሮአጋጣሚ በማውረስ እስከ አሁን ሕይወታቸውን በማቃወስ የሚጫወትባቸው አሉ፡፡ የዚህ አንዱና ዋነኛው ችግር የተፈጥሮን ሩካቤ ሳያውቁ ግለ ወሲብን ማጣጣም ነገ በትዳር መሃል ባለው ሕገ ሩካቤ ጣዕም ይቸገራሉ፡፡ አጋንንቱም ይህንን በመጠቀም የተፈጥሮ ሩካቤ
/ኃጢአተ አውናን/
ዓይነ ጥላ እግዚአብሔር በሰጠን ሳይሆን እራሱ በቀደደልን የክፋት እና የጨለማ መንገድን በመምራት ብሎም ሕይወትን በማበላሸት ተወዳዳሪ የለውም፡፡ የዚህ መንፈስ አንዱ ጠባዩ አፈንጋጭነቱ ነው፡፡ ይህንን የማፈንገጥ ጠባይ በእኛ ሕይወት ውስጥ በማስለጥ ኢ-ሩካቤ እና ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ማወሰቦችን ያለማምደናል፡፡ ከዚህ ቀደም እንዳየነው ዓይነ ጥላ ከማሕፀን፣ከአራስነት እና ከጊዜ ቦኃላ ወደ ሕይወታችን በመግባት በራሱ ተንኮል በመቃኘት፣ከተፈጥሮ ያፈነገጠ ሕይወት እንዲኖረን ያደርገናል፡፡ በዚህ ጠባዩ የእሱን መርገም፣በእኛ ሕይወት በመድገም የእርግማን ትውልድ ያደርገናል፡፡ ከሁሉም የሚከፋው በመናፍስቱ የሚመጣ ግለ ወሲብ ነው፡፡ ምክንያቱም መልሶ በማገርሸት ይጠምደናል፡፡
ግለ ወሲብ በሰው ልጆች ሕይወት ጥንታዊ ኃጢአት ከሆነው አንዱ ነው፡፡ ግለ ወሲብ በሰው ልጆች ዘንድ መቼ እንደተጀመረ ጥንታዊ የታሪክ ዳራውን ስናይ ቀደምት ጀማሪዎቹ ሮማዎች ናቸው፡፡ ዘመኑም ከክርስቶስ ልደት በፊት በ4000 ዓመተ ዓለም ገደማ ነው፡፡ ግለ ወሲብ በሮማ ኢምፓየር በዓለም ላይ እጅጉን እንደተስፋፋ የታሪክ መዛግብት ይነግረናል፡፡ ከሮማ በመቀጠል ግብጾች ከክርስቶስ ልደት በፊት በ3000 ዓመተ ዓለም እንደ ጀመሩ ተመዝግቧል፡፡ ጥንታውያን ሮማዎችም ሆኖ ግብጾች ግለ ወሲብን ከማህበራዊ እድገታቸው ጋር በማያያዝ ለፍትወት ማብረጃ እና ለወሊድ መቆጣጠሪያ ይጠቀሙበት ነበር፡፡ ይህንን ያወቀው ቅዱሳ ጳውሎስ በሮም ለሚኖሩ ክርስትያኖች እንዲማሩበት እንዲጠነቀቁበት ‹‹ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የማይገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባ ለወጡ፤ወንዶቹ ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታው ተቃጠሉ›› በማለት ጽፎላቸዋል፡፡ /ሮሜ 1÷26-27/ ልብ ካልን ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን መልእክት የጻፈው ከጥንት ጀምሮ በሮም ግለ ወሲብና ግብረ ሰዶም ስለ ተስፋፋ ክርስትያኖች ከዚህ ጸያፍ ድርጊት እንዲታቀቡ ለማሳሰብ እንደ ሆነ ግልጽ ነው፡፡
ወዳጆቼ ግለ ወሲብን ጠላት ሰይጣን ገና የሰው ልጆች ተፈጥረው በአግባቡ መብዛት ባልጀመሩበት ዘመን ነው ወደ ሕይወታው ያሰረጸው፡፡ በዚህ መልኩ ሰይጣን ያመጣውን፣ለሰዎች ያስለመደውን ግለ ወሲብ በዘመናችን በማስፋፋት ዛሬ ላይ አድርሶታል፣ብዙዎችን አሰቃይቶበታል እያሰቃየም ነው፡፡
ተወዳጆች ሆይ ግለ ወሲብ ማለት ተፈጥሮአችን ባልሆነ መልኩና መንገድ እርካታን ለማግኘት የምንጠቀምበትሁለተኛው የሰይጣን ወጥመድ ነው፡፡ ድርጊቱም የራስን አካል በራስ አካል ማርካት ነው፡፡ ግለ ወሲብ በወንዶችም በሴቶችም ላይ ይጸናል፡፡ ግለ ወሲብ በሁለት መንገድ ወደኛ ይመጣል፡፡ አንደኛው በርኩሳን መናፍስት እንደ ዓይነ ጥላና እንደ ዝሙት መንፈስ ባሉ ይመጣል፡፡ በፊልም በምናያቸው፣በምናነባቸውና ዘልማድ በምናደርጋቸው ትእይንቶች ይመጣሉ፡፡
ግለ ወሲብ ከልጅነት እስከ ወጣትነት ባለ እድሜ ውስጥ የሚጠናወት አስከፊወሲብን ተግባር ነው፡፡ ልዩ ልክፍትም ነው፡፡ ምክንያቱም ግለ ወሲብን ወንዶቹም ሴቶቹም ከለመዱት በቀላሉ ለመላቀቅ ይቸገራሉ፡፡ ለብዙዎች ግለ ለመተው ሺሻን መተው ይቀላቸዋል፡፡ መንፈሳዊ ነን የሚሉትም በዚህ ችግር ክፉኛ ይጠቃሉ፡፡ ይህ ድርጊት እግዚአብሔር ቆርጦ ካልጣለልን በስተቀር አንዳንዱቹ በምክር፣ በንስሐ፣በጸበል መተው ይቸገራሉ፡፡ ድርጊቱም እንደ ኮሶ ሲጣባ፣ግራ የሚያጋባ ሕይወት ውስጥ ይከተናል፡፡ ሌላ ችግሩ ግለ ወሲብን በእጁ መፈጸም የጀመረ ሰው ምናልባት ትቶት ወደ ትዳር ዓለም ውስጥ ሲገባ ትልቅ ችግር ይገጥመዋል፡፡ እራስን በራስ ማወሰብ ለምዶ የተፈጥሮ የሆነው ሕጋዊ ሩካቤ እምብዛም ላያስደስተው ይችላል፡፡
ብዙ ወንዶችና ሴቶች በእጅ የሚፈጸም ግለ ወሲብን ከትዳር በፊት ይፈጽሙታል፡፡ ይህም በተግባር የሚፈጸመውን ሩካቤ በመፍራት፣በራሳቸው ሕይወት የግላቸውን ይፈጽማሉ፡፡ የግለ ወሲብ አንዱ ችግር ዘርን ያለ አግባብ ያለቦታው በማፍሰስ በኃጢአት ላይ ኃጢአትን መጨመር ነው፡፡ ወዳጄ ስንት ለአገርና ለወግን ለቤተ ክርስትያን የሚጠቅሙ ዘሮች ያለ ቦታቸው ወድቀዋል፡፡ አንተ ያለ ቦታው የምታፈሰው ዘር ምናልባት ባለ ትዳሮች ልጃቸው አንዲሆን የሚመኙት ነው፡፡ ይህን መጨረሻው ላይ በዝርዝር እናያለን፡፡
ሴቶች ደንግልናቸውን ከመጠበቅና ደፍረውም ተፈጥሮአዊ ሩካቤን ለመፈጸም ከመፍራት አንጻር ግለ ወሲብን በአልጋቸው ላይ ይፈጽማሉ፡፡ ግን በእነዚህ ሁሉ ድርጊቶች የዝሙት መንፈስ ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡ ዝሙትንሥራ አልፈጽምም ብለን የሥጋ ንጽህናችንን ብትጠብቅም በግለ ውሲብ በመፈተን ንጽህናችንን እናጎድላለን ‹‹ሴቶቻቸውም ለባሕሪያቸው የሚገባውን ለባሕሪያቸው በማይገባው ለወጡ›› የተባለው ይሄም ነው፡፡ /ሮሜ 1÷26/ ሰይጣን መናልባትም ኃጢአት እስከ ማይመስል ድረስ እየመከረ፣በግለ ወሲብ እያሰከረ ትውልዱን ይጫወትበታል፡፡ ይህንን ድርጊት የሚፈጽሙትን ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹እናንተ ከአባታችሁ ከዲያቢሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ›› በማለት በእጅጉ ይገስጸናል፡፡ ዮሐ 8÷44
ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ እኛን በግለ ወሲብ በመጥመዱ በማስለመዱ ሁለት ጥቅም ያገኛል፡፡ በተለይ ሰውን ከተፈጥሮ ውጭ ዓይን አፋር የሚያደርግ ዓይነ ጥላ ግለ ወሲብን ያስለምዳል፡፡ አንደኛው ተፈጥሮአችን ባልሆነና በማይስማማን መልኩ እርካታን እያገኘን ግለ ወሲብን በማቆራኘት ከተፈጥሮ ሩካቤ ማስወጣት ሲሆን ሁለተኛው በግለ ወሲብ ምክንያት የኃጢአታችንን ሒሳብ ከፍ በማድረግ ከፈጣሪ ማጣለት እና መቆራረጥ ነው፡፡ ሰይጣን በግለ ወሲብ እነዚህን ሰይጣናዊበፊልም ጥቅም ስለሚያገኝ ነው ግለ ወሲብን ለመተው ከባድ የሚሆንብን፡፡
ሁለተኛው በምናያቸው፣በምናነባቸውና ዘልማድ በምናደርጋቸው ትእይንቶች የሚመጣው ግለ ወሲብ የብዙ ሰው ልማድ ሆኗል፡፡ ይህ ክፉ ሰይጣናዊ ልማድ በአሁን ሰዓት ያልታወቀበት ግን ብዙ ወጣቶች የሚሰቀዩበት ወረርሽኝ ሆኗል፡፡ ወዳጆቼ ከኃጢአት ሁሉ ክፉ ኃጢአት አንድ ድርጊት ልማድ ሲሆን ነው፡፡ ልማድ ከሆነ ንስሐ፣ምክር፣ትምህርት በቀላሉ ላያላቅቁን ይችላሉ፡፡ ልማድ ከሆነ ደግሞ ድፍረት ይሆንና የድፍረት ኃጢአት ሆኖ ስንተገብረው ምንም ላይመስለን ይችላል፡፡ እንደ ዳዊት ‹‹የድፍረት ኃጢአት እንዳይገዛኛ ባሪያህን ጠብቅ፤የዚያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ፣ከታላቅም ኃጢአት እነጻለሁ›› ብለን ልንጸልይ ይገባል፡፡ /መዝ 19÷13/
ግለ ወሲብን ከአፈጻጸሙ አንጻር በአራት ከፍለን እናያቸዋልን፡፡ አንደኛ የደናግል ግለ ወሲብ ነው፡፡ ከላይ እንዳየነው በውስጣችን ያለው ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ ሩካቤ ብንፈጽም ድንግልናየን አጣለሁ ግን ደግሞ በፍትወት እሰቃያለሁ የሚሉትን ሰዎችን የሚያጠቃ ነው፡፡ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ለድንግልናቸው እንጂ ለቅድስናቸው ካለመጠንቀቅ ይፈጽሙታል፡፡ ይህም አንዳንዴ ሴቶቹ ግለ ወሲብን ለብቻቸው፣አልጋቸው ውስጥ በመሆን በእጃቸው አፍረታቸውንና የስሜት አካላቸውን በመነካካት ይፈጽሙታል፡፡
ወንዶቹ ደግሞ የከበረ እጃቸውን በመጠቀም ግለ ወሲብን ይፈጽማሉ፡፡ በዚህ ድርጊት ቅድስና እና ንጽሕና ይጠፋል፡፡ ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ ይህንን ጠባይ ከልጅነታቸው ጊዜ ጀምሮአጋጣሚ በማውረስ እስከ አሁን ሕይወታቸውን በማቃወስ የሚጫወትባቸው አሉ፡፡ የዚህ አንዱና ዋነኛው ችግር የተፈጥሮን ሩካቤ ሳያውቁ ግለ ወሲብን ማጣጣም ነገ በትዳር መሃል ባለው ሕገ ሩካቤ ጣዕም ይቸገራሉ፡፡ አጋንንቱም ይህንን በመጠቀም የተፈጥሮ ሩካቤ
ጣዕምን ያጠፋባቸዋል፡፡
ሁለተኛ የወጣቶች ግለ ወሲብ ነው፡፡ ይህም ወጣቶች በወሲብ ፊልም፣ በመጠጥ፣በሱስ እና በሌሎችም ነገሮች በመገፋፋት፣አጋንንት ተጨምሮበት የሚፈጽሙት ግለ ወሲብ ነው፡፡ ይህ አብዛኛውን ጊዜ ዓይነ ጥላ ሴቷን ከወንድ፣ወንዱን ከሴት አላስቀርብ እያለ የሚገረግርባቸው ወጣቶች የሚፈጽሙት ነው፡፡ እራሳቸውን ከተቃራኒ ጾታ በማራቅ ደስታን ለማግኘት ዓይነ ጥላቸው በግለ ወሲብ እንዲጠቁ እና እራሳቸውን እንዲደብቁ ያደርጋቸዋል፡፡እንዲሁም የፍትወት እሳት ድንገት ሲያቃጥላቸው ለማብረድ፣እርካታን ለማግኘት የሚያውቁትን ሰው በሕሊና በማሰብ፣በምስል በመከሰት ይፈጽማል፡፡
ሦስተኛው የባለ ትዳሮችና የእጮኛሞች ግለ ወሲብ ነው፡፡ ባል እና ሚስት፣እጮኛሞች በሥራ ምክንያት ሲራራቁ፣ሲጣሉ፣ሲኳረፉ፣ሲለያዩ የሚፈጽሙት ነው፡፡ ይህ ደግሞ አጋንንቱ የጸብ ወይም የጥል ጊዜያቸውን ለማስረዘም እና ሩካቤያቸውን ለማሰልቸት ይጠቀምበታል፡፡ አንዳንዴም ባለ ትዳሮች ከትዳራቸው ውጪ ያለን ሰው በሕሊና፣በምናብ በማሰብ ይፈጽሙታል፡፡ ይህ ድርጊት ደግሞ ከእውነተኛው ዝሙት ልዩነት የለውም፡፡
አራተኛ ሰዎች ሰይጣንን ያስለመዱት ግን ሰይጣን መልሶ የሚጫወትባቸው ግለ ወሲብ ነው፡፡ ይህም ሰይጣንና የእኛ አባቶች የማያውቁት በዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ የሚፈጸም ግለ ወሲብ ነው፡፡ አንደኛው በስካይ ፒ የሚፈጸም ግለ ወሲብ ነው፡፡ ከእውነተኛው ሩካቤ ብዙም የማይለይ ነው፡፡ እውነት የሚያስመስለው ሁለቱም እየተያዩ ስለሚፈጽሙ ደስታውና እርካታው የገሐዱን ሩካቤ ይመስላል፡፡ ሁለተኛው ሰይጣን የማያውቀው ግን እኛ ያስለመድነው ፎን ሴክስ እና ቻት ሴክስ የሚባል ነው፡፡ ስለ እውነት እናውራ ከተባለ ፎን ሴክስ፣ቻት ሴክስ እና በስካይ ፒ የሚፈጸም ግለ ወሲብ እኛ ሰይጣንን ያስለመድነው እንጂ እሱ እኛን ያስለመደን አይደለም፡፡ በተለይ ፎን እና ቻት ሴክስ ከምናውቃቸውና ከማናውቃቸው ሰዎች ጋር የሚፈጸም ስለሆነ እራስን በእግዚአብሔር ፊት ማርከስ እና መናቅ ካልሆነ በስተቀር በራሳችን የምናመጣው ጣጣ ነው፡፡
ተወዳጆች ሆይ ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ ውስጣችን ካለ ይህ ክፉ ድርጊት እንደ ኮሶ በመጣባት ለጸያፍ ሕይወት ይዳርገናል፡፡ የዚህ ድርጊት መጨረሻው ደናግሎች ድንግልናቸውን፣ቅድስናቸውን፣ንጽህናቸውን ያጎድፍባቸዋል፡፡ ወጣቶችንና ባለምከንያት ትዳሮችን ደግሞ ከተፈጥሮ ሩካቤ በማስፈንገጥ የሞራል ውድቀት ውስጥ ይከታቸዋል፡፡
ወዳጆቼ በግለ ወሲብ በተለይም በወንዶች ላይ ዘርን ያለቦታው ማፍሰስን ያስከትላል፡፡ ይህ ደግሞ ትልቅ ኃጢአት ነው፡፡ ላዘውም ኃጢአተ አውናን፡፡ ምናልባት ብዙዎች እርግዝናን ከመከላከል ጋር በማያያዝ የሚፈጽሙት ተግባር ነው፡፡ ነገር ግን ተግባረ አውናን በመሆኑ ያስቀጣል፡፡ የከበረውን የወንድ ዘር ያለ ቦታው ማፍሰ ተገቢ ስላልሆነ፡፡
ደስታ
ዘርን በግለ ወሲብ ማፍሰስ በወገባችን ያለን ልጅ በሚዳ ላይ እንደመጣል ነው፡፡ ሆን ተብሎ ዘርን ማፍሰስ ትልቅ ኃጢአት ነው፡፡ በግለ ወሲብ ጊዜ ዘርን ማፍሰስ የእርካታ ምልክት ቢሆንም በእኛ ውስጥ ማለትም በሚፈሰው ዘር ውስጥ ያሉት ልጆች ናቸው፡፡ የሚሳዝነው ወልደን ካሳደግናቸው ልጆች ዘርን ከማህጸን ውጪና በግለ ወሲብ በማፍሰሳችን የማናውቃቸው የበተናቸው ልጆች ይበልጣሉ፡፡
ወዳጆቼ የሰው ልጅ ዘር በእግዚአብሔር ዘንድ ክብር ነው፡፡ እግዚአብሔር ልጆችንአባቶቻችን በማህጸን ለመፍጠር የሚጠቀምበት አንዱ የሰው ልጅ ዘር ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ጥበብ የሚገለጥበትን የሰው ዘር ያለ ቦታው ማፍሰስ ተገቢ አይደለም፡፡ ይህን ድርጊት ‹‹ኃጢአተ አውናን›› በማለት ይገልጹታል፡፡
የይሁዳ ልጅ ዔር የሚባል ልጅ ነበረው፡፡ እሱም ትዕማር የምትባል ልጅ አግብቶ ይኖር ነበር፡፡ የይሁዳ ልጅ ዔር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ ክፉ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ዔርን ቀሰፈው ሞተም፡፡ ይሁዳም የዔርን ወንድም ልጁ አውናንን ‹‹ወደ ወንድምህ ሚስት ግባ፣አግባትም፣ለወንድህም ዘር አቁምለት›› አለው፡፡ አውናንም እንደ ወንድሙ ዔር ክፉ ነበርና ለወንድሙ ዘር እንዳይተካለት ከትዕማር ጋር ሩካቤ ሥጋ ሲፈጽም ዘሩን ከማህጸንዋ ውጪ በምድር ላይ ያፈሰው ነበር፡፡ በማህጸን ጽንስን የሚጠቀልለው እግዚአብሔር የአውናንን ተንኮልና ግፍ ተመለከተ፡፡ በአጸያፊ ድርጊቱ እግዚአብሔር አውናንን ቀሰፈው እንደ ወንድሙ ዔር ሞተ፡፡ /ዘፍውጪና 38÷6-10/
እግዚአብሔር በሐዲስ ኪዳን ንስሐን ባይሰጠን ኖሮ፣በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ባይታረቀን ኖሮ ዘርን ከማህጸን በግለ ወሲብ እያፈሰስን፣ዘርን ያለ ቦታው ስናውለው፣ስንጥለው እንደ አውናን በተቀሰፍን ነበር፡፡ ምህረቱ እና ቸርነቱ ይዞን ይኸው ከነ በደላችን አለን፡፡ በዓለማችን ላይ በሕይወት ካሉት የሰው ልጆች ይልቅ የመፈጠር ዕድል እያላቸው ግን ባልባሌ ቦታ በሚፈስ ዘር ልጆች የመሆናቸው እድል የተጨናገፉ ይበልጣሉ፡፡ ስለዚህ ስንት ጳጳሳት፣አገር መሪዎች፣ለወገንና ለአገር የሚጠቅሙትውልድ ሰዎች የሚሆኑትን ዘርን ያለ ቦታው በማፍሰስ ምክንያት እያጠፋን ስለሆነ ከዚህ ደርጊት ልንታቀብ ይገባል፡፡
ለዚህም ነው እኛን ያልተቀሰፈው እግዚአብሔር የታገሰው ያልኩት፡፡ ምክንያቱም አውናን ተፈጥሮአዊ ሩካቤን እየፈጸመ በተንኮሉ ዘሩን ከማሕጸን ውጪ ያፈስ ስለነበር ነው እግዚአብሔር የቀሰፈውና የሞተው፡፡ እኛ ግን ተፈጥሮአችን ባልሆነና ለባሕርያችን የማይስማማውን ግለ ወሲብን በእጃችን እየፈጸምን አለመቀሰፋችን እግዚአብሔር የንስሐ እድል እየሰጠንና ለንስሐ እያጨን መሆኑን ያስረዳል፡፡ ‹‹ኃጢአተኛው ከመንገዱ ተመልሶ በሕይወት ይኖር ዘንድ እንጂ ኃጢአተኛው ይሞት አልፈቅድ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ /ሕዝ 33÷11/
ተወዳጆች ሆይ ከዚህ ጸያፍ እና አጋንንታዊ ተግባር ለመላቀቅ ድርጊቱን የሚጸየፍ ሕሊና፣ለንስሐ የጀገነ ልቦና ያስፈልገናል፡፡ እንዲሁን ንስሐ፣ጾም፣ጸሎት በተለይም ስግደት ያስፈልገናል፡፡ በተረፈ መምህራንንና አባቶች ካህናትን በማማከር፣እግዚአብሔርን በመማጸን ከዚህ ሰይጣናዊ ተግባር ለመላቀቅ መሞከር ሳይሆን መተግበር አለብን፡፡ነገአችንን እባካችሁ በልጅነታችን የገባው ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ በግለ ወሲብ እንዳይጫወትብን፣ እንዳያበላሽብን፣ከወደደን በሞቱ ሕይወቱን ከሰጠን ከአምላካችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር እንዳያቆራርጠን አጋንንቱን ልንነቃበት ይገቃል፣ እስከ ዛሬ የተጫወተብን ይበቃል፡፡
