☘ልሳን☘
☘☘☘
አንድ ኢትዮጵያዊ ካህን ከባሕር ማዶ ለትምህርት ተልኮ ሳለ ክርስቲያን ነን የሚሉት ነጮቹ በአንድ አዳራሽ ተሰብስበው እንደ ሃገር ቤቱ ዛር ቤት ሲጯጯሁ ይሰማና የጤና ስላልመሰለው ጠጋ ብሎ ይጠይቃል። ተጠያቂዎቹም "መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸው በልሳን እየተናገሩ ነው" ሲሉ ይመልሳሉ።
ሻሽ ባለመጠምጠሙ ትኩረት ሰጥቶ የሚከታተለው ስለሌለ እስኪ ጉዳያቸውን ልይ ከበረታሁም ፈተና አቀርብላቸዋለው ብሎ ወደ አዳራሹ ይዘልቃል።
መሪ የለ ተመሪ ከመድረኩ ላይና ከመድረኩ በታች ግማሹ ሽር ሽር እያለ፣ ከፊሉ ምድር ላይ እየተንፈራፈረ ከሰው ልጅ ሥርዓት ውጪ በሆነ መልኩ ይጯጯሃል። ኢትዮጵያዊው ካህን አንድ ነገር አሰበ አስቦም አልቀረ ፈጸመው።
ከመዝሙረ ዳዊት ውስጥ መዝሙር አንዱን በግእዝ ልሳን ልበለውና መተርጎም አለመተርጎማቸውን ልፈትን ብሎ ዘሎ መድረካቸው ላይ ወጣና ከመዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ አንድ ላይ ወስዶ በቅድሚያ እየደጋገመ ፍካሬ ፍካሬ ፍካሬ! አለ ቀጠለና..
"ፍካሬ ዘጻድቃን ወዘኃጥኣን መዝሙር ዘዳዊት ሃሌሉያ ብፁዕ ብእሲ ዘኢሖረ በምክረ ረሲአን ወዘኢቆመ ውስተ ፍኖተ ኃጥኣን.......እያለ እስከ ፍጻሜው ዘለቀውና ሲጨርስ ቀጥ ብሎ ቆመ።
የመድረኩ መሪ ጮሌ ፈረንጅ ሮጦ መጣና ለአዳራሹ ሕዝብ "ሃሌሉያ ጌታ የተመሰገነ ይሁን" ብሎ ካስጮሃቸው በኋላ ትርጉሙን ስሙ አለና እንዲህ ተረጎመው "እኔ አንድ ጥቁር አፍሪካዊ በነጮች መካከል ተገኝቼ ጌታን በመቀበሌና በልሳን በመናገሬ እጅግ በጣም ተደስቻለሁ" ይላል ብሎ ተረጎመው። አዳራሹ በጩኸትና በጭብጨባ አስተጋባ ይኼኔ ኢትዮጵያዊው ቄስ አዝኖ ተሳልቆባቸው ወጥቶ ሄደ።
🍇 🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇
ትርጉሙ ይሄ ነበር..." ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ።"
(መዝሙረ ዳዊት 1:1).......
ወገኖቼ በዚህ ዓይነት የማታለል ድርጊት የጠፋ ወደገኖቻችን ብዙ ናቸው። ለእነዚህ ነፍሳት መጥፋት ተጠያቂዎች ደግሞ አይወቅብንም ብለው ባፈጠጠ ውሸት በሃይማኖት ስም በሕዝባችን ላይ የሚጫወቱት ጊዜ የሰጣቸው መናፍቃን ናቸው። መንፈስ ቅዱስ የእውነት መንፈስ ነው።
መንፈስ ተሞላን እያሉ መዋሸት ፣ አረፋ እስኪደፍቁ መንፈራገጥ፣ ቅዱሳንንም መስደብና መንቀፍም አይገባም
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
☘☘☘
አንድ ኢትዮጵያዊ ካህን ከባሕር ማዶ ለትምህርት ተልኮ ሳለ ክርስቲያን ነን የሚሉት ነጮቹ በአንድ አዳራሽ ተሰብስበው እንደ ሃገር ቤቱ ዛር ቤት ሲጯጯሁ ይሰማና የጤና ስላልመሰለው ጠጋ ብሎ ይጠይቃል። ተጠያቂዎቹም "መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸው በልሳን እየተናገሩ ነው" ሲሉ ይመልሳሉ።
ሻሽ ባለመጠምጠሙ ትኩረት ሰጥቶ የሚከታተለው ስለሌለ እስኪ ጉዳያቸውን ልይ ከበረታሁም ፈተና አቀርብላቸዋለው ብሎ ወደ አዳራሹ ይዘልቃል።
መሪ የለ ተመሪ ከመድረኩ ላይና ከመድረኩ በታች ግማሹ ሽር ሽር እያለ፣ ከፊሉ ምድር ላይ እየተንፈራፈረ ከሰው ልጅ ሥርዓት ውጪ በሆነ መልኩ ይጯጯሃል። ኢትዮጵያዊው ካህን አንድ ነገር አሰበ አስቦም አልቀረ ፈጸመው።
ከመዝሙረ ዳዊት ውስጥ መዝሙር አንዱን በግእዝ ልሳን ልበለውና መተርጎም አለመተርጎማቸውን ልፈትን ብሎ ዘሎ መድረካቸው ላይ ወጣና ከመዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ አንድ ላይ ወስዶ በቅድሚያ እየደጋገመ ፍካሬ ፍካሬ ፍካሬ! አለ ቀጠለና..
"ፍካሬ ዘጻድቃን ወዘኃጥኣን መዝሙር ዘዳዊት ሃሌሉያ ብፁዕ ብእሲ ዘኢሖረ በምክረ ረሲአን ወዘኢቆመ ውስተ ፍኖተ ኃጥኣን.......እያለ እስከ ፍጻሜው ዘለቀውና ሲጨርስ ቀጥ ብሎ ቆመ።
የመድረኩ መሪ ጮሌ ፈረንጅ ሮጦ መጣና ለአዳራሹ ሕዝብ "ሃሌሉያ ጌታ የተመሰገነ ይሁን" ብሎ ካስጮሃቸው በኋላ ትርጉሙን ስሙ አለና እንዲህ ተረጎመው "እኔ አንድ ጥቁር አፍሪካዊ በነጮች መካከል ተገኝቼ ጌታን በመቀበሌና በልሳን በመናገሬ እጅግ በጣም ተደስቻለሁ" ይላል ብሎ ተረጎመው። አዳራሹ በጩኸትና በጭብጨባ አስተጋባ ይኼኔ ኢትዮጵያዊው ቄስ አዝኖ ተሳልቆባቸው ወጥቶ ሄደ።
🍇 🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇
ትርጉሙ ይሄ ነበር..." ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ።"
(መዝሙረ ዳዊት 1:1).......
ወገኖቼ በዚህ ዓይነት የማታለል ድርጊት የጠፋ ወደገኖቻችን ብዙ ናቸው። ለእነዚህ ነፍሳት መጥፋት ተጠያቂዎች ደግሞ አይወቅብንም ብለው ባፈጠጠ ውሸት በሃይማኖት ስም በሕዝባችን ላይ የሚጫወቱት ጊዜ የሰጣቸው መናፍቃን ናቸው። መንፈስ ቅዱስ የእውነት መንፈስ ነው።
መንፈስ ተሞላን እያሉ መዋሸት ፣ አረፋ እስኪደፍቁ መንፈራገጥ፣ ቅዱሳንንም መስደብና መንቀፍም አይገባም
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
የወፏ__ምክር
🦆🦆🦆🦆
አንድ ሰው አንዲት በጣም ቆንጆ ወፍ በመዳፉ ውስጥ ይዞ ጨምቆ ሊገድላት ሲል ከመሞቷ በፊት አንድ ወይም ሁለት ቃላት ትናገር ዘንድ እንዲፈቅድላት ጠየቀችው፡፡
እንዲህም አለች “እባክህ አትግደለኝ፡፡ ሶስት ጠቃሚ ምክሮችን እሰጥሃለሁ፡፡ የመጀመሪያው ምክር፤ በእጅህ ያለውን ነገር አትልቀቅ፡፡ ሁለተኛው ምክር፤ ስለሆነው ነገር ሁሉ አትቆጭ፡፡” ካለችው በኋላ ዝም አለች፡፡
ሶስተኛውንም ምክር ትነግረው ዘንድ ሲጠይቃት “ሶስተኛው ምክር ለልጆችህና ለልጅ ልጆችህ በጣም ጠቃሚ ስለሆነ ካለቀከኝ አልነግርህም፡፡” አለችው፡፡
በዚህ ጊዜ ሰውየው ሶስተኛውን ምክር ለመስማት በጣም ጓጉቶ ስለነበረ ወፏን ሲለቃት ከአንድ ዛፍ ላይ በርራ ወጥታ “ምንድን ነበር ያልኩህ? ታስታውሳለህ?” ብላ ጠየቀችው፡፡ እርሱም “በእጅህ ያለውን ነገር አትልቀቅ ነው ያልሺኝ፡፡” አላት፡፡ “ሁለተኛውስ?” “ስላለፈው ነገር ሁሉ አትቆጭ፡፡”“አዎ፡፡ ነገር ግን የነገርኩህን ነገር አልተቀበልክም፡፡ ባትለቀኝ ኖሮ ከሆዴ ውስጥ ለልጅ ልጆችህ የሚሆን ወርቅ ታገኝ ነበር፡፡ ይኸው ነው፡፡” አለችው፡፡
ሰውየው “ሶስተኛውስ ታዲያ?” አላት፡፡
እሷም “ሶስተኛው የሁለተኛው ምክር ድጋሚ ነው፡፡ ስላጣኸው ነገር አትቆጭ፡፡ ይኸው
ነው፡፡ ደህና ሁን፡፡ ብላው በራ ሄደች።
🐦🐤🐦🐤🐦🐤🐦🐤🐦🐤🐦🐤