ሁለተኛ የወጣቶች ግለ ወሲብ ነው፡፡ ይህም ወጣቶች በወሲብ ፊልም፣ በመጠጥ፣በሱስ እና በሌሎችም ነገሮች በመገፋፋት፣አጋንንት ተጨምሮበት የሚፈጽሙት ግለ ወሲብ ነው፡፡ ይህ አብዛኛውን ጊዜ ዓይነ ጥላ ሴቷን ከወንድ፣ወንዱን ከሴት አላስቀርብ እያለ የሚገረግርባቸው ወጣቶች የሚፈጽሙት ነው፡፡ እራሳቸውን ከተቃራኒ ጾታ በማራቅ ደስታን ለማግኘት ዓይነ ጥላቸው በግለ ወሲብ እንዲጠቁ እና እራሳቸውን እንዲደብቁ ያደርጋቸዋል፡፡እንዲሁም የፍትወት እሳት ድንገት ሲያቃጥላቸው ለማብረድ፣እርካታን ለማግኘት የሚያውቁትን ሰው በሕሊና በማሰብ፣በምስል በመከሰት ይፈጽማል፡፡
ሦስተኛው የባለ ትዳሮችና የእጮኛሞች ግለ ወሲብ ነው፡፡ ባል እና ሚስት፣እጮኛሞች በሥራ ምክንያት ሲራራቁ፣ሲጣሉ፣ሲኳረፉ፣ሲለያዩ የሚፈጽሙት ነው፡፡ ይህ ደግሞ አጋንንቱ የጸብ ወይም የጥል ጊዜያቸውን ለማስረዘም እና ሩካቤያቸውን ለማሰልቸት ይጠቀምበታል፡፡ አንዳንዴም ባለ ትዳሮች ከትዳራቸው ውጪ ያለን ሰው በሕሊና፣በምናብ በማሰብ ይፈጽሙታል፡፡ ይህ ድርጊት ደግሞ ከእውነተኛው ዝሙት ልዩነት የለውም፡፡
አራተኛ ሰዎች ሰይጣንን ያስለመዱት ግን ሰይጣን መልሶ የሚጫወትባቸው ግለ ወሲብ ነው፡፡ ይህም ሰይጣንና የእኛ አባቶች የማያውቁት በዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ የሚፈጸም ግለ ወሲብ ነው፡፡ አንደኛው በስካይ ፒ የሚፈጸም ግለ ወሲብ ነው፡፡ ከእውነተኛው ሩካቤ ብዙም የማይለይ ነው፡፡ እውነት የሚያስመስለው ሁለቱም እየተያዩ ስለሚፈጽሙ ደስታውና እርካታው የገሐዱን ሩካቤ ይመስላል፡፡ ሁለተኛው ሰይጣን የማያውቀው ግን እኛ ያስለመድነው ፎን ሴክስ እና ቻት ሴክስ የሚባል ነው፡፡ ስለ እውነት እናውራ ከተባለ ፎን ሴክስ፣ቻት ሴክስ እና በስካይ ፒ የሚፈጸም ግለ ወሲብ እኛ ሰይጣንን ያስለመድነው እንጂ እሱ እኛን ያስለመደን አይደለም፡፡ በተለይ ፎን እና ቻት ሴክስ ከምናውቃቸውና ከማናውቃቸው ሰዎች ጋር የሚፈጸም ስለሆነ እራስን በእግዚአብሔር ፊት ማርከስ እና መናቅ ካልሆነ በስተቀር በራሳችን የምናመጣው ጣጣ ነው፡፡
ተወዳጆች ሆይ ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ ውስጣችን ካለ ይህ ክፉ ድርጊት እንደ ኮሶ በመጣባት ለጸያፍ ሕይወት ይዳርገናል፡፡ የዚህ ድርጊት መጨረሻው ደናግሎች ድንግልናቸውን፣ቅድስናቸውን፣ንጽህናቸውን ያጎድፍባቸዋል፡፡ ወጣቶችንና ባለምከንያት ትዳሮችን ደግሞ ከተፈጥሮ ሩካቤ በማስፈንገጥ የሞራል ውድቀት ውስጥ ይከታቸዋል፡፡
ወዳጆቼ በግለ ወሲብ በተለይም በወንዶች ላይ ዘርን ያለቦታው ማፍሰስን ያስከትላል፡፡ ይህ ደግሞ ትልቅ ኃጢአት ነው፡፡ ላዘውም ኃጢአተ አውናን፡፡ ምናልባት ብዙዎች እርግዝናን ከመከላከል ጋር በማያያዝ የሚፈጽሙት ተግባር ነው፡፡ ነገር ግን ተግባረ አውናን በመሆኑ ያስቀጣል፡፡ የከበረውን የወንድ ዘር ያለ ቦታው ማፍሰ ተገቢ ስላልሆነ፡፡
ደስታ
ዘርን በግለ ወሲብ ማፍሰስ በወገባችን ያለን ልጅ በሚዳ ላይ እንደመጣል ነው፡፡ ሆን ተብሎ ዘርን ማፍሰስ ትልቅ ኃጢአት ነው፡፡ በግለ ወሲብ ጊዜ ዘርን ማፍሰስ የእርካታ ምልክት ቢሆንም በእኛ ውስጥ ማለትም በሚፈሰው ዘር ውስጥ ያሉት ልጆች ናቸው፡፡ የሚሳዝነው ወልደን ካሳደግናቸው ልጆች ዘርን ከማህጸን ውጪና በግለ ወሲብ በማፍሰሳችን የማናውቃቸው የበተናቸው ልጆች ይበልጣሉ፡፡
ወዳጆቼ የሰው ልጅ ዘር በእግዚአብሔር ዘንድ ክብር ነው፡፡ እግዚአብሔር ልጆችንአባቶቻችን በማህጸን ለመፍጠር የሚጠቀምበት አንዱ የሰው ልጅ ዘር ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ጥበብ የሚገለጥበትን የሰው ዘር ያለ ቦታው ማፍሰስ ተገቢ አይደለም፡፡ ይህን ድርጊት ‹‹ኃጢአተ አውናን›› በማለት ይገልጹታል፡፡
የይሁዳ ልጅ ዔር የሚባል ልጅ ነበረው፡፡ እሱም ትዕማር የምትባል ልጅ አግብቶ ይኖር ነበር፡፡ የይሁዳ ልጅ ዔር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ ክፉ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ዔርን ቀሰፈው ሞተም፡፡ ይሁዳም የዔርን ወንድም ልጁ አውናንን ‹‹ወደ ወንድምህ ሚስት ግባ፣አግባትም፣ለወንድህም ዘር አቁምለት›› አለው፡፡ አውናንም እንደ ወንድሙ ዔር ክፉ ነበርና ለወንድሙ ዘር እንዳይተካለት ከትዕማር ጋር ሩካቤ ሥጋ ሲፈጽም ዘሩን ከማህጸንዋ ውጪ በምድር ላይ ያፈሰው ነበር፡፡ በማህጸን ጽንስን የሚጠቀልለው እግዚአብሔር የአውናንን ተንኮልና ግፍ ተመለከተ፡፡ በአጸያፊ ድርጊቱ እግዚአብሔር አውናንን ቀሰፈው እንደ ወንድሙ ዔር ሞተ፡፡ /ዘፍውጪና 38÷6-10/
እግዚአብሔር በሐዲስ ኪዳን ንስሐን ባይሰጠን ኖሮ፣በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ባይታረቀን ኖሮ ዘርን ከማህጸን በግለ ወሲብ እያፈሰስን፣ዘርን ያለ ቦታው ስናውለው፣ስንጥለው እንደ አውናን በተቀሰፍን ነበር፡፡ ምህረቱ እና ቸርነቱ ይዞን ይኸው ከነ በደላችን አለን፡፡ በዓለማችን ላይ በሕይወት ካሉት የሰው ልጆች ይልቅ የመፈጠር ዕድል እያላቸው ግን ባልባሌ ቦታ በሚፈስ ዘር ልጆች የመሆናቸው እድል የተጨናገፉ ይበልጣሉ፡፡ ስለዚህ ስንት ጳጳሳት፣አገር መሪዎች፣ለወገንና ለአገር የሚጠቅሙትውልድ ሰዎች የሚሆኑትን ዘርን ያለ ቦታው በማፍሰስ ምክንያት እያጠፋን ስለሆነ ከዚህ ደርጊት ልንታቀብ ይገባል፡፡
ለዚህም ነው እኛን ያልተቀሰፈው እግዚአብሔር የታገሰው ያልኩት፡፡ ምክንያቱም አውናን ተፈጥሮአዊ ሩካቤን እየፈጸመ በተንኮሉ ዘሩን ከማሕጸን ውጪ ያፈስ ስለነበር ነው እግዚአብሔር የቀሰፈውና የሞተው፡፡ እኛ ግን ተፈጥሮአችን ባልሆነና ለባሕርያችን የማይስማማውን ግለ ወሲብን በእጃችን እየፈጸምን አለመቀሰፋችን እግዚአብሔር የንስሐ እድል እየሰጠንና ለንስሐ እያጨን መሆኑን ያስረዳል፡፡ ‹‹ኃጢአተኛው ከመንገዱ ተመልሶ በሕይወት ይኖር ዘንድ እንጂ ኃጢአተኛው ይሞት አልፈቅድ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ /ሕዝ 33÷11/
ተወዳጆች ሆይ ከዚህ ጸያፍ እና አጋንንታዊ ተግባር ለመላቀቅ ድርጊቱን የሚጸየፍ ሕሊና፣ለንስሐ የጀገነ ልቦና ያስፈልገናል፡፡ እንዲሁን ንስሐ፣ጾም፣ጸሎት በተለይም ስግደት ያስፈልገናል፡፡ በተረፈ መምህራንንና አባቶች ካህናትን በማማከር፣እግዚአብሔርን በመማጸን ከዚህ ሰይጣናዊ ተግባር ለመላቀቅ መሞከር ሳይሆን መተግበር አለብን፡፡ነገአችንን እባካችሁ በልጅነታችን የገባው ዓይነ ጥላና የዝሙት መንፈስ በግለ ወሲብ እንዳይጫወትብን፣ እንዳያበላሽብን፣ከወደደን በሞቱ ሕይወቱን ከሰጠን ከአምላካችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር እንዳያቆራርጠን አጋንንቱን ልንነቃበት ይገቃል፣ እስከ ዛሬ የተጫወተብን ይበቃል፡፡
ክፍል አሥራ ሰባት
የወሲብ ፊልም ማየት እና የዝሙት አጋንንት ጥንውት
/ፖርኖ ግራፊ፣ትውልድ አጥፊ/
/ከሰው ተደብቀን በእግዚአብሔር ፊት የምንሠራው ግልጥ ኃጢአት/
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ተወዳጆች ሆይ በክፍል አሥራ ስድስት ግብረ ሰዶምና ሌዝብያንነትን አጋንንት እንዴት እንደሚዋረሰን እንዴት እንደሚጠናወተን አይተናል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ የመንፈሳዊም የዓለማዊም ሰዎች አንገብጋቢ ችግር የሆነው የወሲብ ፊልም ማየት ጉዳቱንና ጣጣውን በዝርዝር እናያለን፡፡ እንደተለመደው ሐፍረትን ገፈፍ አድርገን፤ከችግሩ ጠንቅነት የተነሳ በግልጽ እንማማራለን፡፡ /ወዳጆቼ ያ መናጢ ‹‹ይህን ለምን ጻፍክ›› ብሎ ነው መሰለኝ ይህን ጽሑፍ ስጽፍላችሁ ከወትሮ በተለየ የገጠመኝ ፈተና በተለይም የጻፍኩት እየተሰወረብኝ፣እየጠፋብኝ፣ኮምፒውተሬም ያላመሏ ዝብርቅ እያለች፣እየበጠበጠች ነው የጻፍኩት፡፡ ለማንኛውም በጥሞና አንብቡ/
ተወዳጆች ሆይ ሕይወታችን በመንፈሳዊ መሠረት ላይ ተገንብቶ ስላላደግን ወደ ወጣትነት ስንጠጋ ለእኛም ለሰውም ግራ የሚያጋባ በጥፋት መንገድ መጓዝ እንጀምራለን፡፡ የመንፈሳዊ ሕይወት ባዶነታችን ግልጽ የሚሆነው፣አድገን የኃጢአት ስርጓጉጥ ውስጥ ስንገባ ነው፡፡ ሰው ጸያፍና ከሃይማኖት ሥርዓት ውጪ የሆኑ ድርጊቶችን ካላወቀ፣አውቆም ላለመተግበር ካልተጠነቀቀ ለአጋንንት የዓላማው ማስፈጸምያ ነው የሚሆነው፡፡
ወዳጆቼ በተለይ እኛ ባለንበት በዚህ በኢንተርኔት ዘመን ልቅ የሆኑ የወሲብ ቪድዎዮችን መመልከት የተለመደ ሆኗል፡፡ አስከፊ የሚያደርገው እግዚአብሔርን እናውቃለን፣ሕጉን እንተገብራለን፣መንፈሳዊ ነን የምንለው የዚህ ልምድና ሱስ ሰለባ መሆናችን ነው፡፡ ብዙዎች የወሲብ ቪድዎዮችን መመልከት ኃጢአት አይመስላቸውም፡፡ አንዳንዱ ‹‹አየሁ እንጂ አልፈጸምኩ›› ብሎ እራሱን ከሕሊና ወቀሳ ለማስመለጥ ይጥራል፡፡
ወዳጆቼ ልቅ የወሲን ፊልሞች ዛሬ የደረሱበት የጥፋት መንገድ ሳይደርሱ ሰይጣን እንዴት በሺህ ዓመታት ሠርቶ እዚህ እንዳሰረሰው ከታሪክ አንጻር እናያለን፡፡ ሰዎች ልቅ ወሲብን መፈጸም የጀመሩት በሮማን ኢምፓየር ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ3000 ዓመተ ዓለም በፊት ነው፡፡ ግን አገር አቀፍ የጥፋት ቅርጽ የያዘው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1500 ዓመተ ዓለም አከባቢ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ማስረጃው ዛሬም ድረስ በድንጋይ ላይ የተቀረጹ ምስሎች እና በራሱ በድንጋዩ ላይ ሙሉ ለሙሉ ግልጽ የሆነ በሰው አምሳል የተሠሩ ሐውልቶች አሉ፡፡
እንዲሁም ሮማውያን በመመገብያ የሸክላ ሰሐናቸው እና በሚጠቀሙት የተለያየ ቁሶቻቸው ላይ ወሲብን የሚገልጽ ስዕሎችን ይስሉ ነበር፡፡ ይህ ማስረጃ ዛሬም አለ፡፡ ልቅ ወሲብ በዚህ መልኩ እያደገ መጥቶ በመጨረሻ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ሕይወት ውስጥ ገባ፡፡ በተለይ ጥንታውያን ሮማዎች ባል ከሚስቱ ውጪ መማገጥ፣ኢ-ሩካቤ መፈጸም ሲፈልግ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ይሄዱ ነበር፡፡ ሴተኛ አዳሪዎቹ ወደ እነሱ የሚመጡትን ወንዶች ሚስቶቻቸውን እስኪጠሉ ድረስ በቅል ወሲብ ያጠምዷቸው ነበር፡፡ ሥርዓት አልባና ከተፈጥሮ ውጪ የሆነን ወሲብ የለመዱት ወንዶቹ ለሴተኛ አዳሪዎቹ እውቅና ሰጥዋቸው፤ሴቶቹም እንደ አንድ ሥራ ያዙት፡፡
በዚህ መልኩ የተስፋፋው ልቅ ወሲብ የፊልም ኢንዱስትሪ ሲመጣ በ1888 ዓ.ም በፈረንሳይ የፊልም ካምፓኒ በወንድ እና በሴት ቀለል ባለ መልኩ ተሠራ፡፡ በዚህ መልኩ የተጀመረው የወሲብ ቪዲዮ በሆሊዉድ ፊልሞች ላይ እራቁት ገላ ሆነው ግን አፍረት ሳይታይ ልቅም ሳይሆን በፊልሞቻቸው መሃል እንደ ቅመም ጣል እያደረጉ ያስገቡት ነበር፡፡ ይህም ሁለት ታዋቂ ተዋናዮች በፊልሙ የፍቅር ታሪክ ምክንያት የሚያደርጉት መሳሳም፣መተሻሸት፣መዳራት ብሎም ግንኑነትን ማድርግ ከፊልም የታሪክ ጭብጥ በላይ አጓጊ ነበር፡፡ እንዲህ እያለ ተለምዶ እራሱን ችሎ ‹‹ፖርኖ ግራፊ›› ተብሎ መስፋፋት ጀመረ፡፡
የወሲብ ፊልምን ፈረንሳይ ትጀምረው አሜሪካ ታስፋፋው እንጂ ቀድሞ በሕገ ወጥነቱ ብዙ አገሮች ይቃወሙት፣በአገራቸውም እንዳይታይ ይከለክሉት ነበር፡፡ በዓለም ላይ ለመጀመርያ ጊዜ የወሲብን ፊል በብሔራዊ ደረጃ ፈቅዳ ሕዝቦችዋ እንዲያዩ ያደረገቸው ዴንማርክ ናት፡፡ ዘመኑን በ1961 ዓ.ም ነበር፡፡
በመቀጠል አሜሪካ በሆሊውድ እጅጉን አስፋፋቸው፡፡ የወሲብ ፊልም እንደ ዛሬ በቢሊዮን ዶላር ገቢ ሳያስገኝ በፊት እጮኛሞች፣ባለት ትዳሮች፣ያረጡ ሴቶች፣በስንፈት የሚቸገሩ ወንዶች፣እድሜያቸው የገፉ አዛውንቶች እንደ ማነቃቅያ እንዲጠቀሙበት ታስቦ ነበር የተሠራው፡፡ በኃላ ግን እራሱን የቻለ ኮሜርሻን ኢንዱስትሪ ሆነ፡፡ በእኛም አገር አንዳንዱ የሥነ ልቦና በስንፈተ ሩካቤ ለሚቸገሩ ባለ ትዳሮች የወሲብን ፊልም እንዲመለከቱ እንደ መፍትሄ ይተቁማሉ፡፡ ከድጡ ወደ ማጡ ማለት ይህ ነው፡፡
በፈረንጆቹ በ2006 ዓ.ም በአሜሪካ በተደረገ ጥናት በወሲብ ፊልም ኢንዱስትሪ አሜሪካ 2.5 ቢሊዮን ዶላር አስገብታለች፡፡ ዜጎችዋን አጥፍታ ገንዘብ ትሰበስባለች፡፡ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ደግሞ 97 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ነበረው፡፡ ወዳጆቼ አሁን ኢንተርኔት እንደልብ በሆነበት በዚህ ጊዜ ትውልድን እያጠፉ ስንት ቢሊዮን ዶላር እንደሚሰበስቡ ሬሾውን መሥራት ነው፡፡ ዛሬ አገራት ሰዎች የልቅ ወሲብ ሱሰኛ እንዲሆኑ በቀላሉ በኢንተርኔት አማካኝነት እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡
ወደ መንፈሳዊ እይታችን ስንመጣ እግዚአብሔር ሩካቤ ሥጋን አክብሮ ባርኮ የሰጠን በአግባቡ እንድንጠቀምበት ነው፡፡ ይህ ደስታ የሚገኝበት፣ልጅ የሚጸነስበትና የሚወለድበት ሩካቤ ሥጋ የምሥጢር ተግባር ነው፡፡ ምንም ባልና ሚስት ቢሆኑ እንኳን ሩካቤን በግልጥ መፈጸም አይቻልም፡፡
ልቅ የወሲብ ፊልም መመልከት የዝሙት መንፈስ መነሐርያ መሆን ነው፡፡ ብዙዎች ‹‹ለመደብርያ ነው፣አንዳንድ ነገር ለማወቅ ነው፣ደስ ስለሚለኝ ነው›› በማለት የወሲብ ፊልም በመመልከት ዛሬ የማይወጡበት አዘቅት ውስጥ ገብተወዋል፡፡ ብዙዎች የወሲብ ፊልም በመመልከት ዘማዊ ሆነዋል፡፡ ድንግልናቸውን፣ቅድስናቸውን አጥተውበታል፡፡ ያየነውን በተግባር እንሞክረው ከሚል የፍትወት ጉጉት ያለ እድሜያቸው ዝሙት ፈጽመው ተበላሽተዋል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እንደ ገዛ ምኞታቸው ለራሳቸው አስተማሪዎችን ያከማቻሉ›› ያለው እንደዚህ ያለን ድርጊትን ነው፡፡ /2ኛ ጢሞ 4÷3/
ወዳጆቼ የወሲብ ፊልም ስንመለከት በተዘዋዋሪ ሳይሆን በቀጥታ የዝሙት መንፈስ ውስጣችን ይሰርጻል፡፡ ፍትወት ያቃጥለናል፡፡ በተግባር ፈጽም ፈጽም ያሰኘናል፡፡
ከላይ እንዳየነው የወሲብ ፊልም ማየት ለምን ኃጢአት እንዳልመሰለን አይገባኝም፡፡ ቆይ ፊልሙን ስናይ እኛም ከሚፈጽሙት ጋር ዋና ተዋናይ እንሆነ የለ እንዴ? ስናይስ በፍትወት ከራስ ጸጉራችን እስከ እግር ጥፍራችን እንቃጠል የለ እንዴ? ወዳጆቼ ለምሳሌ በአንድ ቪዲዮ ተከታታይነት ያለው አምስት የወሲብ ፊልም ካየን በሐሳባችን ከአምስቱም ጋር እናመነዝር የለ? መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመነዘረ›› ይላል /ማቴ 5÷28/ በዓይን ማየት፣በልብ መመኘት እንደ ዝሙት ከተቆጠረ፤በተግባር የሚፈጸመውን የወሲብ ፊልም እያየን በምኞት በፍትወት ስሜት እየተባበርንማ እንዴት አመንዝራነት አይሆንብንም?
የወሲብ ፊልም ማየት አንዱ ጣጣው በማየታችን እኛም አብረን ተዋናይ ስለምንሆን ወንዶቹም ሴቶቹም ለግለ ወሲብ እንጋለጣለን፡፡ ዛሬ በግለ ወሲብ እጅጉን የምንቸገረው የወሲብ ፊልም በማየታችን ልማድ ያደረግናቸው ውስጣችን ሰርጸው ነው፡፡ ብዙዎች የወሲብ ፊልምን ሲያዩ በፍትወት ስለሚቃጠሉ የፍትወት ስሜታቸውን ለማብረድ
የወሲብ ፊልም ማየት እና የዝሙት አጋንንት ጥንውት
/ፖርኖ ግራፊ፣ትውልድ አጥፊ/
/ከሰው ተደብቀን በእግዚአብሔር ፊት የምንሠራው ግልጥ ኃጢአት/
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ተወዳጆች ሆይ በክፍል አሥራ ስድስት ግብረ ሰዶምና ሌዝብያንነትን አጋንንት እንዴት እንደሚዋረሰን እንዴት እንደሚጠናወተን አይተናል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ የመንፈሳዊም የዓለማዊም ሰዎች አንገብጋቢ ችግር የሆነው የወሲብ ፊልም ማየት ጉዳቱንና ጣጣውን በዝርዝር እናያለን፡፡ እንደተለመደው ሐፍረትን ገፈፍ አድርገን፤ከችግሩ ጠንቅነት የተነሳ በግልጽ እንማማራለን፡፡ /ወዳጆቼ ያ መናጢ ‹‹ይህን ለምን ጻፍክ›› ብሎ ነው መሰለኝ ይህን ጽሑፍ ስጽፍላችሁ ከወትሮ በተለየ የገጠመኝ ፈተና በተለይም የጻፍኩት እየተሰወረብኝ፣እየጠፋብኝ፣ኮምፒውተሬም ያላመሏ ዝብርቅ እያለች፣እየበጠበጠች ነው የጻፍኩት፡፡ ለማንኛውም በጥሞና አንብቡ/
ተወዳጆች ሆይ ሕይወታችን በመንፈሳዊ መሠረት ላይ ተገንብቶ ስላላደግን ወደ ወጣትነት ስንጠጋ ለእኛም ለሰውም ግራ የሚያጋባ በጥፋት መንገድ መጓዝ እንጀምራለን፡፡ የመንፈሳዊ ሕይወት ባዶነታችን ግልጽ የሚሆነው፣አድገን የኃጢአት ስርጓጉጥ ውስጥ ስንገባ ነው፡፡ ሰው ጸያፍና ከሃይማኖት ሥርዓት ውጪ የሆኑ ድርጊቶችን ካላወቀ፣አውቆም ላለመተግበር ካልተጠነቀቀ ለአጋንንት የዓላማው ማስፈጸምያ ነው የሚሆነው፡፡
ወዳጆቼ በተለይ እኛ ባለንበት በዚህ በኢንተርኔት ዘመን ልቅ የሆኑ የወሲብ ቪድዎዮችን መመልከት የተለመደ ሆኗል፡፡ አስከፊ የሚያደርገው እግዚአብሔርን እናውቃለን፣ሕጉን እንተገብራለን፣መንፈሳዊ ነን የምንለው የዚህ ልምድና ሱስ ሰለባ መሆናችን ነው፡፡ ብዙዎች የወሲብ ቪድዎዮችን መመልከት ኃጢአት አይመስላቸውም፡፡ አንዳንዱ ‹‹አየሁ እንጂ አልፈጸምኩ›› ብሎ እራሱን ከሕሊና ወቀሳ ለማስመለጥ ይጥራል፡፡
ወዳጆቼ ልቅ የወሲን ፊልሞች ዛሬ የደረሱበት የጥፋት መንገድ ሳይደርሱ ሰይጣን እንዴት በሺህ ዓመታት ሠርቶ እዚህ እንዳሰረሰው ከታሪክ አንጻር እናያለን፡፡ ሰዎች ልቅ ወሲብን መፈጸም የጀመሩት በሮማን ኢምፓየር ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ3000 ዓመተ ዓለም በፊት ነው፡፡ ግን አገር አቀፍ የጥፋት ቅርጽ የያዘው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1500 ዓመተ ዓለም አከባቢ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ማስረጃው ዛሬም ድረስ በድንጋይ ላይ የተቀረጹ ምስሎች እና በራሱ በድንጋዩ ላይ ሙሉ ለሙሉ ግልጽ የሆነ በሰው አምሳል የተሠሩ ሐውልቶች አሉ፡፡
እንዲሁም ሮማውያን በመመገብያ የሸክላ ሰሐናቸው እና በሚጠቀሙት የተለያየ ቁሶቻቸው ላይ ወሲብን የሚገልጽ ስዕሎችን ይስሉ ነበር፡፡ ይህ ማስረጃ ዛሬም አለ፡፡ ልቅ ወሲብ በዚህ መልኩ እያደገ መጥቶ በመጨረሻ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ሕይወት ውስጥ ገባ፡፡ በተለይ ጥንታውያን ሮማዎች ባል ከሚስቱ ውጪ መማገጥ፣ኢ-ሩካቤ መፈጸም ሲፈልግ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ይሄዱ ነበር፡፡ ሴተኛ አዳሪዎቹ ወደ እነሱ የሚመጡትን ወንዶች ሚስቶቻቸውን እስኪጠሉ ድረስ በቅል ወሲብ ያጠምዷቸው ነበር፡፡ ሥርዓት አልባና ከተፈጥሮ ውጪ የሆነን ወሲብ የለመዱት ወንዶቹ ለሴተኛ አዳሪዎቹ እውቅና ሰጥዋቸው፤ሴቶቹም እንደ አንድ ሥራ ያዙት፡፡
በዚህ መልኩ የተስፋፋው ልቅ ወሲብ የፊልም ኢንዱስትሪ ሲመጣ በ1888 ዓ.ም በፈረንሳይ የፊልም ካምፓኒ በወንድ እና በሴት ቀለል ባለ መልኩ ተሠራ፡፡ በዚህ መልኩ የተጀመረው የወሲብ ቪዲዮ በሆሊዉድ ፊልሞች ላይ እራቁት ገላ ሆነው ግን አፍረት ሳይታይ ልቅም ሳይሆን በፊልሞቻቸው መሃል እንደ ቅመም ጣል እያደረጉ ያስገቡት ነበር፡፡ ይህም ሁለት ታዋቂ ተዋናዮች በፊልሙ የፍቅር ታሪክ ምክንያት የሚያደርጉት መሳሳም፣መተሻሸት፣መዳራት ብሎም ግንኑነትን ማድርግ ከፊልም የታሪክ ጭብጥ በላይ አጓጊ ነበር፡፡ እንዲህ እያለ ተለምዶ እራሱን ችሎ ‹‹ፖርኖ ግራፊ›› ተብሎ መስፋፋት ጀመረ፡፡
የወሲብ ፊልምን ፈረንሳይ ትጀምረው አሜሪካ ታስፋፋው እንጂ ቀድሞ በሕገ ወጥነቱ ብዙ አገሮች ይቃወሙት፣በአገራቸውም እንዳይታይ ይከለክሉት ነበር፡፡ በዓለም ላይ ለመጀመርያ ጊዜ የወሲብን ፊል በብሔራዊ ደረጃ ፈቅዳ ሕዝቦችዋ እንዲያዩ ያደረገቸው ዴንማርክ ናት፡፡ ዘመኑን በ1961 ዓ.ም ነበር፡፡
በመቀጠል አሜሪካ በሆሊውድ እጅጉን አስፋፋቸው፡፡ የወሲብ ፊልም እንደ ዛሬ በቢሊዮን ዶላር ገቢ ሳያስገኝ በፊት እጮኛሞች፣ባለት ትዳሮች፣ያረጡ ሴቶች፣በስንፈት የሚቸገሩ ወንዶች፣እድሜያቸው የገፉ አዛውንቶች እንደ ማነቃቅያ እንዲጠቀሙበት ታስቦ ነበር የተሠራው፡፡ በኃላ ግን እራሱን የቻለ ኮሜርሻን ኢንዱስትሪ ሆነ፡፡ በእኛም አገር አንዳንዱ የሥነ ልቦና በስንፈተ ሩካቤ ለሚቸገሩ ባለ ትዳሮች የወሲብን ፊልም እንዲመለከቱ እንደ መፍትሄ ይተቁማሉ፡፡ ከድጡ ወደ ማጡ ማለት ይህ ነው፡፡
በፈረንጆቹ በ2006 ዓ.ም በአሜሪካ በተደረገ ጥናት በወሲብ ፊልም ኢንዱስትሪ አሜሪካ 2.5 ቢሊዮን ዶላር አስገብታለች፡፡ ዜጎችዋን አጥፍታ ገንዘብ ትሰበስባለች፡፡ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ደግሞ 97 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ነበረው፡፡ ወዳጆቼ አሁን ኢንተርኔት እንደልብ በሆነበት በዚህ ጊዜ ትውልድን እያጠፉ ስንት ቢሊዮን ዶላር እንደሚሰበስቡ ሬሾውን መሥራት ነው፡፡ ዛሬ አገራት ሰዎች የልቅ ወሲብ ሱሰኛ እንዲሆኑ በቀላሉ በኢንተርኔት አማካኝነት እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡
ወደ መንፈሳዊ እይታችን ስንመጣ እግዚአብሔር ሩካቤ ሥጋን አክብሮ ባርኮ የሰጠን በአግባቡ እንድንጠቀምበት ነው፡፡ ይህ ደስታ የሚገኝበት፣ልጅ የሚጸነስበትና የሚወለድበት ሩካቤ ሥጋ የምሥጢር ተግባር ነው፡፡ ምንም ባልና ሚስት ቢሆኑ እንኳን ሩካቤን በግልጥ መፈጸም አይቻልም፡፡
ልቅ የወሲብ ፊልም መመልከት የዝሙት መንፈስ መነሐርያ መሆን ነው፡፡ ብዙዎች ‹‹ለመደብርያ ነው፣አንዳንድ ነገር ለማወቅ ነው፣ደስ ስለሚለኝ ነው›› በማለት የወሲብ ፊልም በመመልከት ዛሬ የማይወጡበት አዘቅት ውስጥ ገብተወዋል፡፡ ብዙዎች የወሲብ ፊልም በመመልከት ዘማዊ ሆነዋል፡፡ ድንግልናቸውን፣ቅድስናቸውን አጥተውበታል፡፡ ያየነውን በተግባር እንሞክረው ከሚል የፍትወት ጉጉት ያለ እድሜያቸው ዝሙት ፈጽመው ተበላሽተዋል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እንደ ገዛ ምኞታቸው ለራሳቸው አስተማሪዎችን ያከማቻሉ›› ያለው እንደዚህ ያለን ድርጊትን ነው፡፡ /2ኛ ጢሞ 4÷3/
ወዳጆቼ የወሲብ ፊልም ስንመለከት በተዘዋዋሪ ሳይሆን በቀጥታ የዝሙት መንፈስ ውስጣችን ይሰርጻል፡፡ ፍትወት ያቃጥለናል፡፡ በተግባር ፈጽም ፈጽም ያሰኘናል፡፡
ከላይ እንዳየነው የወሲብ ፊልም ማየት ለምን ኃጢአት እንዳልመሰለን አይገባኝም፡፡ ቆይ ፊልሙን ስናይ እኛም ከሚፈጽሙት ጋር ዋና ተዋናይ እንሆነ የለ እንዴ? ስናይስ በፍትወት ከራስ ጸጉራችን እስከ እግር ጥፍራችን እንቃጠል የለ እንዴ? ወዳጆቼ ለምሳሌ በአንድ ቪዲዮ ተከታታይነት ያለው አምስት የወሲብ ፊልም ካየን በሐሳባችን ከአምስቱም ጋር እናመነዝር የለ? መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመነዘረ›› ይላል /ማቴ 5÷28/ በዓይን ማየት፣በልብ መመኘት እንደ ዝሙት ከተቆጠረ፤በተግባር የሚፈጸመውን የወሲብ ፊልም እያየን በምኞት በፍትወት ስሜት እየተባበርንማ እንዴት አመንዝራነት አይሆንብንም?
የወሲብ ፊልም ማየት አንዱ ጣጣው በማየታችን እኛም አብረን ተዋናይ ስለምንሆን ወንዶቹም ሴቶቹም ለግለ ወሲብ እንጋለጣለን፡፡ ዛሬ በግለ ወሲብ እጅጉን የምንቸገረው የወሲብ ፊልም በማየታችን ልማድ ያደረግናቸው ውስጣችን ሰርጸው ነው፡፡ ብዙዎች የወሲብ ፊልምን ሲያዩ በፍትወት ስለሚቃጠሉ የፍትወት ስሜታቸውን ለማብረድ
ግለ ወሲብን በመፈጸም ወንዶች የከበረ ዘራቸውን ያፈሳሉ፣ሴቶች በእጃቸው አፍረታቸውን በመነካካት ደስታን ለማግኘት ሲሉ ግለ ወሲብን ይፈጽማሉ፡፡ በተለይ ሴቶች በሕብረት ሆነው የወሲብ ፊልም ሲያዩ በፍትወት በመቃጠላቸው የተመሳሳይ ጾታን ውሳቤ ይፈጽማሉ፡፡ በዚህ መልኩ የገባው አጋንንት በፍትወት በመጠናወት የወሲብ ፊልምና የግለ ወሲብ ሱሰኛ ያደረገናል፡፡
ወዳጆቼ አሁን ባለው ሁኔታ በዓለማችን ላይ ግብረ ሰዶም እና አስገድዶ መድፈርን በአሳዛኝ ሁኔታ እንዲስፋፋ ያደረገው የወሲብ ፊልም ተጽእኖ ነው፡፡ አንዳንዶች የወሲብ ፊልም አይተው ያየነውትን በተግባር ልፈጽም ልይ ከማለት ጉጉት የተነሳ ከሥጋ ዘመዳቸው ጋር፣ከሕፃናት ጋር፣ወንዶቹ ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር፣ሴቶቹ ከወንደኛ አዳሪዎች ጋር ኢ-ሩካቤ በመፈጸማቸው የማይወጡት የሕይወት አዘቅት ውስጥ ገብተዋል፡፡
የዛሬ 20 ዓመት ሰዎች ዝሙትን ለመፈጸም ተጣማሪያቸውን ፍለጋ ሄደው ነው የሚዘሙቱት፡፡ ዛሬ ግን ዝሙቱን ሳንፈለገው በእጃችን፣በስልካችን ላይ ነው ያለው፡፡ ዝሙቱ በኢንተርኔት አማካኝነት እጃችንና እቤታችን ድረስ መጥቶልናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹እሳት እና ወኃ አቅርቤልሃለሁ እጅህን ወደ ፈቀድከው ስደድ›› ነው ያለው፡፡ ስለዚህ እሳቱም ውኃውም በእጃችን ላይ ስለላ የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ የወሲብ ፊልም በየቀኑ የምናይ ከሆነ በየቀኑ ከማናውቃቸው ግን በፊልም ከምናያቸው ሰዎች ጋር ዝሙት እየፈጸምን ነው፡፡ ውስጣችን የገባው ዓይነ ጥላ ደግሞ የማንላቀቀው የማንተወው ሱስ ያደርግብናል፡፡
ብዙዎች ልብ የማይሉትን ግን የሚገቸገሩትን ነገር እናንሳ፡፡ ‹‹ጸበል መጠመቅ ስጀምር፣ማስቀደስ ስጀምር፣ቤተክርስትያን መሄድ ስጀምር ሕልመ ሌሊት ይመታኛል›› ይላሉ፡፡ በእርግጥም ሕልመ ሌሊት ክፉኛ ይፈትናቸዋል፡፡ ግን በሕልመ ሌሊት የተመሰለው የዝሙት አጋንንት ገና ድሮ የወሲብ ፊልም ሲያዩ መግባቱን አያውቁም፡፡ የወሲብ ፊልም ሲያዩ የተጠናወታቸው የዝሙት መንፈስ አድፍጦ ይቀመጥና ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ሲመለሱ ሌሊት ወንዱን በሴት፣ሴቷን በወንድ እየተመሰለ በሕልመ ሌሊት ይጥላቸዋል፡፡ በዚህም መንነፈሳዊ ተግባራትን ማከናወን ይቸገራሉ፡፡ የወሲብ ፊልም በማየት ያግበሰበስናቸው የዝሙት አጋንንቶች ወደ ቅድስና ሕይወት ስንገባ ስለማይመቻቸው፣ጾም ጸሎቱ ጸበሉ፣ቅዳሴው ስለሚቃጥላቸው ከዚህ ለማምለጥ በሕልመ ሌሊት ሌሊት መፈጥፈጥ ይጀምራሉ፡፡
አንዳንዱን መንፈሱ በመንፈሳዊ ቦታም ይፈትነዋል፡፡ ያየናቸውን ሰዎች ገና በቅጡ ሳናውቃቸው፣ሳንግባባቸው በፍትወት የምንመኛቸው አንዱም በዚህ ሳብያ ውስጣችን የገባው መንፈስ እራሱን ሲገልጥ የምናየው ምልክት ነው፡፡ ብዙዎቻችን በጸሎት ሰዓት በዝሙት ምስል ከሳች ሐሳቦች የምንሰቃየው ያኔ ውስጣችን ያስገባነው መንፈስ ሲዋጋን ነው፡፡ የወሲብ ፊልም አንዱ ጎጂ ጎኑ እኛ ማየቱን ህርም ብለን፣ንስሐ ገብተን ብንተወውም ምስሉ፣ትእይንቱ በአጋንንቱ ምክንያት ውስጣችን ስለቀረ፣በጸሎት ሰዓት ፊታችን ድቅን እያለ እጅጉን ይፈትነናል፡፡
የወሲብ ፊልም መመልከት ሌላ ጠንቁ ከሃይማኖታችን ሥርዓት፣ከባህላችንንና ከትውፊታችን ጋር የማይጣጣሙ ኢ-ሩካቤን እንድናውቅና እንድንፈጽም ያደርጉናል፡፡ ዛሬ የአንዳንድ እጮኛሞች እና የባለትዳሮች የሩካቤ ጠብ ‹‹እንደ ፊልሙ ሁኚልኝ›› ከሚል መነሻም ነው፡፡ የምዕራባውያንን ነውር፣በትዳራቸው ላይ ለመተግበር ይሞክራሉ፡፡ በዚህ ጸያፍ ድርጊት የእርግማንን ዘር እንወልዳለን፡፡ ለእኛም ለአገርም የማይበጁ ልጆችን እናፈራበታለን፡፡
የወሲብ ፊልም ባለ ትዳሮችን አፋቷል፡፡ ኢ-ሩካቤን አምጥቷል፡፡ ግብረ ሰዶምን አስፋፍቷል፡፡ ግለ ወሲብን አጠናውቷል፡፡ አስገድዶ መድፈርን አስከትሏል፡፡ ለዘማዊነት ሕይወት ዳርጓል፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ወጣቱን የዝሙት መንፈስ እያጠናወተው፣ወደ ዝሙት ሕይወት እየከተተው ያለው የወሲብ ፊልም መመልከት ነው፡፡
ወዳጆቼ ምዕራባውያን በወሲብ ፊልማቸው ላይ በተለይ የሴትን ልጅ ክብር ሲያጎድፉ፣ሲያቃልሏቸው፣የጸያፍ ስሜት መወጫ ሲያደርጓቸው ይታያል፡፡ የወንዱን የበላይነት የሚያሳዩበት፣ሴቷን የሚያዋርዱበት ትውልድ ማጥፊያ መሣሪያቸው ነው፡፡ እኛ ደግሞ የእነሱ የጥፋት መሣሪያና ማስፈጸሚያ መሆን የለብንም፡፡ እጅግ የሚያሳዝነው ፈረንጆቹ የወሲብ ፊልም የሚሰሩትን ‹‹ፖርን ስታር›› ብለው ቢሰይሟቸውም በተለይ ሴቶቹ ፊልሙን ከሠሩ በኋላ ደስተኛ እንዳልሆኑና ለጭንቀት እና ለድብርት በሽታ እንደሚጋለጡ በጥናት ተረጓግጧል፡፡ ስለዚህ በፊልሙ ላይ ለትወና የሚያሳዩት ውሸት እና የጥፋት ደስታ እውነት እንዳይመስላችሁ፡፡ በሺ የሚቆጠር ዶላር ስለሚከፈላቸው ሁኑ እንደተባሉት ነው የሚሆኑት፡፡ ከፊልሙ ቀረጻ በኋላ ግን በማህበረሰባቸው የተጠሉና እጅጉን የተናቁ ይሆናሉ፡፡ አንዳንዶቹም እራሳቸውን ያጠፋሉ፡፡
ወደድንም ጠላንም የወሲብ ፊልም እያየን ገና ለገና ‹‹እኔ አልፈጽመውም›› እያልን ብንመለከት ቅድስናችንን እናጎድፋለን፡፡ ባንፈጽምም በስሜት ተባባሪነታችን፣በፍትወት በመቃጠላችን በሐልዮ ኃጢአት እንወድቃለን፡፡ ይሁዳ በመልእክቱ ‹‹በመጨረሻው ዘመን በኃጢአተኝነት እንደ ገዛ ምኞታቸው እየሄዱ ዘባቾች ይሆናሉ›› ያለው የወሲብ ፊልም በማየት በኃጢአት እግዚአብሔር ላይ ለመዘበት የምንሞክረውን እኛንም ነው፡፡ /ይሁ 1÷18/
ወዳጆቼ በዚህ ችግር የተጠቃነው ሰዎች ‹‹ከዚህ አስከፊ ችግር እንዴት እንላቀቅ›› የሚለው ዋና ጉዳያችን ነው፡፡ በነገራችን ላይ የወሲብ ፊልም በማየት ሱስ የተጠቁት በምዕራባውያን ዘንድ እንደ አንድ ትልቅ በሽተኛ ነው የሚታዩት፡፡ ምክንያቱም በወሲብ ፊልም የሚያዩት ነገር ማህበራዊ ሕይወታቸው፣የግል ሕይወታቸው፣የትዳር ሕይወታቸው ይበላሻል፡፡ ስለዚህ ከዚህ ሲስ ለመላቀቅ የረጅም ጊዜ ምናልባትም ዓመት የሚፈጅ የሥነ-ልቦና ህክምና ይሰጥዋቸዋል፡፡
ወደ እኛ ስንመጣ ግን የዝሙት አጋንንቱ ነው ውስጣችን በመግባት ሱስ የሚያደርግብን፡፡ ይህም አጋንንቱን ይጠቅመዋል፡፡ አንደኛ ዘማዊ ያደርገናል፡፡ ሁለተኛ የኢ-ሩካቤ ሱሰኛ ያደርገናል፡፡ ሶስተኛ ግለ ወሲብን ያጠናውተናል፡፡ አራተኛ ግብረ ሰዶማዊ ያደርገናል፡፡ አምስተኛ በትዳር ላይ እንድንማግጥ ያደርገናል፡፡ ስድስተኛ ሰላማዊ የትዳር ሩካቤያችንን ይረብሽብናል፡፡ ሰባተኛ ቅድስናን ከእኛ ያርቃል፡፡ ስምንተኛ ከእግዚአብሔር ያጣላናል ያቆራርጠናል፣በጸያፍ ግብራችን እንድንጠላ ያደርገናል፡፡ ዘጠነኛ አራሱን የቻለ አንድ በሽታ ይሆንብናል፡፡ አሥረኛ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ትልቅ እንቅፋት ይሆንብናል፡፡
ስለዚህ ከዚህ ሱስ ለመላቀቅ በመጀመሪያ የአጋንንት የጥፋት ስልት መሆኑንና እኛን ለማነላሸት የተሠራ ሰይጣናዊ ሥራ መሆኑን ልናውቅ ይገባል፡፡ እንዲሁን ንስሐ በመግባት በጾም፣በጸሎት፣በስግደት በመበርታት በዚህ ሱስ የተጠናወተንን የዝሙት አጋንንት ለማራቅ፣ለመላቀቅ መጣር አለብን፡፡ በተለይ ሰው እግዚአብሔር ካልረዳው ምንም ማድረግ ስለማይችል ከዚህ ጸያፍ ችግር እንዲገላግለን ወደ ፈጣሪያችን መጮህ ይገባናል፡፡ በእርግጥ የወሲብ ፊልሞች በስልካችን አፖች ላይ ይዘን ስለምንዞር ላለማየት ከራሳችን ጋር ቃል ልንገባና በማየት ከእግዚአብሔር ጋር እንዳንጣላ የምናይበትን አማራጮች አለመጠቀም ነው፡፡ በተረፈ አምላከ ቅዱሳን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡
‹‹ለምኞት እንዳትታዘዙ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አይንገሥ›› ሮሜ 6÷12
አንብበው ሲጨርሱ እንደተለመደው ለወዳጆ ያዳርሱ!
ክፍል አሥራ ስምንት
እንጸልያለን፣እንጾማለን፣ጸበል እንጠመቃለን ስለዚህ ዓይነ ጥላ የለብኝም ማለት እንችላለን?
ዓይነ ጥላው ከሌለ ታድያ
ወዳጆቼ አሁን ባለው ሁኔታ በዓለማችን ላይ ግብረ ሰዶም እና አስገድዶ መድፈርን በአሳዛኝ ሁኔታ እንዲስፋፋ ያደረገው የወሲብ ፊልም ተጽእኖ ነው፡፡ አንዳንዶች የወሲብ ፊልም አይተው ያየነውትን በተግባር ልፈጽም ልይ ከማለት ጉጉት የተነሳ ከሥጋ ዘመዳቸው ጋር፣ከሕፃናት ጋር፣ወንዶቹ ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር፣ሴቶቹ ከወንደኛ አዳሪዎች ጋር ኢ-ሩካቤ በመፈጸማቸው የማይወጡት የሕይወት አዘቅት ውስጥ ገብተዋል፡፡
የዛሬ 20 ዓመት ሰዎች ዝሙትን ለመፈጸም ተጣማሪያቸውን ፍለጋ ሄደው ነው የሚዘሙቱት፡፡ ዛሬ ግን ዝሙቱን ሳንፈለገው በእጃችን፣በስልካችን ላይ ነው ያለው፡፡ ዝሙቱ በኢንተርኔት አማካኝነት እጃችንና እቤታችን ድረስ መጥቶልናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹እሳት እና ወኃ አቅርቤልሃለሁ እጅህን ወደ ፈቀድከው ስደድ›› ነው ያለው፡፡ ስለዚህ እሳቱም ውኃውም በእጃችን ላይ ስለላ የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ የወሲብ ፊልም በየቀኑ የምናይ ከሆነ በየቀኑ ከማናውቃቸው ግን በፊልም ከምናያቸው ሰዎች ጋር ዝሙት እየፈጸምን ነው፡፡ ውስጣችን የገባው ዓይነ ጥላ ደግሞ የማንላቀቀው የማንተወው ሱስ ያደርግብናል፡፡
ብዙዎች ልብ የማይሉትን ግን የሚገቸገሩትን ነገር እናንሳ፡፡ ‹‹ጸበል መጠመቅ ስጀምር፣ማስቀደስ ስጀምር፣ቤተክርስትያን መሄድ ስጀምር ሕልመ ሌሊት ይመታኛል›› ይላሉ፡፡ በእርግጥም ሕልመ ሌሊት ክፉኛ ይፈትናቸዋል፡፡ ግን በሕልመ ሌሊት የተመሰለው የዝሙት አጋንንት ገና ድሮ የወሲብ ፊልም ሲያዩ መግባቱን አያውቁም፡፡ የወሲብ ፊልም ሲያዩ የተጠናወታቸው የዝሙት መንፈስ አድፍጦ ይቀመጥና ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ሲመለሱ ሌሊት ወንዱን በሴት፣ሴቷን በወንድ እየተመሰለ በሕልመ ሌሊት ይጥላቸዋል፡፡ በዚህም መንነፈሳዊ ተግባራትን ማከናወን ይቸገራሉ፡፡ የወሲብ ፊልም በማየት ያግበሰበስናቸው የዝሙት አጋንንቶች ወደ ቅድስና ሕይወት ስንገባ ስለማይመቻቸው፣ጾም ጸሎቱ ጸበሉ፣ቅዳሴው ስለሚቃጥላቸው ከዚህ ለማምለጥ በሕልመ ሌሊት ሌሊት መፈጥፈጥ ይጀምራሉ፡፡
አንዳንዱን መንፈሱ በመንፈሳዊ ቦታም ይፈትነዋል፡፡ ያየናቸውን ሰዎች ገና በቅጡ ሳናውቃቸው፣ሳንግባባቸው በፍትወት የምንመኛቸው አንዱም በዚህ ሳብያ ውስጣችን የገባው መንፈስ እራሱን ሲገልጥ የምናየው ምልክት ነው፡፡ ብዙዎቻችን በጸሎት ሰዓት በዝሙት ምስል ከሳች ሐሳቦች የምንሰቃየው ያኔ ውስጣችን ያስገባነው መንፈስ ሲዋጋን ነው፡፡ የወሲብ ፊልም አንዱ ጎጂ ጎኑ እኛ ማየቱን ህርም ብለን፣ንስሐ ገብተን ብንተወውም ምስሉ፣ትእይንቱ በአጋንንቱ ምክንያት ውስጣችን ስለቀረ፣በጸሎት ሰዓት ፊታችን ድቅን እያለ እጅጉን ይፈትነናል፡፡
የወሲብ ፊልም መመልከት ሌላ ጠንቁ ከሃይማኖታችን ሥርዓት፣ከባህላችንንና ከትውፊታችን ጋር የማይጣጣሙ ኢ-ሩካቤን እንድናውቅና እንድንፈጽም ያደርጉናል፡፡ ዛሬ የአንዳንድ እጮኛሞች እና የባለትዳሮች የሩካቤ ጠብ ‹‹እንደ ፊልሙ ሁኚልኝ›› ከሚል መነሻም ነው፡፡ የምዕራባውያንን ነውር፣በትዳራቸው ላይ ለመተግበር ይሞክራሉ፡፡ በዚህ ጸያፍ ድርጊት የእርግማንን ዘር እንወልዳለን፡፡ ለእኛም ለአገርም የማይበጁ ልጆችን እናፈራበታለን፡፡
የወሲብ ፊልም ባለ ትዳሮችን አፋቷል፡፡ ኢ-ሩካቤን አምጥቷል፡፡ ግብረ ሰዶምን አስፋፍቷል፡፡ ግለ ወሲብን አጠናውቷል፡፡ አስገድዶ መድፈርን አስከትሏል፡፡ ለዘማዊነት ሕይወት ዳርጓል፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ወጣቱን የዝሙት መንፈስ እያጠናወተው፣ወደ ዝሙት ሕይወት እየከተተው ያለው የወሲብ ፊልም መመልከት ነው፡፡
ወዳጆቼ ምዕራባውያን በወሲብ ፊልማቸው ላይ በተለይ የሴትን ልጅ ክብር ሲያጎድፉ፣ሲያቃልሏቸው፣የጸያፍ ስሜት መወጫ ሲያደርጓቸው ይታያል፡፡ የወንዱን የበላይነት የሚያሳዩበት፣ሴቷን የሚያዋርዱበት ትውልድ ማጥፊያ መሣሪያቸው ነው፡፡ እኛ ደግሞ የእነሱ የጥፋት መሣሪያና ማስፈጸሚያ መሆን የለብንም፡፡ እጅግ የሚያሳዝነው ፈረንጆቹ የወሲብ ፊልም የሚሰሩትን ‹‹ፖርን ስታር›› ብለው ቢሰይሟቸውም በተለይ ሴቶቹ ፊልሙን ከሠሩ በኋላ ደስተኛ እንዳልሆኑና ለጭንቀት እና ለድብርት በሽታ እንደሚጋለጡ በጥናት ተረጓግጧል፡፡ ስለዚህ በፊልሙ ላይ ለትወና የሚያሳዩት ውሸት እና የጥፋት ደስታ እውነት እንዳይመስላችሁ፡፡ በሺ የሚቆጠር ዶላር ስለሚከፈላቸው ሁኑ እንደተባሉት ነው የሚሆኑት፡፡ ከፊልሙ ቀረጻ በኋላ ግን በማህበረሰባቸው የተጠሉና እጅጉን የተናቁ ይሆናሉ፡፡ አንዳንዶቹም እራሳቸውን ያጠፋሉ፡፡
ወደድንም ጠላንም የወሲብ ፊልም እያየን ገና ለገና ‹‹እኔ አልፈጽመውም›› እያልን ብንመለከት ቅድስናችንን እናጎድፋለን፡፡ ባንፈጽምም በስሜት ተባባሪነታችን፣በፍትወት በመቃጠላችን በሐልዮ ኃጢአት እንወድቃለን፡፡ ይሁዳ በመልእክቱ ‹‹በመጨረሻው ዘመን በኃጢአተኝነት እንደ ገዛ ምኞታቸው እየሄዱ ዘባቾች ይሆናሉ›› ያለው የወሲብ ፊልም በማየት በኃጢአት እግዚአብሔር ላይ ለመዘበት የምንሞክረውን እኛንም ነው፡፡ /ይሁ 1÷18/
ወዳጆቼ በዚህ ችግር የተጠቃነው ሰዎች ‹‹ከዚህ አስከፊ ችግር እንዴት እንላቀቅ›› የሚለው ዋና ጉዳያችን ነው፡፡ በነገራችን ላይ የወሲብ ፊልም በማየት ሱስ የተጠቁት በምዕራባውያን ዘንድ እንደ አንድ ትልቅ በሽተኛ ነው የሚታዩት፡፡ ምክንያቱም በወሲብ ፊልም የሚያዩት ነገር ማህበራዊ ሕይወታቸው፣የግል ሕይወታቸው፣የትዳር ሕይወታቸው ይበላሻል፡፡ ስለዚህ ከዚህ ሲስ ለመላቀቅ የረጅም ጊዜ ምናልባትም ዓመት የሚፈጅ የሥነ-ልቦና ህክምና ይሰጥዋቸዋል፡፡
ወደ እኛ ስንመጣ ግን የዝሙት አጋንንቱ ነው ውስጣችን በመግባት ሱስ የሚያደርግብን፡፡ ይህም አጋንንቱን ይጠቅመዋል፡፡ አንደኛ ዘማዊ ያደርገናል፡፡ ሁለተኛ የኢ-ሩካቤ ሱሰኛ ያደርገናል፡፡ ሶስተኛ ግለ ወሲብን ያጠናውተናል፡፡ አራተኛ ግብረ ሰዶማዊ ያደርገናል፡፡ አምስተኛ በትዳር ላይ እንድንማግጥ ያደርገናል፡፡ ስድስተኛ ሰላማዊ የትዳር ሩካቤያችንን ይረብሽብናል፡፡ ሰባተኛ ቅድስናን ከእኛ ያርቃል፡፡ ስምንተኛ ከእግዚአብሔር ያጣላናል ያቆራርጠናል፣በጸያፍ ግብራችን እንድንጠላ ያደርገናል፡፡ ዘጠነኛ አራሱን የቻለ አንድ በሽታ ይሆንብናል፡፡ አሥረኛ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ትልቅ እንቅፋት ይሆንብናል፡፡
ስለዚህ ከዚህ ሱስ ለመላቀቅ በመጀመሪያ የአጋንንት የጥፋት ስልት መሆኑንና እኛን ለማነላሸት የተሠራ ሰይጣናዊ ሥራ መሆኑን ልናውቅ ይገባል፡፡ እንዲሁን ንስሐ በመግባት በጾም፣በጸሎት፣በስግደት በመበርታት በዚህ ሱስ የተጠናወተንን የዝሙት አጋንንት ለማራቅ፣ለመላቀቅ መጣር አለብን፡፡ በተለይ ሰው እግዚአብሔር ካልረዳው ምንም ማድረግ ስለማይችል ከዚህ ጸያፍ ችግር እንዲገላግለን ወደ ፈጣሪያችን መጮህ ይገባናል፡፡ በእርግጥ የወሲብ ፊልሞች በስልካችን አፖች ላይ ይዘን ስለምንዞር ላለማየት ከራሳችን ጋር ቃል ልንገባና በማየት ከእግዚአብሔር ጋር እንዳንጣላ የምናይበትን አማራጮች አለመጠቀም ነው፡፡ በተረፈ አምላከ ቅዱሳን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡
‹‹ለምኞት እንዳትታዘዙ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አይንገሥ›› ሮሜ 6÷12
አንብበው ሲጨርሱ እንደተለመደው ለወዳጆ ያዳርሱ!
ክፍል አሥራ ስምንት
እንጸልያለን፣እንጾማለን፣ጸበል እንጠመቃለን ስለዚህ ዓይነ ጥላ የለብኝም ማለት እንችላለን?
ዓይነ ጥላው ከሌለ ታድያ
ለምን ፈተና በዛብን፣ነገሮች ተዘጋጉብን?
እንዴት ባለ ስልት ነው የሚፈትነን፣የሚጫወትብን?
ይቀጥላል …
ጥቅምት 12/2/11 ዓ.ም
አዲስ አበባ
እንዴት ባለ ስልት ነው የሚፈትነን፣የሚጫወትብን?
ይቀጥላል …
ጥቅምት 12/2/11 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ሰላም ወገኖች....እንዴት ከርማችኋል...ትንሽ ተጠፋፍተናል....መንፈሳዊው ውጊያ እንዴት ነው? በረታችሁ ወይስ ደከማችሁ
"እንጨት" አዳምን ከቤቱ አባረረው!
"እንጨት" ኖህን ከጥፋት ውሃ አዳነው!
"እንጨት" ይስኅቅን ክመታረድ አዳነው!
"እንጨት" የኤርትራን ባህር ለሁለት ከፈለ!
"እንጨት" ለዳዊት ቅብአ ዘይት ሆነ!
"እንጨት" ለአሮን በትር ሆነ!
"እንጨት" የጽዮን ጽላት ሆነ!
"እንጨት" ኪሩቤል ሆነ!
"እንጨት" ሰይጣንን አሰረ!
"እንጨት" ሲኦልን ሰባበረ!
"እንጨት" ገነትን መርቆ ከፈተ!
"እንጨት" ፈያታዊን ወደ ገነት ሰደደ!
"እንጨት" አለምን ቀደሰ!
"እንጨት" ድንግልንና ዮሐንስን አማማለ!
"እንጨት" አዳምን ወደ ቀድሞ ክብሩ መለስው!
"እንጨት" ለአንካሶች ምርኩዛቸው ነው!
"እንጨት" ለእውራን ብርሃናቸው ነው!
"እንጨት" ለለምጻሞች መንጺያቸው ነው!
"እንጨት" ለተራቡት ምግባቸው ነው!
"እንጨት" ለነብያት ትንቢታቸው ነው!
"እንጨት" ለሐዋርያት ስብከታቸው ነው!
"እንጨት" ለሰማዕታት ሞገሳቸው ነው!
"እንጨት" ለክርስቲያኖች ሰላም ነው!
ስለዚህም "እንጨት" ፍቅር፡ ክብር፡ ስግደት ይገባዋል!!❤
"እንጨት" ኖህን ከጥፋት ውሃ አዳነው!
"እንጨት" ይስኅቅን ክመታረድ አዳነው!
"እንጨት" የኤርትራን ባህር ለሁለት ከፈለ!
"እንጨት" ለዳዊት ቅብአ ዘይት ሆነ!
"እንጨት" ለአሮን በትር ሆነ!
"እንጨት" የጽዮን ጽላት ሆነ!
"እንጨት" ኪሩቤል ሆነ!
"እንጨት" ሰይጣንን አሰረ!
"እንጨት" ሲኦልን ሰባበረ!
"እንጨት" ገነትን መርቆ ከፈተ!
"እንጨት" ፈያታዊን ወደ ገነት ሰደደ!
"እንጨት" አለምን ቀደሰ!
"እንጨት" ድንግልንና ዮሐንስን አማማለ!
"እንጨት" አዳምን ወደ ቀድሞ ክብሩ መለስው!
"እንጨት" ለአንካሶች ምርኩዛቸው ነው!
"እንጨት" ለእውራን ብርሃናቸው ነው!
"እንጨት" ለለምጻሞች መንጺያቸው ነው!
"እንጨት" ለተራቡት ምግባቸው ነው!
"እንጨት" ለነብያት ትንቢታቸው ነው!
"እንጨት" ለሐዋርያት ስብከታቸው ነው!
"እንጨት" ለሰማዕታት ሞገሳቸው ነው!
"እንጨት" ለክርስቲያኖች ሰላም ነው!
ስለዚህም "እንጨት" ፍቅር፡ ክብር፡ ስግደት ይገባዋል!!❤
አርጋኖን ተበልቶ ይጸለያል?
የአርጋኖን ጸሎት ተጀምሮ ሲቋረጥ ሰይጣን ይመታናል?
አርጋኖን ከተጀመረ አይቋረጥም?
ፀሎቱ በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነት እና በአጋንንት ዘንድ ያለው መፈራት?
የፀሎቱ ጠቀሜታ ምንድን ነው?
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ሼር በማድረግ ላላወቁት አሳውቁ፣ለጥያቄያቸው መልስ ይሁኑ!
ተወዳጆች ሆይ ከፋሲካ በኃላ ባለው በዓለ ሃምሳ ብዙዎቻችን በጸሎት ሕይወታችን የምንዘናጋባት፣በጸሎት እንደ አጽዋማት ወቅት የማንበረታበት፣ጸሎታችንም ወጥ የማይሆንበት እና መቋረጥ የበዛበት ወይም የሚታጎልበት ወቅት ነው፡፡ ይህም የሚሆነው በፍስክ ወቅት የምንበላቸው ምግቦች ለሰውነት ከበድ የሚሉ ስለሆነ ጸሎታችንን ያዘናጉታል፡፡ እንዲሁም ጸሎትን እንደ ውዴታ እንጂ እንደ ግዴታ የማየት እና የመተግበር ልምዱ ስለሌለን ነው፡፡ ሌላው ድካማችንን፣ስንፍናችንን ተገን እያደረገ በየምክንያት ወደ ሕይወታችን ገባ ወጣ የሚለው ሰይጣን የሚያመጣብን ፈተና ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ በዚህ ርዕስ ለብዙዎቻችን ጥያቄ የሚሆነውን ስለ አጋርኖን ጸሎት የማያዳግም ምላሽ ለመስጠት ነው፡፡
ወዳጆቼ ስለ አርጋኖን ጸሎት ጥያቄዎች ከመመለሳችን በፊት እስኪ ትንሽ ስለ ጸሎቱ ደራሲ ዘርዘር አደርገን እንይ፡፡ ምክንያቱም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ‹‹የደራሲውን መጽሐፍ ከማወቅህ በፊት ስለ ደራሲው ማንነት እወቅ›› ስለሚል ነው፡፡
ይህ ታላቅ የእመቤታችን የምስጋና ጸሎት የተደረሰው በኢትዮጲያዊው ቄርሎስ በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነው፡፡ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ጥቅምት 3 ቀን በ1357 ዓ.ም ተጸንሰው በዚያው ዓመት ሐምሌ 7 ቀን በእለተ ማክሰኞ ተወለዱ፡፡ ከመወለዳቸው አስቀድሞ ለእናት አባታቸው በወርኅ መስከረም ቅዱስ ዑራኤል በሰማእታት አለቃ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የተሰየመ ልጅ እንደሚወልዱ ነግሯቸዋል፡፡
አባ ጊዮርጊስ እናትና አባታቸው ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማዋቸው በእውቀት እና በጥበብ አሳደጓቸው፡፡ ለአቅመ ትምህርት ሲደርሱ በጊዘው በኢትዮጲያ ታላቅ የትምህርት ማዕከል በነበረው በሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ ገዳም ገብተው ከታላቁ ሊቅ ዐቃቤ ሰዓት አባ ሠረቀ ብርሃን ጋር እንዲማሩ ሰጥዋቸው፡፡
አባ ጊዮርጊስ ከማኅፀን የተመረጡና ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ቢሆኑም ገዳሙንና አባቶችን በእውቀት ሳይሆን በጉልበት ነበር የሚያገለግሉት፡፡ ግን ሌሊት ሌሊት ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ስዕል ሥር አብዝተው በመስገድ ፈጣሪያቸውን ይማጸኑ ነበር፡፡ አባ ጊዮርጊስ ገዳሙንና አባቶችን በጉልበት ቢያገለግሉም ከአባ ሠረቀ ብርሃም የሚሰጣቸው ትምህርት ሊገባቸው አልቻለም፡፡ ትምህርት እንዳልገባቸው የተረዱት አባ ሠረቀ ብርሃን እንዳይወቀሱ የአባ ጊዮርጊስን አባት አስጠርተው ‹‹ይህ ልጅ ትምህርት ሊገባው አልቻለም ስለዚህ ሌላ ሙያ አስተምረው›› ብለው ለአባቱ ሰጡት፡፡ አባታቸውም መልሰው ‹‹ልጁን የወለድኩት በስዕለት ነውና ከዚህ ገዳምን እያገለገለና አባቶችን እየረዳ ይኑር›› ብለው እዛው ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ትተዋቸው ሄዱ፡፡
በዚያም ትምህርታቸውን እየተማሩ በቀን ዘጠኝ ዘጠኝ ቅርጫት እህል እየፈጩ ማገልገል ቢጀምሩም ቅን አገልግሎት የሚያበረክቱላቸው መነኮሳት ከማመስገን ይልቅ ‹‹ትምህርት የማይገባው›› እያሉ ይዘልፋቸውና ይሰድቧቸው ጀመር፡፡ አባ ጊዮርጊስም ጸጋ እግዚአብሔር ያደረባቸው ደግ ሰው ናቸውና እንደ ሰደቡኝ ልሳደብ፣እንደ ናቁኝ ልናቅ ሳይሉ የተለመደ አገልግሎታቸውን ሳያቋርጡ ከእመቤታችን ሥዕል ስር በግምባራቸው ተደፍተው ‹‹እመቤቴ ሆይ መነኮሳቱ በእኔ ላይ እየፈጸሙብኝ ያለውን ነቀፋ እና ዘለፋ ተመልክተሸ ትምህርቴን እንዲገልጽልኝ ከልጅሽ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ አማልጂኝ›› እያሉ ሲያለቅሱና ሲማፀኑ፤እመቤታችን በገሃድ ተገልጻ ‹‹አይዞህ አታልቅስ ትምህርት ተከልክሎብህ ሳይሆን የምትጠቀምበት ጊዜው እስኪደርስ ነበር፤አሁን ግን ጊዜው ደርሷልና እስከ ሰባት ቀን በዚሁ በሱባዔው እንዳለህ ሆነህ ጠብቀኝ›› ብላቸው ተሰወረች፡፡
አባ ጊዮርጊስም በሱባዔ እንዳሉ በሰባተኛው ቀን እንደተለመደው በሥዕለ ማርያም ሥር ተደፍተው እያለቀሱ ሳሉ እመቤታችን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤልን አስከትላና ጽዋዓ እሳት አስይዛ መጥታ የሕይወት ጽዋዓ አጠጣቻቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስም የሕይወት ጽዋዕን ከጠጡ በኃላ የሰማይና የምድር ምስጢር ሁሉ ተገለጠላቸው፡፡ በእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ተመልተው እግዚአብሔር በመዓልትና በሌሊት በዜማ የሚመሰገንባቸውን፣እመቤታችን በጸሎት የምትመሰገንበትንና ሌሎችንም የምስጋናና የጸሎት ቅዱሳት መጻሕፍትን ደርሰዋል፡፡
አስደናቂ ገድላቸው እንደሚነግረን የአባ ጊዮርጊስ የድርሰት ሥራዎች የሆኑት በተለይም የታወቁት አሥራ ሰባት ናቸው፡፡ እነሱም መጽሐፈ ብርሃን የመዓልትና የሌሊት ሰዓታት፣አርጋኖን፣ኆኅተ ብረሃን፣ውዳሴ መስቀል፣ዕንዚራ ስብሐት፣ሕይወተ ማርያም፣ተአምኆተ ብርሃን/ተአምኆተ ቅዱሳን/ ፣ውዳሴ ስብሐት፣ ውዳሴ ሐዋርያት፣ፍካሬ ሃይማኖት፣ጸሎተ ፈትቶ/በቅዳሴ ጊዜ የሚጸለይ/፣ መጽሐፈ ምስጢር፣መዓዛ ቅዳሴ፣ ቅዳሴ እግዚእ ካልእ፣ውዳሴ ማርያም ካልእ፣ጸሎት ዘቤት ውስተ ቤት እና መዝሙረ ድንግል ናቸው፡፡ ግን በገድሉ ውስጥ በቀጥታ ካልተጠቀሱት መካከል መልክአ ውዳሴ፣መልክአ ሥዕል፣ይዌድስዋ ማርያም/የሰዓታት ክፍል/ እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ ወዳጆቼ ከእነዚህ የአባ ጊዮርጊስ የመንፈስ ቅዱስ ድርሰቶች ውስጥ ለርእሳችን የመረጥነውን አርጋኖን ስለተባለው የእመቤታችን ምስጋና እንመልከት፡፡
ነገረ አርጋኖን ፦
አባታችን አባ ጊዮርጊስ አንድ ቀን የድረሰት መጽሐፍ ሊጽፍ ወደደና ቀኑን ሙሉ ሲጽፋ ዋለ፡፡ በማግስቱም በዚያው ድረሰት ላይ ሊጨምር በወደደ ጊዜ የጻፈበት ጥራዝ ቀለሙ ጠፍቶ ነጭ ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም የተሰረቀ መስሎት በልቡ አዘነ፡፡ ጥራዞቹንም በቆጠራቸው ጊዜ ከቁጥር ሳይጎሉ አገኛቸው፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ በድጋሜ ጻፈ፡፡ በማግስቱም እንደ መጀመሪያው ነጭ ሆኖ አገኘው፡፡ እስከ ሦስትና አራት ቀን ደጋግሞ ጻፈ ግን እንደ መጀመሪያው ሆነበት፡፡
ከዚህ በኃላ ወደ እመቤታችን ይማልል፣ይጸልይ ጀመረ፡፡ እመቤታችንንም ‹‹ይህ የሆነው በኃጢአቴ ነውን? ወይስ አይደለም? እባክሽ ግለጪልኝ›› አላት፡፡ አንድ ቀን አባ ጊዮርጊስ በሌሊት እኩሌታ ወደ ቤተ ክርስትያን ሲሄድ እመቤታችን በድንገት በማይነገር ክብር ተገለጸችላቸው፡፡ ከእሷም ጋር የቅዱሳን ማኅበር ሁሉ ነበሩ፡፡ እመቤታችንም በእጇ ከጸሐይ ከጨረቃ የበለጠ የሚያበራ መጽሐፍ ይዛ ነበር፤አባ ጊዮርጊስም እመቤታችንን ባየ ጊዜ ወደ መሬት ወደቀ፣እንደ በድንም ሆነ፡፡ እመቤታችንም አነሳችውና ‹‹ሳትጠይቀኝ መጽሐፌን ትጽፍ ዘንድ ለምን ደፈርህ›› አለችው፡፡ መልሳም ‹‹እኔ ወድጄህ ከእናትህ ማኅፀን መርጨህ ለጴጥሮስ፣ለጳውሎስና ለዮሐንስ አደራ ሰጥቼህ የለምን›› አለችው፡፡
አባ ጊዮርጊስም ‹‹እመቤቴ ሆይ ይቅር በይኝ፤ደስ የሚያሰኝሽ መስሎኝ ነውና ይህን ባለማወቅ ሠርቻለሁና›› አሏት፡፡ እመቤታችንም ‹‹ወዳጄ ሆይ ይቅር ብየሃለሁ፣ልትጽፍ የወደድከው መጽሐፍም እነሆ በእጄ አለ፤ከአሁን በኃላ የተወደደ ልጄ በአንደበትህ ሊገልጸው ወዷልና፡፡ ነገር ግን ከአርያም ከሰማይ ኅይልን እስክትላበስ ድረስ አትቸኩል›› ብላ ተሰወረችው፡፡
ያን ጊዜ የአባ ጊዮርጊስ ልቡ እንደ ፀሐይ በራ፣የመለኮትም ባሕር በኅሊናው አበራ፡፡ በመንፈስ ቅዱስም መስታወት የተሰወረውን ሁሉ አየ፡፡ እግዚአብሔርን በሚወድ በንጉሥ ዳዊት ዘመን አርጋኖንን ደረሰ፡፡ መጽሐፉንም በሦስት ስሞች ጠራው፡፡ እነሱም አርጋኖነ
የአርጋኖን ጸሎት ተጀምሮ ሲቋረጥ ሰይጣን ይመታናል?
አርጋኖን ከተጀመረ አይቋረጥም?
ፀሎቱ በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነት እና በአጋንንት ዘንድ ያለው መፈራት?
የፀሎቱ ጠቀሜታ ምንድን ነው?
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ሼር በማድረግ ላላወቁት አሳውቁ፣ለጥያቄያቸው መልስ ይሁኑ!
ተወዳጆች ሆይ ከፋሲካ በኃላ ባለው በዓለ ሃምሳ ብዙዎቻችን በጸሎት ሕይወታችን የምንዘናጋባት፣በጸሎት እንደ አጽዋማት ወቅት የማንበረታበት፣ጸሎታችንም ወጥ የማይሆንበት እና መቋረጥ የበዛበት ወይም የሚታጎልበት ወቅት ነው፡፡ ይህም የሚሆነው በፍስክ ወቅት የምንበላቸው ምግቦች ለሰውነት ከበድ የሚሉ ስለሆነ ጸሎታችንን ያዘናጉታል፡፡ እንዲሁም ጸሎትን እንደ ውዴታ እንጂ እንደ ግዴታ የማየት እና የመተግበር ልምዱ ስለሌለን ነው፡፡ ሌላው ድካማችንን፣ስንፍናችንን ተገን እያደረገ በየምክንያት ወደ ሕይወታችን ገባ ወጣ የሚለው ሰይጣን የሚያመጣብን ፈተና ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ በዚህ ርዕስ ለብዙዎቻችን ጥያቄ የሚሆነውን ስለ አጋርኖን ጸሎት የማያዳግም ምላሽ ለመስጠት ነው፡፡
ወዳጆቼ ስለ አርጋኖን ጸሎት ጥያቄዎች ከመመለሳችን በፊት እስኪ ትንሽ ስለ ጸሎቱ ደራሲ ዘርዘር አደርገን እንይ፡፡ ምክንያቱም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ‹‹የደራሲውን መጽሐፍ ከማወቅህ በፊት ስለ ደራሲው ማንነት እወቅ›› ስለሚል ነው፡፡
ይህ ታላቅ የእመቤታችን የምስጋና ጸሎት የተደረሰው በኢትዮጲያዊው ቄርሎስ በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነው፡፡ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ጥቅምት 3 ቀን በ1357 ዓ.ም ተጸንሰው በዚያው ዓመት ሐምሌ 7 ቀን በእለተ ማክሰኞ ተወለዱ፡፡ ከመወለዳቸው አስቀድሞ ለእናት አባታቸው በወርኅ መስከረም ቅዱስ ዑራኤል በሰማእታት አለቃ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የተሰየመ ልጅ እንደሚወልዱ ነግሯቸዋል፡፡
አባ ጊዮርጊስ እናትና አባታቸው ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማዋቸው በእውቀት እና በጥበብ አሳደጓቸው፡፡ ለአቅመ ትምህርት ሲደርሱ በጊዘው በኢትዮጲያ ታላቅ የትምህርት ማዕከል በነበረው በሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ ገዳም ገብተው ከታላቁ ሊቅ ዐቃቤ ሰዓት አባ ሠረቀ ብርሃን ጋር እንዲማሩ ሰጥዋቸው፡፡
አባ ጊዮርጊስ ከማኅፀን የተመረጡና ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ቢሆኑም ገዳሙንና አባቶችን በእውቀት ሳይሆን በጉልበት ነበር የሚያገለግሉት፡፡ ግን ሌሊት ሌሊት ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ስዕል ሥር አብዝተው በመስገድ ፈጣሪያቸውን ይማጸኑ ነበር፡፡ አባ ጊዮርጊስ ገዳሙንና አባቶችን በጉልበት ቢያገለግሉም ከአባ ሠረቀ ብርሃም የሚሰጣቸው ትምህርት ሊገባቸው አልቻለም፡፡ ትምህርት እንዳልገባቸው የተረዱት አባ ሠረቀ ብርሃን እንዳይወቀሱ የአባ ጊዮርጊስን አባት አስጠርተው ‹‹ይህ ልጅ ትምህርት ሊገባው አልቻለም ስለዚህ ሌላ ሙያ አስተምረው›› ብለው ለአባቱ ሰጡት፡፡ አባታቸውም መልሰው ‹‹ልጁን የወለድኩት በስዕለት ነውና ከዚህ ገዳምን እያገለገለና አባቶችን እየረዳ ይኑር›› ብለው እዛው ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ትተዋቸው ሄዱ፡፡
በዚያም ትምህርታቸውን እየተማሩ በቀን ዘጠኝ ዘጠኝ ቅርጫት እህል እየፈጩ ማገልገል ቢጀምሩም ቅን አገልግሎት የሚያበረክቱላቸው መነኮሳት ከማመስገን ይልቅ ‹‹ትምህርት የማይገባው›› እያሉ ይዘልፋቸውና ይሰድቧቸው ጀመር፡፡ አባ ጊዮርጊስም ጸጋ እግዚአብሔር ያደረባቸው ደግ ሰው ናቸውና እንደ ሰደቡኝ ልሳደብ፣እንደ ናቁኝ ልናቅ ሳይሉ የተለመደ አገልግሎታቸውን ሳያቋርጡ ከእመቤታችን ሥዕል ስር በግምባራቸው ተደፍተው ‹‹እመቤቴ ሆይ መነኮሳቱ በእኔ ላይ እየፈጸሙብኝ ያለውን ነቀፋ እና ዘለፋ ተመልክተሸ ትምህርቴን እንዲገልጽልኝ ከልጅሽ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ አማልጂኝ›› እያሉ ሲያለቅሱና ሲማፀኑ፤እመቤታችን በገሃድ ተገልጻ ‹‹አይዞህ አታልቅስ ትምህርት ተከልክሎብህ ሳይሆን የምትጠቀምበት ጊዜው እስኪደርስ ነበር፤አሁን ግን ጊዜው ደርሷልና እስከ ሰባት ቀን በዚሁ በሱባዔው እንዳለህ ሆነህ ጠብቀኝ›› ብላቸው ተሰወረች፡፡
አባ ጊዮርጊስም በሱባዔ እንዳሉ በሰባተኛው ቀን እንደተለመደው በሥዕለ ማርያም ሥር ተደፍተው እያለቀሱ ሳሉ እመቤታችን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤልን አስከትላና ጽዋዓ እሳት አስይዛ መጥታ የሕይወት ጽዋዓ አጠጣቻቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስም የሕይወት ጽዋዕን ከጠጡ በኃላ የሰማይና የምድር ምስጢር ሁሉ ተገለጠላቸው፡፡ በእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ተመልተው እግዚአብሔር በመዓልትና በሌሊት በዜማ የሚመሰገንባቸውን፣እመቤታችን በጸሎት የምትመሰገንበትንና ሌሎችንም የምስጋናና የጸሎት ቅዱሳት መጻሕፍትን ደርሰዋል፡፡
አስደናቂ ገድላቸው እንደሚነግረን የአባ ጊዮርጊስ የድርሰት ሥራዎች የሆኑት በተለይም የታወቁት አሥራ ሰባት ናቸው፡፡ እነሱም መጽሐፈ ብርሃን የመዓልትና የሌሊት ሰዓታት፣አርጋኖን፣ኆኅተ ብረሃን፣ውዳሴ መስቀል፣ዕንዚራ ስብሐት፣ሕይወተ ማርያም፣ተአምኆተ ብርሃን/ተአምኆተ ቅዱሳን/ ፣ውዳሴ ስብሐት፣ ውዳሴ ሐዋርያት፣ፍካሬ ሃይማኖት፣ጸሎተ ፈትቶ/በቅዳሴ ጊዜ የሚጸለይ/፣ መጽሐፈ ምስጢር፣መዓዛ ቅዳሴ፣ ቅዳሴ እግዚእ ካልእ፣ውዳሴ ማርያም ካልእ፣ጸሎት ዘቤት ውስተ ቤት እና መዝሙረ ድንግል ናቸው፡፡ ግን በገድሉ ውስጥ በቀጥታ ካልተጠቀሱት መካከል መልክአ ውዳሴ፣መልክአ ሥዕል፣ይዌድስዋ ማርያም/የሰዓታት ክፍል/ እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ ወዳጆቼ ከእነዚህ የአባ ጊዮርጊስ የመንፈስ ቅዱስ ድርሰቶች ውስጥ ለርእሳችን የመረጥነውን አርጋኖን ስለተባለው የእመቤታችን ምስጋና እንመልከት፡፡
ነገረ አርጋኖን ፦
አባታችን አባ ጊዮርጊስ አንድ ቀን የድረሰት መጽሐፍ ሊጽፍ ወደደና ቀኑን ሙሉ ሲጽፋ ዋለ፡፡ በማግስቱም በዚያው ድረሰት ላይ ሊጨምር በወደደ ጊዜ የጻፈበት ጥራዝ ቀለሙ ጠፍቶ ነጭ ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም የተሰረቀ መስሎት በልቡ አዘነ፡፡ ጥራዞቹንም በቆጠራቸው ጊዜ ከቁጥር ሳይጎሉ አገኛቸው፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ በድጋሜ ጻፈ፡፡ በማግስቱም እንደ መጀመሪያው ነጭ ሆኖ አገኘው፡፡ እስከ ሦስትና አራት ቀን ደጋግሞ ጻፈ ግን እንደ መጀመሪያው ሆነበት፡፡
ከዚህ በኃላ ወደ እመቤታችን ይማልል፣ይጸልይ ጀመረ፡፡ እመቤታችንንም ‹‹ይህ የሆነው በኃጢአቴ ነውን? ወይስ አይደለም? እባክሽ ግለጪልኝ›› አላት፡፡ አንድ ቀን አባ ጊዮርጊስ በሌሊት እኩሌታ ወደ ቤተ ክርስትያን ሲሄድ እመቤታችን በድንገት በማይነገር ክብር ተገለጸችላቸው፡፡ ከእሷም ጋር የቅዱሳን ማኅበር ሁሉ ነበሩ፡፡ እመቤታችንም በእጇ ከጸሐይ ከጨረቃ የበለጠ የሚያበራ መጽሐፍ ይዛ ነበር፤አባ ጊዮርጊስም እመቤታችንን ባየ ጊዜ ወደ መሬት ወደቀ፣እንደ በድንም ሆነ፡፡ እመቤታችንም አነሳችውና ‹‹ሳትጠይቀኝ መጽሐፌን ትጽፍ ዘንድ ለምን ደፈርህ›› አለችው፡፡ መልሳም ‹‹እኔ ወድጄህ ከእናትህ ማኅፀን መርጨህ ለጴጥሮስ፣ለጳውሎስና ለዮሐንስ አደራ ሰጥቼህ የለምን›› አለችው፡፡
አባ ጊዮርጊስም ‹‹እመቤቴ ሆይ ይቅር በይኝ፤ደስ የሚያሰኝሽ መስሎኝ ነውና ይህን ባለማወቅ ሠርቻለሁና›› አሏት፡፡ እመቤታችንም ‹‹ወዳጄ ሆይ ይቅር ብየሃለሁ፣ልትጽፍ የወደድከው መጽሐፍም እነሆ በእጄ አለ፤ከአሁን በኃላ የተወደደ ልጄ በአንደበትህ ሊገልጸው ወዷልና፡፡ ነገር ግን ከአርያም ከሰማይ ኅይልን እስክትላበስ ድረስ አትቸኩል›› ብላ ተሰወረችው፡፡
ያን ጊዜ የአባ ጊዮርጊስ ልቡ እንደ ፀሐይ በራ፣የመለኮትም ባሕር በኅሊናው አበራ፡፡ በመንፈስ ቅዱስም መስታወት የተሰወረውን ሁሉ አየ፡፡ እግዚአብሔርን በሚወድ በንጉሥ ዳዊት ዘመን አርጋኖንን ደረሰ፡፡ መጽሐፉንም በሦስት ስሞች ጠራው፡፡ እነሱም አርጋኖነ
ውዳሴ፣መሰንቆ መዝሙር፣ዕንዚራ ስብሐት ናቸው፡፡ እመቤታችንም አባ ጊዮርጊስ ስለ ደረሰው ስለ አርጋኖን የጸሎትና የምስጋና መጽሐፍ ክብሩን ስትገልጽለት አባ ጊዮርጊስም ‹‹ከደረስኳቸውና ከተናገርኳቸው ድርሳናት ሁሉ አርጋኖን ውዳሴ ይጣፍጣል፣ይበልጣል›› አለ፡፡ ተወዳጆች ሆይ ልብ በሉ ይህ ታላቅ የእመቤታችን የጸሎት እና የምስጋና መጽሐፍ ከሰማይ የተገለጠ እና ለአባ ጊዮርጊስ ከእመቤታችን እጅ የተሰጠ መጽሐፍ ነው፡፡
የአርጋኖን መጽሐፍ ይዘት በአጭሩ
የአርጋኖን መጽሐፍ ይዘት በሁለት ከፍለን ማየት እንችላለን፡፡ የመጀመርያው መጽሐፍ ስለ እመቤታችን ንጽህና፣ቅድስና፣ፍጹም ድንግልና አብዝቶና አምልቶ ያናገራል፡፡ የእመቤታችንን ወላዲተ አምላክነትን ይመሰክራል፡፡ እንዲሁም ስለ ክብራ በተለያዩ የከበሩ ማዕድናት እየመሰለ ያደንቃል፡፡ ሌላው ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ያለውን ምስጢራት በእሷ ይገልጻል፡፡
ሁለተኛው መጽሐፉ የእመቤታችን ምስጋና ቢሆን ስለ ተወዳጅ ልጅዋ በሰፊው ያትታል፡፡ በተለይ በእሷ ስም የጌታን ሕማም ስቃይ እያሳሰበ፤ጌታንም እያመሰገነ፣ሰማያዊ ክብሩም ይገጽልናል፡፡ እሷን ብቻ ሳይሆን ልጇንም አምልቶ እና አስፍቶ ያመሰግናል፡፡ ስለ አርጋኖን ይህንን ካልን ወደ ጥያቄያችን እንመለስ፡፡
አርጋኖን ተበልቶ ይጸለያል?
አርጋኖን ሳንበላም በልተንም የምንጸልየው ጸሎት ነው፡፡ ምክንያቱም ጸሎቱ ምስጋና ስለሆነ ነው፡፡ ምስጋና ደግሞ ከሆድ ሳይሆን ከልብ የሚገናኝ ነው፡፡ እመቤታችንን በአርጋኖን ጸሎት ማመስገን የፈለገ ሰው የበረታ ሌሊት ወይም ጠዋት መጸለይ፡፡ ካልሆነልንና ካልተመቸን በየትኛውም ሰዓት መጸለይ እንችላለን፡፡ ለምሳሌ በሥራና በተለያየ ምክንያት አርጋኖንን ሌሊት አልያም ጠዋት መጸለይ ያቃተው ሰው ማታ በጸሎት ሰዓቱ አርጋኖንን መጸለይ ይችላል፡፡
አርጋኖን ከሌሎቹ ጸሎቶት አንዱ የሚለይበት ጸሎቱ ረጅም በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ አጋንንት የጸሎቱን ርዝመት እንደ ስንፍና ምክንያት ተጠቅሞ እንዳንጸልይ እንዳያረገን በላንም አልበላን በሚመቸን ሰዓት መጸለይ፡፡ በተለይ ሌሊት ወይም ጠዋት መጸለይ ያልቻልን ሰዎች ማታ ብንጸልይ ይመረጣል፡፡ በእመቤታችን ተባርከን ስለምንተኛ ቅዠቱም፣ፈተናውም ይርቅልናል፡፡ ሰናይ ሕልምም ያሳየናል፡፡
የአርጋኖን ጸሎት ተጀምሮ ሲቋረጥ ሰይጣን ይመታናል?
ወዳጆቼ እንኳን አርጋኖንን የሚያክል ታላቅ ጸሎት ቀርቶ ማንኛውም ጸሎት ባይቋረጥ ይመረጣል፡፡ ምክንያቱም ከላይ እንዳልኩት ለእኛ ለኦርቶዶክሶች ጸሎት ውዴታችን ሳይሆን ግዴታችን ነውና፡፡ ስለዚህ ጸሎት ማቋረጥ ለመንፈሳዊ ሕይወት መዳከም እና ለተለያዩ ፈተናዎች ይዳርገናል፡፡ ጌታችንም እያቋረጣችሁ ሳይሆን ተግታችሁ ጸልዩ ነው ያለን፡፡ ለሥጋችን በቀን ሁለት ሦስቴ በቋሚነት ምግብ እንደምንበላ ሁሉ ጸሎትም ነፍስ ምግብ ነውና ቢያስ በሃያ አራት ሰዓት ሁለቴ ጠዋት እና ማታ ልንጸልይ ይገባል ያስገድዳል፡፡
አርጋኖን ከጸሎት ባሻገር ምስጋና ስለሆነ ጸልየን ብናቋርጥ ሰይጣን አይመታንም፡፡ ከተቋረጠ ሰይጣን ይመታል የሚሉት አንድም ቀን ጸሎቱን ጸልየው የማይውቁት ሰዎች ናቸው፡፡ በመሠረቱ አንድ ሰው በለቅሶ፣በሠርግ፣በሕመምና በተለያዩ ማህበራዊ ገጠመኞች እና ችግሮች ጸሎትን የሚያቋርኝበት እና ጸሎቱም የሚታጎልበት ጊዜ ይኖረዋል፡፡ ስለዚህ በተቻለን አቅም ሳናቋርጥ ብንጸልይ እመቤታችን ትለመነናለች፣ችግራችንን ትፈታልናለች፣የአጋንንትን ፈተና ታስታግስልናለች፣ታርቅልናለች፡፡ እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባን ጸሎትን ለምሳሌ አርጋኖንን ስንጸልይ ሰይጣን የሚርቀን ስናቋርጥ የሚመታን ከሆነ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ሳይሆን ጸሎታችን ነው ያሰኛል፡፡ ይህ ደግሞ ልክ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ስንጸልይም ሳንጸልይም ይጠብቀናል፡፡ ደግሞስ እስከ ዛሬ እራሳችንን የጠበቅነው በየትኛው ጸሎታችን ነው? ቂም በቋጠረው፣ይቅርታን እንቢኝ ባለው፣ኃጢአት በተጫነው፣ቅድስና በሌለው ማንነታችንና ጸሎታችን ነው የምንጠብቀው? ወይስ በቸርነቱ እና በጠባቂነቱ?
ስለዚህ አርጋኖንን ስንጸልይ ሰይጣንን የሚያርቅ ስናቋርጠው ሰይጣንን የሚያቀርብ አይደለም፡፡ ወዳጆቼ እስኪ አንድ ቀን እናመስግናት እና የሚሆነውን እንይ፡፡ ሰይጣን እናታችንን እንዳናመሰግናት፣አርጋኖን ጸልየን ነፍሳችንን የእመቤታችንን ፍቅር እንዳንመግባት የሚፈጥረው ሰይጣናዊ አሉባልታ እንጂ እውነታ የለውም፡፡ ሌላው መረሳት የሌለበት እመቤታችን ከምስጋናዎችዋ ሁሉ እጅጉን የምትወደው አርጋኖንን ነው፡፡ አባ ጊዮርጊስም ከደረስዋቸው ድርሰቶች ሁሉ አብልጠው የሚወዱት አርጋኖንን ነው፡፡
አርጋኖን ስንጸልይ ይረዝምብናል ለምንል እንዲህ እንጸልይ
ተወዳጆች ሆይ አርጋኖን ከሌሎቹ ጸሎቶች ለመጸለይ ምቹ የሚያደርገው በምዕራፍ በምዕራፍ መከፋፈሉ ነው፡፡ በምዕራፍ ሲከፋፈል የሐሳብ ፍሰት መቋረጥ እና መፋለስ የለውም፡፡ አንዱን ምዕራፍ ጨርሶ ወደ ሌላኛው ምዕራፍ ስንገባ በአዲስ ምስጋና ነው የሚጀምረው፡፡ ይህ ደግሞ ጊዜ ለሌለንና ጸሎቱ ረጅም ነው እያልን ላለመጸለይ ምክንያት ለምናቀርብ ሰዎች የቻልነውን ያህል አመስግነን ምዕራፉን ስንጨርስ በአባታችን ሆይ ዘግተን እመቤታችንን መማፀን እንችላለን፡፡ ልክ እንደ ዳዊት አንድም ሁለት ሦስትም ምዕራፍ መጸለይ እንችላለን፡፡
የዛሬ አሥር ዓመት አንድ የእመቤታችን ወዳጅ ሱባዔ ትገባና እመቤታችን አርጋኖን ብትጸልይ ብዙ በረከት እንደምታገኝ፣ብዙ ችግሯ እንደሚፈታና አርጋኖንን ብትጸልይ እመቤታችን አብልጣ እንደምትወዳት ትነግራታለች፡፡ ልጅትዋም ‹‹ጸሎቱ ረጅም ነው እንዴት አድርጌ ነው የምጸልየው?›› ስትላት እመቤታችንም የቻለችውን ያህል ጸልያ ምዕራፉ ላይ ማቆም እንደምትችል ነግራት እስከ ዛሬ ስትችል ሙሉውን ያልቻለች ቀን በምዕራፉ ላይ እያበቃች ትጸልያለች፡፡ ስለዚህ የእኛን ችግር ከእኛ የበለጠ የምታውቀው እመቤታችን ስለሆነች እንዳቅማችን በመጸለይ ከእመቤታችን ጸጋና በረከትን እናትርፍበት፡፡
አርጋኖን ከተጀመረ አይቋረጥም?
ከላይ እንዳየነው ማንኛውም ጸሎት ባይቋረጥ ይመከራል፡፡ ግን አርጋኖን መጸለይ ከተጀመረ አይቋረጥም የሚለው ሰይጣናዊ አሉባልታ ብዙዎችን ጸሎቱን እንዲወዱት ሳይሆን እንዲፈሩት አድርጓቸዋል፡፡ ሰይጣን ጸሎት የምናቋርጥበትን መቶ ምክንያቶችን እየደረደረ፣በጎን ደግሞ በሰዎች ላይ እያደረ ‹‹አርጋኖን ከተጀመረ አይቋረጥም›› እያስባለ ጸሎቱን እንደ ጸሎት እንድንወደው ሳይሆን እንድንፈራው አድርጎናል፡፡ ወዳጆቼ ከቻላችሁ በቋሚነት ካልቻላችሁ ባገኛችሁት አጋጣሚና ጊዜ እናትችሁን በአርጋኖን አመስግኗት ጸልዩበት እንጂ የሰይጣንን አሉባልታ እየሰማችሁ ከጸሎቱ በረከት ሳትሳተፉ እንዳትቀሩ፡፡ እኛ ጸሎቱን ከጀመርን እመቤታችን ስለምታበረታን ጸሎቱን መፍራት ሳይሆን መጸለይ ይገባል፡፡
ጸሎቱ በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነት እና በአጋንንት ዘንድ ያለው መፈራት
ወዳጆቼ ለአጋንንት ሁሉም ጸሎቶች ቢያቃጥሉትም አርጋኖን ግን ለአጋንንት እሳት ከመሆኑም ባሻገር ጸሎቱ እጅጉን ይከብደዋል፡፡ አጋንንት ከማይቋቋመው ጸሎቶች አንዱ አርጋኖን ነው፡፡ ጸሎቱ በእመቤታችን ዘንድ እጅጉን ተወዳጅ ስለሆነ በአጋንንት ዘንድ ደግሞ ይጠላል፡፡ ስለዚህ አርጋኖንን ስትጸልዩ ጸሎቱ በራሱ ምልክት ያሳያቹኃል፡፡ በተለይ በውስጣችን አንዳች የሚፈትነን መንፈስ ካለ ገና ጸሎቱን ሳንጀምር እንጨናነቃለን፣ያስጠላናል፣ሰውነታንን ይከብደናል፡፡ ስንጀምረው ያስፋሽገናል፣ጸሎቱ አልገፋ ይለናል፣ተራራ መስሎ ይታየናል፡፡ እየጸለይነው ሰውነታን ይዝላል፣እሳት ይለቅብናል፣ያልበናል፣ወገባችን እግራችን ይብረከረካል ይንቀጠቀጣል፡፡ የምናውቀው አማረኛ
የአርጋኖን መጽሐፍ ይዘት በአጭሩ
የአርጋኖን መጽሐፍ ይዘት በሁለት ከፍለን ማየት እንችላለን፡፡ የመጀመርያው መጽሐፍ ስለ እመቤታችን ንጽህና፣ቅድስና፣ፍጹም ድንግልና አብዝቶና አምልቶ ያናገራል፡፡ የእመቤታችንን ወላዲተ አምላክነትን ይመሰክራል፡፡ እንዲሁም ስለ ክብራ በተለያዩ የከበሩ ማዕድናት እየመሰለ ያደንቃል፡፡ ሌላው ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ያለውን ምስጢራት በእሷ ይገልጻል፡፡
ሁለተኛው መጽሐፉ የእመቤታችን ምስጋና ቢሆን ስለ ተወዳጅ ልጅዋ በሰፊው ያትታል፡፡ በተለይ በእሷ ስም የጌታን ሕማም ስቃይ እያሳሰበ፤ጌታንም እያመሰገነ፣ሰማያዊ ክብሩም ይገጽልናል፡፡ እሷን ብቻ ሳይሆን ልጇንም አምልቶ እና አስፍቶ ያመሰግናል፡፡ ስለ አርጋኖን ይህንን ካልን ወደ ጥያቄያችን እንመለስ፡፡
አርጋኖን ተበልቶ ይጸለያል?
አርጋኖን ሳንበላም በልተንም የምንጸልየው ጸሎት ነው፡፡ ምክንያቱም ጸሎቱ ምስጋና ስለሆነ ነው፡፡ ምስጋና ደግሞ ከሆድ ሳይሆን ከልብ የሚገናኝ ነው፡፡ እመቤታችንን በአርጋኖን ጸሎት ማመስገን የፈለገ ሰው የበረታ ሌሊት ወይም ጠዋት መጸለይ፡፡ ካልሆነልንና ካልተመቸን በየትኛውም ሰዓት መጸለይ እንችላለን፡፡ ለምሳሌ በሥራና በተለያየ ምክንያት አርጋኖንን ሌሊት አልያም ጠዋት መጸለይ ያቃተው ሰው ማታ በጸሎት ሰዓቱ አርጋኖንን መጸለይ ይችላል፡፡
አርጋኖን ከሌሎቹ ጸሎቶት አንዱ የሚለይበት ጸሎቱ ረጅም በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ አጋንንት የጸሎቱን ርዝመት እንደ ስንፍና ምክንያት ተጠቅሞ እንዳንጸልይ እንዳያረገን በላንም አልበላን በሚመቸን ሰዓት መጸለይ፡፡ በተለይ ሌሊት ወይም ጠዋት መጸለይ ያልቻልን ሰዎች ማታ ብንጸልይ ይመረጣል፡፡ በእመቤታችን ተባርከን ስለምንተኛ ቅዠቱም፣ፈተናውም ይርቅልናል፡፡ ሰናይ ሕልምም ያሳየናል፡፡
የአርጋኖን ጸሎት ተጀምሮ ሲቋረጥ ሰይጣን ይመታናል?
ወዳጆቼ እንኳን አርጋኖንን የሚያክል ታላቅ ጸሎት ቀርቶ ማንኛውም ጸሎት ባይቋረጥ ይመረጣል፡፡ ምክንያቱም ከላይ እንዳልኩት ለእኛ ለኦርቶዶክሶች ጸሎት ውዴታችን ሳይሆን ግዴታችን ነውና፡፡ ስለዚህ ጸሎት ማቋረጥ ለመንፈሳዊ ሕይወት መዳከም እና ለተለያዩ ፈተናዎች ይዳርገናል፡፡ ጌታችንም እያቋረጣችሁ ሳይሆን ተግታችሁ ጸልዩ ነው ያለን፡፡ ለሥጋችን በቀን ሁለት ሦስቴ በቋሚነት ምግብ እንደምንበላ ሁሉ ጸሎትም ነፍስ ምግብ ነውና ቢያስ በሃያ አራት ሰዓት ሁለቴ ጠዋት እና ማታ ልንጸልይ ይገባል ያስገድዳል፡፡
አርጋኖን ከጸሎት ባሻገር ምስጋና ስለሆነ ጸልየን ብናቋርጥ ሰይጣን አይመታንም፡፡ ከተቋረጠ ሰይጣን ይመታል የሚሉት አንድም ቀን ጸሎቱን ጸልየው የማይውቁት ሰዎች ናቸው፡፡ በመሠረቱ አንድ ሰው በለቅሶ፣በሠርግ፣በሕመምና በተለያዩ ማህበራዊ ገጠመኞች እና ችግሮች ጸሎትን የሚያቋርኝበት እና ጸሎቱም የሚታጎልበት ጊዜ ይኖረዋል፡፡ ስለዚህ በተቻለን አቅም ሳናቋርጥ ብንጸልይ እመቤታችን ትለመነናለች፣ችግራችንን ትፈታልናለች፣የአጋንንትን ፈተና ታስታግስልናለች፣ታርቅልናለች፡፡ እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባን ጸሎትን ለምሳሌ አርጋኖንን ስንጸልይ ሰይጣን የሚርቀን ስናቋርጥ የሚመታን ከሆነ የሚጠብቀን እግዚአብሔር ሳይሆን ጸሎታችን ነው ያሰኛል፡፡ ይህ ደግሞ ልክ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ስንጸልይም ሳንጸልይም ይጠብቀናል፡፡ ደግሞስ እስከ ዛሬ እራሳችንን የጠበቅነው በየትኛው ጸሎታችን ነው? ቂም በቋጠረው፣ይቅርታን እንቢኝ ባለው፣ኃጢአት በተጫነው፣ቅድስና በሌለው ማንነታችንና ጸሎታችን ነው የምንጠብቀው? ወይስ በቸርነቱ እና በጠባቂነቱ?
ስለዚህ አርጋኖንን ስንጸልይ ሰይጣንን የሚያርቅ ስናቋርጠው ሰይጣንን የሚያቀርብ አይደለም፡፡ ወዳጆቼ እስኪ አንድ ቀን እናመስግናት እና የሚሆነውን እንይ፡፡ ሰይጣን እናታችንን እንዳናመሰግናት፣አርጋኖን ጸልየን ነፍሳችንን የእመቤታችንን ፍቅር እንዳንመግባት የሚፈጥረው ሰይጣናዊ አሉባልታ እንጂ እውነታ የለውም፡፡ ሌላው መረሳት የሌለበት እመቤታችን ከምስጋናዎችዋ ሁሉ እጅጉን የምትወደው አርጋኖንን ነው፡፡ አባ ጊዮርጊስም ከደረስዋቸው ድርሰቶች ሁሉ አብልጠው የሚወዱት አርጋኖንን ነው፡፡
አርጋኖን ስንጸልይ ይረዝምብናል ለምንል እንዲህ እንጸልይ
ተወዳጆች ሆይ አርጋኖን ከሌሎቹ ጸሎቶች ለመጸለይ ምቹ የሚያደርገው በምዕራፍ በምዕራፍ መከፋፈሉ ነው፡፡ በምዕራፍ ሲከፋፈል የሐሳብ ፍሰት መቋረጥ እና መፋለስ የለውም፡፡ አንዱን ምዕራፍ ጨርሶ ወደ ሌላኛው ምዕራፍ ስንገባ በአዲስ ምስጋና ነው የሚጀምረው፡፡ ይህ ደግሞ ጊዜ ለሌለንና ጸሎቱ ረጅም ነው እያልን ላለመጸለይ ምክንያት ለምናቀርብ ሰዎች የቻልነውን ያህል አመስግነን ምዕራፉን ስንጨርስ በአባታችን ሆይ ዘግተን እመቤታችንን መማፀን እንችላለን፡፡ ልክ እንደ ዳዊት አንድም ሁለት ሦስትም ምዕራፍ መጸለይ እንችላለን፡፡
የዛሬ አሥር ዓመት አንድ የእመቤታችን ወዳጅ ሱባዔ ትገባና እመቤታችን አርጋኖን ብትጸልይ ብዙ በረከት እንደምታገኝ፣ብዙ ችግሯ እንደሚፈታና አርጋኖንን ብትጸልይ እመቤታችን አብልጣ እንደምትወዳት ትነግራታለች፡፡ ልጅትዋም ‹‹ጸሎቱ ረጅም ነው እንዴት አድርጌ ነው የምጸልየው?›› ስትላት እመቤታችንም የቻለችውን ያህል ጸልያ ምዕራፉ ላይ ማቆም እንደምትችል ነግራት እስከ ዛሬ ስትችል ሙሉውን ያልቻለች ቀን በምዕራፉ ላይ እያበቃች ትጸልያለች፡፡ ስለዚህ የእኛን ችግር ከእኛ የበለጠ የምታውቀው እመቤታችን ስለሆነች እንዳቅማችን በመጸለይ ከእመቤታችን ጸጋና በረከትን እናትርፍበት፡፡
አርጋኖን ከተጀመረ አይቋረጥም?
ከላይ እንዳየነው ማንኛውም ጸሎት ባይቋረጥ ይመከራል፡፡ ግን አርጋኖን መጸለይ ከተጀመረ አይቋረጥም የሚለው ሰይጣናዊ አሉባልታ ብዙዎችን ጸሎቱን እንዲወዱት ሳይሆን እንዲፈሩት አድርጓቸዋል፡፡ ሰይጣን ጸሎት የምናቋርጥበትን መቶ ምክንያቶችን እየደረደረ፣በጎን ደግሞ በሰዎች ላይ እያደረ ‹‹አርጋኖን ከተጀመረ አይቋረጥም›› እያስባለ ጸሎቱን እንደ ጸሎት እንድንወደው ሳይሆን እንድንፈራው አድርጎናል፡፡ ወዳጆቼ ከቻላችሁ በቋሚነት ካልቻላችሁ ባገኛችሁት አጋጣሚና ጊዜ እናትችሁን በአርጋኖን አመስግኗት ጸልዩበት እንጂ የሰይጣንን አሉባልታ እየሰማችሁ ከጸሎቱ በረከት ሳትሳተፉ እንዳትቀሩ፡፡ እኛ ጸሎቱን ከጀመርን እመቤታችን ስለምታበረታን ጸሎቱን መፍራት ሳይሆን መጸለይ ይገባል፡፡
ጸሎቱ በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነት እና በአጋንንት ዘንድ ያለው መፈራት
ወዳጆቼ ለአጋንንት ሁሉም ጸሎቶች ቢያቃጥሉትም አርጋኖን ግን ለአጋንንት እሳት ከመሆኑም ባሻገር ጸሎቱ እጅጉን ይከብደዋል፡፡ አጋንንት ከማይቋቋመው ጸሎቶች አንዱ አርጋኖን ነው፡፡ ጸሎቱ በእመቤታችን ዘንድ እጅጉን ተወዳጅ ስለሆነ በአጋንንት ዘንድ ደግሞ ይጠላል፡፡ ስለዚህ አርጋኖንን ስትጸልዩ ጸሎቱ በራሱ ምልክት ያሳያቹኃል፡፡ በተለይ በውስጣችን አንዳች የሚፈትነን መንፈስ ካለ ገና ጸሎቱን ሳንጀምር እንጨናነቃለን፣ያስጠላናል፣ሰውነታንን ይከብደናል፡፡ ስንጀምረው ያስፋሽገናል፣ጸሎቱ አልገፋ ይለናል፣ተራራ መስሎ ይታየናል፡፡ እየጸለይነው ሰውነታን ይዝላል፣እሳት ይለቅብናል፣ያልበናል፣ወገባችን እግራችን ይብረከረካል ይንቀጠቀጣል፡፡ የምናውቀው አማረኛ
እየጠፋን አልነበብ ይለናል፣እንተባተባለን፡፡ መንጠራራት እና ጩኸ ጩኸ የሚል ስሜት ይሰማናል፡፡
ይህን ጸሎት በርትተን ከጸለይን የሚፈትነን መንፈስ ይያዝልናል፡፡ አባ ጊዮርጊስም አርጋኖንን ሰይጣን እንዴት እንደሚጠላው ሲገልጽ ‹‹ሰይፍ ነው አንገቱን ይቆርጠዋል፣መራጃ ነው ወገቡን ይሰብረዋል፣ሰይጣን ይህንን የምስጋና ጸሎት በሰማ ጊዜ ዓይኑ ይፈጣል ጥርሱ ይገጣል›› በማለት ገልጾታል፡፡ ስለዚህ አጋንንት ከሚጠላቸው እና ከሚረታባቸው ጸሎቶች ውስጥ አንዱ አርጋኖን ስለሆነ በርትተን እንጸልይ፡፡
የጸሎቱ ጠቀሜታ
ተወዳጆች ሆይ የአርጋኖን ጸሎት ጠቀሜታ ይህ ነው ተብሎ ለመግለጽ ቃላት ቢያጥርም ጸሎቱ በእመቤታችን ዘንድ ከፍተኛ መወድድንና ባለሟልነትን ያሰጣል፡፡ የእመቤታችን ጸጋና በረከት እንዲያድርብን ያደርጋል፡፡ የሚፈታተነንን አጋንንት ልምሾ ያደርጋል፡፡ ስለ እመቤታችን ቅድስናና ክብር በብዙ ያሳውቃል፡፡ በተለይ ብሉይ ኪዳንንና ሐዲስ ኪዳንን በሰፊው ስለሚዳስስ መንፈሳዊ እውቀታችንን ከፍ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም በሱባዔ ወቅት ለምሳሌ በገና፣በዓብይና በፍልሰታ አጽዋማት ወቅት በርትተን ብንጸልየው ምስጢር ይገልጻል፣ጥያቄያችን እንዲመለስ ያደርጋል፣ችግራችንን እንዲፈታ ያግዛል፡፡ የጸሎቱ ኃይል አጋንንትን ይቀጠቅጣል እንደ ሰም ያቀልጣል፡፡ በዚህም ድል መንሳትን ያጎናጽፈናል፡፡ ፀሎቱ ለአጋንንት ሬት ለእኛ ወተት በመሆኑ የእመቤታችንን ፍቅር ያበዛልናል።
በመጨረሻ የአርጋኖን ጸሎት ቡራኬ ‹‹ይህንን መጽሐፍ የሚያነብ ሁሉ አንደበቱ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት የጣፈጠ ከማር ወለላና ከሱካር ምንጭ ይልቅ የጣፈጠ ይሁን፡፡ በዚህ ጸሎት የሚጸልይ ሁሉ የሕይወት እሳትን በሚዳስስ እጅሽ በረከት የተባረከ ይሁን፡፡ የመንፈስ ቅዱስ መዓዛም በተዋሃደው አንደበትሽ የተመረቀ ይሁን፡፡ ዓለምን በያዙ በሥላሴ እጅ የተባረከ ይሁን›› /አርጋኖን ዘሰኑይ ገጽ 11/
ተወዳጆች ሆይ ‹‹በዓለ ሃምሳ፣እጅ ታጥቦ ወደ ምሳ›› የሚባለውን የአጅሬን ተረት ተወት እድርገን እናታችንን በአርጋኖን እናመስግናት፣ጸልየን ለጥያቄያችን መልስ እናግኝባት፡፡
ሚያዝያ 27/8/11 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ይህን ጸሎት በርትተን ከጸለይን የሚፈትነን መንፈስ ይያዝልናል፡፡ አባ ጊዮርጊስም አርጋኖንን ሰይጣን እንዴት እንደሚጠላው ሲገልጽ ‹‹ሰይፍ ነው አንገቱን ይቆርጠዋል፣መራጃ ነው ወገቡን ይሰብረዋል፣ሰይጣን ይህንን የምስጋና ጸሎት በሰማ ጊዜ ዓይኑ ይፈጣል ጥርሱ ይገጣል›› በማለት ገልጾታል፡፡ ስለዚህ አጋንንት ከሚጠላቸው እና ከሚረታባቸው ጸሎቶች ውስጥ አንዱ አርጋኖን ስለሆነ በርትተን እንጸልይ፡፡
የጸሎቱ ጠቀሜታ
ተወዳጆች ሆይ የአርጋኖን ጸሎት ጠቀሜታ ይህ ነው ተብሎ ለመግለጽ ቃላት ቢያጥርም ጸሎቱ በእመቤታችን ዘንድ ከፍተኛ መወድድንና ባለሟልነትን ያሰጣል፡፡ የእመቤታችን ጸጋና በረከት እንዲያድርብን ያደርጋል፡፡ የሚፈታተነንን አጋንንት ልምሾ ያደርጋል፡፡ ስለ እመቤታችን ቅድስናና ክብር በብዙ ያሳውቃል፡፡ በተለይ ብሉይ ኪዳንንና ሐዲስ ኪዳንን በሰፊው ስለሚዳስስ መንፈሳዊ እውቀታችንን ከፍ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም በሱባዔ ወቅት ለምሳሌ በገና፣በዓብይና በፍልሰታ አጽዋማት ወቅት በርትተን ብንጸልየው ምስጢር ይገልጻል፣ጥያቄያችን እንዲመለስ ያደርጋል፣ችግራችንን እንዲፈታ ያግዛል፡፡ የጸሎቱ ኃይል አጋንንትን ይቀጠቅጣል እንደ ሰም ያቀልጣል፡፡ በዚህም ድል መንሳትን ያጎናጽፈናል፡፡ ፀሎቱ ለአጋንንት ሬት ለእኛ ወተት በመሆኑ የእመቤታችንን ፍቅር ያበዛልናል።
በመጨረሻ የአርጋኖን ጸሎት ቡራኬ ‹‹ይህንን መጽሐፍ የሚያነብ ሁሉ አንደበቱ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት የጣፈጠ ከማር ወለላና ከሱካር ምንጭ ይልቅ የጣፈጠ ይሁን፡፡ በዚህ ጸሎት የሚጸልይ ሁሉ የሕይወት እሳትን በሚዳስስ እጅሽ በረከት የተባረከ ይሁን፡፡ የመንፈስ ቅዱስ መዓዛም በተዋሃደው አንደበትሽ የተመረቀ ይሁን፡፡ ዓለምን በያዙ በሥላሴ እጅ የተባረከ ይሁን›› /አርጋኖን ዘሰኑይ ገጽ 11/
ተወዳጆች ሆይ ‹‹በዓለ ሃምሳ፣እጅ ታጥቦ ወደ ምሳ›› የሚባለውን የአጅሬን ተረት ተወት እድርገን እናታችንን በአርጋኖን እናመስግናት፣ጸልየን ለጥያቄያችን መልስ እናግኝባት፡፡
ሚያዝያ 27/8/11 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የግእዝ ቁጥሮች በአኀዝና በፊደል
=====================
0. - አልቦ
1. ፩ አሐዱ
2. ፪ ክልኤቱ
3. ፫ ሠለስቱ
4. ፬ አርባዕቱ
5. ፭ ሐምስቱ
6. ፮ ስድስቱ
7. ፯ ስብዓቱ
8. ፰ ስመንቱ
9. ፱ ተሰዓቱ
10. ፲ አሠርቱ
11. ፲፩ አሠርቱ ወአሐዱ
12. ፲፪ አሠርቱ ወክልኤቱ
13. ፲፫ አሠርቱ ወሠለስቱ
14. ፲፬ አሠርቱ ወአርባዕቱ
15. ፲፭ አሠርቱ ወሐምስቱ
16. ፲፮ አሠርቱ ወስድስቱ
17. ፲፯ አሠርቱ ወሰብዓቱ
18. ፲፰ አሠርቱ ወስመንቱ
19. ፲፱ አሠርቱ ወተሰዓቱ
20. ፳ እስራ
21. ፳፩ እስራ ወአሐዱ
22. ፳፪ እስራ ወክልኤቱ
23. ፳፫ እስራ ወሠለስቱ
24. ፳፬ እስራ ወአርባዕቱ
25. ፳፭ እስራ ወሐምስቱ
26. ፳፮ እስራ ወስድስቱ
27. ፳፯ እስራ ወሰብዓቱ
28. ፳፰ እስራ ወሰመንቱ
29. ፳፱ እስራ ወተሰዓቱ
30. ፴ ሠላሳ
31. ፴፩ ሠላሳ ወአሐዱ
32. ፴፪ ሠላሳ ወክልኤቱ
33. ፴፫ ሠላሳ ወሠለስቱ
34. ፴፬ ሠላሳ ወአርባዕቱ
35. ፴፭ ሠላሳ ወሐምስቱ
36. ፴፮ ሠላሳ ወስድስቱ
37. ፴፯ ሠላሳ ወሰብዓቱ
38. ፴፰ ሠላሳ ወሰመንቱ
39. ፴፱ ሠላሳ ወተሰዓቱ
40. ፵ አርብዓ
50. ፶ ሃምሳ
60. ፷ ስድሳ
70. ፸ ሰብዓ
80. ፹ ሰማንያ
90. ፺ ተሰዓ
100. ፻ ምዕት
101. ፻፩ ምዕት ወአሐዱ
102. ፻፪ ምዕት ወክልኤቱ
103. ፻፫ ምዕት ወሠለስቱ
104. ፻፬ ምዕት ወአርባዕቱ
105. ፻፭ መዕት ወሐምስቱ
106. ፻፮ ምዕት ወስድስቱ
107. ፻፯ ምዕት ወሰብዓቱ
108. ፻፰ ምዕት ወስመንቱ
109. ፻፱ ምዕት ወተሰዓቱ
110. ፻፲ ምዕት ወአሠርቱ
111. ፻፲ወ፩ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ
112. ፻፲ወ፪ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ
113. ፻፲ወ፫ ምዕት አሠርቱ ወሠለስቱ
114. ፻፲ወ፬ ምዕት አሠርቱ ወአርባዕቱ
115. ፻፲ወ፭ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ
116. ፻፲ወ፮ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ
117. ፻፲ወ፯ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ
118. ፻፲ወ፰ ምዕት አሠርቱ ወስመንቱ
119. ፻፲ወ፱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ
120. ፻፳ ምዕት ወእስራ
130. ፻፴ ምዕት ወሠላሳ
140. ፻፵ ምዕት ወአርብዓ
150. ፻፶ ምዕት ወሃምሳ
160. ፻፷ ምዕት ወስድሳ
170. ፻፸ ምዕት ወሰብዓ
180. ፻፹ ምዕት ወሰማንያ
190. ፻፺ ምዕት ወተሰዓ
200. ፪፻ ክልኤቱ ምዕት
201. ፪፻ወ፩ ክልኤቱ ምዕት ወአሐዱ
202. ፪፻ወ፪ ክልኤቱ ምዕት ወክልኤቱ
203. ፪፻ወ፫ ክልኤቱ ምዕት ወሠለስቱ
204. ፪፻ወ፬ ክልኤቱ ምዕት ወአርባዕቱ
205. ፪፻ወ፭ ክልኤቱ ምዕት ወሐምስቱ
206. ፪፻ወ፮ ክልኤቱ ምዕት ወስድስቱ
207. ፪፻ወ፯ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓቱ
208. ፪፻ወ፰ ክለኤቱ ምዕት ወስመንቱ
209. ፪፻ወ፱ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓቱ
210. ፪፻ወ፲ ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ
211. ፪፻፲ወ፩ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ
212. ፪፻፲ወ፪ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ
213. ፪፻፲ወ፫ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሠልስቱ
214. ፪፻፲ወ፬ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአርባቱ
215. ፪፻፲ወ፭ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ
216. ፪፻፲ወ፮ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ
217. ፪፻፲ወ፯ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ
218. ፪፻፲ወ፰ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰመንቱ
219. ፪፻፲ወ፱ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ
220. ፪፻፳ ክልኤቱ ምዕት ወእስራ
230. ፪፻፴ ክልኤቱ ምሪዕት ወሠላሳ
240. ፪፻፵ ክልኤቱ ምዕት ወአርብዓ
250. ፪፻፶ ክልኤቱ ምዕት ወሃምሳ
260. ፪፻፷ ክልኤቱ ምዕት ወስድሳ
270. ፪፻፸ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓ
280. ፪፻፹ ክልኤቱ ምዕት ወሰማንያ
290. ፪፻፺ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓ
300. ፫፻ ሠለስቱ ምዕት
400. ፬፻ አርባዕቱ ምዕት
500. ፭፻ ሐምስቱ ምዕት
600. ፮፻ ስድስቱ ምዕት
700. ፯፻ ስብዓቱ ምዕት
800. ፰፻ ስመንቱ ምዕት
900. ፱፻ ተሰዓቱ ምዕት
1000. ፲፻ አሠርቱ ምዕት
2000. ፳፻ እስራ ምዕት
30
=====================
0. - አልቦ
1. ፩ አሐዱ
2. ፪ ክልኤቱ
3. ፫ ሠለስቱ
4. ፬ አርባዕቱ
5. ፭ ሐምስቱ
6. ፮ ስድስቱ
7. ፯ ስብዓቱ
8. ፰ ስመንቱ
9. ፱ ተሰዓቱ
10. ፲ አሠርቱ
11. ፲፩ አሠርቱ ወአሐዱ
12. ፲፪ አሠርቱ ወክልኤቱ
13. ፲፫ አሠርቱ ወሠለስቱ
14. ፲፬ አሠርቱ ወአርባዕቱ
15. ፲፭ አሠርቱ ወሐምስቱ
16. ፲፮ አሠርቱ ወስድስቱ
17. ፲፯ አሠርቱ ወሰብዓቱ
18. ፲፰ አሠርቱ ወስመንቱ
19. ፲፱ አሠርቱ ወተሰዓቱ
20. ፳ እስራ
21. ፳፩ እስራ ወአሐዱ
22. ፳፪ እስራ ወክልኤቱ
23. ፳፫ እስራ ወሠለስቱ
24. ፳፬ እስራ ወአርባዕቱ
25. ፳፭ እስራ ወሐምስቱ
26. ፳፮ እስራ ወስድስቱ
27. ፳፯ እስራ ወሰብዓቱ
28. ፳፰ እስራ ወሰመንቱ
29. ፳፱ እስራ ወተሰዓቱ
30. ፴ ሠላሳ
31. ፴፩ ሠላሳ ወአሐዱ
32. ፴፪ ሠላሳ ወክልኤቱ
33. ፴፫ ሠላሳ ወሠለስቱ
34. ፴፬ ሠላሳ ወአርባዕቱ
35. ፴፭ ሠላሳ ወሐምስቱ
36. ፴፮ ሠላሳ ወስድስቱ
37. ፴፯ ሠላሳ ወሰብዓቱ
38. ፴፰ ሠላሳ ወሰመንቱ
39. ፴፱ ሠላሳ ወተሰዓቱ
40. ፵ አርብዓ
50. ፶ ሃምሳ
60. ፷ ስድሳ
70. ፸ ሰብዓ
80. ፹ ሰማንያ
90. ፺ ተሰዓ
100. ፻ ምዕት
101. ፻፩ ምዕት ወአሐዱ
102. ፻፪ ምዕት ወክልኤቱ
103. ፻፫ ምዕት ወሠለስቱ
104. ፻፬ ምዕት ወአርባዕቱ
105. ፻፭ መዕት ወሐምስቱ
106. ፻፮ ምዕት ወስድስቱ
107. ፻፯ ምዕት ወሰብዓቱ
108. ፻፰ ምዕት ወስመንቱ
109. ፻፱ ምዕት ወተሰዓቱ
110. ፻፲ ምዕት ወአሠርቱ
111. ፻፲ወ፩ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ
112. ፻፲ወ፪ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ
113. ፻፲ወ፫ ምዕት አሠርቱ ወሠለስቱ
114. ፻፲ወ፬ ምዕት አሠርቱ ወአርባዕቱ
115. ፻፲ወ፭ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ
116. ፻፲ወ፮ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ
117. ፻፲ወ፯ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ
118. ፻፲ወ፰ ምዕት አሠርቱ ወስመንቱ
119. ፻፲ወ፱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ
120. ፻፳ ምዕት ወእስራ
130. ፻፴ ምዕት ወሠላሳ
140. ፻፵ ምዕት ወአርብዓ
150. ፻፶ ምዕት ወሃምሳ
160. ፻፷ ምዕት ወስድሳ
170. ፻፸ ምዕት ወሰብዓ
180. ፻፹ ምዕት ወሰማንያ
190. ፻፺ ምዕት ወተሰዓ
200. ፪፻ ክልኤቱ ምዕት
201. ፪፻ወ፩ ክልኤቱ ምዕት ወአሐዱ
202. ፪፻ወ፪ ክልኤቱ ምዕት ወክልኤቱ
203. ፪፻ወ፫ ክልኤቱ ምዕት ወሠለስቱ
204. ፪፻ወ፬ ክልኤቱ ምዕት ወአርባዕቱ
205. ፪፻ወ፭ ክልኤቱ ምዕት ወሐምስቱ
206. ፪፻ወ፮ ክልኤቱ ምዕት ወስድስቱ
207. ፪፻ወ፯ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓቱ
208. ፪፻ወ፰ ክለኤቱ ምዕት ወስመንቱ
209. ፪፻ወ፱ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓቱ
210. ፪፻ወ፲ ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ
211. ፪፻፲ወ፩ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ
212. ፪፻፲ወ፪ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ
213. ፪፻፲ወ፫ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሠልስቱ
214. ፪፻፲ወ፬ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአርባቱ
215. ፪፻፲ወ፭ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ
216. ፪፻፲ወ፮ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ
217. ፪፻፲ወ፯ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ
218. ፪፻፲ወ፰ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰመንቱ
219. ፪፻፲ወ፱ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ
220. ፪፻፳ ክልኤቱ ምዕት ወእስራ
230. ፪፻፴ ክልኤቱ ምሪዕት ወሠላሳ
240. ፪፻፵ ክልኤቱ ምዕት ወአርብዓ
250. ፪፻፶ ክልኤቱ ምዕት ወሃምሳ
260. ፪፻፷ ክልኤቱ ምዕት ወስድሳ
270. ፪፻፸ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓ
280. ፪፻፹ ክልኤቱ ምዕት ወሰማንያ
290. ፪፻፺ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓ
300. ፫፻ ሠለስቱ ምዕት
400. ፬፻ አርባዕቱ ምዕት
500. ፭፻ ሐምስቱ ምዕት
600. ፮፻ ስድስቱ ምዕት
700. ፯፻ ስብዓቱ ምዕት
800. ፰፻ ስመንቱ ምዕት
900. ፱፻ ተሰዓቱ ምዕት
1000. ፲፻ አሠርቱ ምዕት
2000. ፳፻ እስራ ምዕት
30
00. ፴፻ ሠላሳ ምዕት
4000. ፵፻ አርብዓ ምዕት
5000. ፶፻ ሃምሳ ምዕት
6000. ፷፻ ሳድስ ምዕት
7000. ፸፻ ሰብዓ ምዕት
8000. ፹፻ ሰማንያ ምዕት
9000. ፺፻ ተሰዓ ምዕት
10,000. ፻፻ እልፍ
20,000. ፪፻፻ ክልኤቱ እልፍ
30,000. ፫፻፻ ሠለስቱ እልፍ
40,000. ፬፻፻ አርባዕቱ እልፍ
50,000. ፭፻፻ ሐምስቱ እልፍ
60,000. ፮፻፻ ስድስቱ እልፍ
70,000. ፯፻፻ ሰብዓቱ እልፍ
80,000. ፰፻፻ ስመንቱ እልፍ
90,000. ፱፻፻ ተሰዓቱ እልፍ
100,000. ፲፻፻ አሠርቱ እልፍ
200,000. ፳፻፻ እስራ እልፍ
300,000. ፴፻፻ ሠላሳ እልፍ
400,000. ፵፻፻ አርብዓ እልፍ
500,000. ፶፻፻ ሃምሳ እልፍ
600,000. ፷፻፻ ስድሳ እልፍ
700,000. ፸፻፻ ሰብዓ እልፍ
800,000. ፹፻፻ ሰማንያ እልፍ
900,000 ፺፻፻ ተሰዓ እልፍ
1,000,000 ፻፻፻ አእላፋት
10,000,000 ፲፻፻፻ ትእልፊት
100,000,000. ፻፻፻፻ ትልፊታት
1,000,000,000. ፲፻፻፻፻ ምእልፊት
4000. ፵፻ አርብዓ ምዕት
5000. ፶፻ ሃምሳ ምዕት
6000. ፷፻ ሳድስ ምዕት
7000. ፸፻ ሰብዓ ምዕት
8000. ፹፻ ሰማንያ ምዕት
9000. ፺፻ ተሰዓ ምዕት
10,000. ፻፻ እልፍ
20,000. ፪፻፻ ክልኤቱ እልፍ
30,000. ፫፻፻ ሠለስቱ እልፍ
40,000. ፬፻፻ አርባዕቱ እልፍ
50,000. ፭፻፻ ሐምስቱ እልፍ
60,000. ፮፻፻ ስድስቱ እልፍ
70,000. ፯፻፻ ሰብዓቱ እልፍ
80,000. ፰፻፻ ስመንቱ እልፍ
90,000. ፱፻፻ ተሰዓቱ እልፍ
100,000. ፲፻፻ አሠርቱ እልፍ
200,000. ፳፻፻ እስራ እልፍ
300,000. ፴፻፻ ሠላሳ እልፍ
400,000. ፵፻፻ አርብዓ እልፍ
500,000. ፶፻፻ ሃምሳ እልፍ
600,000. ፷፻፻ ስድሳ እልፍ
700,000. ፸፻፻ ሰብዓ እልፍ
800,000. ፹፻፻ ሰማንያ እልፍ
900,000 ፺፻፻ ተሰዓ እልፍ
1,000,000 ፻፻፻ አእላፋት
10,000,000 ፲፻፻፻ ትእልፊት
100,000,000. ፻፻፻፻ ትልፊታት
1,000,000,000. ፲፻፻፻፻ ምእልፊት