ክርስቲያን በህይወት ዘመኑ ጠቢብ፣ ብልህ፣አስተዋይ መሆን አለበት ለሂወቱ የሚጠቅመውን ነገር አጥብቆ ሊይዝ ይገባዋል።
ያለፈውን ነገር እያሰበ አይቆጭም ለወደፊቱ ይማራል እንጂ
" እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 10:16)
🍇መልካም ሰንበት🍇
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
🦆🦆🦆🦆
አንድ ሰው አንዲት በጣም ቆንጆ ወፍ በመዳፉ ውስጥ ይዞ ጨምቆ ሊገድላት ሲል ከመሞቷ በፊት አንድ ወይም ሁለት ቃላት ትናገር ዘንድ እንዲፈቅድላት ጠየቀችው፡፡
እንዲህም አለች “እባክህ አትግደለኝ፡፡ ሶስት ጠቃሚ ምክሮችን እሰጥሃለሁ፡፡ የመጀመሪያው ምክር፤ በእጅህ ያለውን ነገር አትልቀቅ፡፡ ሁለተኛው ምክር፤ ስለሆነው ነገር ሁሉ አትቆጭ፡፡” ካለችው በኋላ ዝም አለች፡፡
ሶስተኛውንም ምክር ትነግረው ዘንድ ሲጠይቃት “ሶስተኛው ምክር ለልጆችህና ለልጅ ልጆችህ በጣም ጠቃሚ ስለሆነ ካለቀከኝ አልነግርህም፡፡” አለችው፡፡
በዚህ ጊዜ ሰውየው ሶስተኛውን ምክር ለመስማት በጣም ጓጉቶ ስለነበረ ወፏን ሲለቃት ከአንድ ዛፍ ላይ በርራ ወጥታ “ምንድን ነበር ያልኩህ? ታስታውሳለህ?” ብላ ጠየቀችው፡፡ እርሱም “በእጅህ ያለውን ነገር አትልቀቅ ነው ያልሺኝ፡፡” አላት፡፡ “ሁለተኛውስ?” “ስላለፈው ነገር ሁሉ አትቆጭ፡፡”“አዎ፡፡ ነገር ግን የነገርኩህን ነገር አልተቀበልክም፡፡ ባትለቀኝ ኖሮ ከሆዴ ውስጥ ለልጅ ልጆችህ የሚሆን ወርቅ ታገኝ ነበር፡፡ ይኸው ነው፡፡” አለችው፡፡
ሰውየው “ሶስተኛውስ ታዲያ?” አላት፡፡
እሷም “ሶስተኛው የሁለተኛው ምክር ድጋሚ ነው፡፡ ስላጣኸው ነገር አትቆጭ፡፡ ይኸው
ነው፡፡ ደህና ሁን፡፡ ብላው በራ ሄደች።
🐦🐤🐦🐤🐦🐤🐦🐤🐦🐤🐦🐤
ክርስቲያን በህይወት ዘመኑ ጠቢብ፣ ብልህ፣አስተዋይ መሆን አለበት ለሂወቱ የሚጠቅመውን ነገር አጥብቆ ሊይዝ ይገባዋል።
ያለፈውን ነገር እያሰበ አይቆጭም ለወደፊቱ ይማራል እንጂ
" እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 10:16)
🍇መልካም ሰንበት🍇
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
“ልጆቼ! ሓኪሞች ብትሆኑ፣ መሀንዲሶች ብትሆኑ፣ የሽመና ሠራተኞች ብትሆኑ፣ መርከበኞችም ብትሆኑ መልካም ነው፡፡ ይህን ጥበብ መማራችሁም ጥሩ ነው፡፡ እኔ ግን ከዚህ የበለጠ ጥበብ አሳያችኋለሁ፡፡ በዚህ (በተማራችሁት ምድራዊ) ጥበባችሁም ሌላ ጥበብ ትማሩበት ዘንድ እማልዳችኋለሁ፡፡ ሰማያዊን ጥበብ! ከላይ በገልጽኩላችሁና እናንተ በተማራችሁት ጥበብ ተጠቅማችሁ ገንዘብ ማግኘታችሁ አይቀርም፡፡ በዚህ ገንዘባችሁ ግን ድሆችን መርዳት ልመዱበት፡፡ ይህ የምነግራችሁን ጥበብ እንደ ቀላል የምታዩት አትሁኑ፡፡ መሀንዲሶች ብትሆኑ በምህንድስና ጥበባችሁና እውቀታችሁ በዚህ ምድር የሚያማምሩ ቪላ ቤቶችን ልትሠሩ ትችላላችሁ፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን
በመንግሥተ ሰማያት ውስጥ የዘላለም ቤታችሁን ትሠራላችሁ፡፡ በዚህ ምድር ለምትሠሩት ቤታችሁ በጣም ብዙ ወጪ ብዙም ድካም ይጠይቃችኋል፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን ብዙ ልፋት የለውም፡፡ ወጪአችሁ መልካምና ፈቃደኛ መሆን ብቻ ነው፡፡ በዚህ ምድር ለምትሠሩት ቤት የተለያዩ ዓይነት ብረቶችና ማቅለጫዎች እንዲሁም የከበሩ ድንጋዮችን ትጠቀማላችሁ፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን ይህ ሁሉ አያስፈልጋችሁም፡፡ የሚያስፈልጋችሁ ብሎን ወይንም ብረት ወይንም የከበረ ድንጋይ ሳይሆን መልካም ምግባራችሁና በጎ ፈቃዳችሁ ብቻ ነው፡፡
እንደውም እኔ እነዚህ የተማራችኋቸው ጥበቦች ጥበብ ብዬ ለመጥራት በጣም እቸገራለሁ፡፡ ለምን ብትሉኝ ከምነግራችሁ ጥበብ ጋር ሳወዳድራቸው በጣም ስለሚያንሱብኝ አያያዛቸው ላላወቀበት ሰውም ብዙ ጉዳት ስለሚያመጡ፡፡ እስኪ አስተውሉት! አንድ ሰው በዚህ ምድር ባገኘው ጥበብና ገንዘብ ተጠቅሞ ድሆችን መርዳት ሲገባው አላግባብ ሲበላ ሲጠጣ በኋላ ግን በስኳር፣ በሪህ፣ በቁርጥማት፣ በራስ ምታት፣ በልብና በኩላሊት በሽታ የሚሰቃይ ከሆነ ይህ ጥበብ እለው ዘንድ እንዴት እደፍራለሁ? እንግዲያውስ ጥበባችሁ ጥበብ ይሁንላችሁ፡፡ ጥበባችሁ ለሥጋችሁም ለነፍሳችሁም የሚጠቅም እንጂ በዚህ ዓለምም ይሁን በሚመጣው ዓለም የሚጎዳችሁ አይሁን፡፡”
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
በመንግሥተ ሰማያት ውስጥ የዘላለም ቤታችሁን ትሠራላችሁ፡፡ በዚህ ምድር ለምትሠሩት ቤታችሁ በጣም ብዙ ወጪ ብዙም ድካም ይጠይቃችኋል፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን ብዙ ልፋት የለውም፡፡ ወጪአችሁ መልካምና ፈቃደኛ መሆን ብቻ ነው፡፡ በዚህ ምድር ለምትሠሩት ቤት የተለያዩ ዓይነት ብረቶችና ማቅለጫዎች እንዲሁም የከበሩ ድንጋዮችን ትጠቀማላችሁ፡፡ በምነግራችሁ ጥበብ ግን ይህ ሁሉ አያስፈልጋችሁም፡፡ የሚያስፈልጋችሁ ብሎን ወይንም ብረት ወይንም የከበረ ድንጋይ ሳይሆን መልካም ምግባራችሁና በጎ ፈቃዳችሁ ብቻ ነው፡፡
እንደውም እኔ እነዚህ የተማራችኋቸው ጥበቦች ጥበብ ብዬ ለመጥራት በጣም እቸገራለሁ፡፡ ለምን ብትሉኝ ከምነግራችሁ ጥበብ ጋር ሳወዳድራቸው በጣም ስለሚያንሱብኝ አያያዛቸው ላላወቀበት ሰውም ብዙ ጉዳት ስለሚያመጡ፡፡ እስኪ አስተውሉት! አንድ ሰው በዚህ ምድር ባገኘው ጥበብና ገንዘብ ተጠቅሞ ድሆችን መርዳት ሲገባው አላግባብ ሲበላ ሲጠጣ በኋላ ግን በስኳር፣ በሪህ፣ በቁርጥማት፣ በራስ ምታት፣ በልብና በኩላሊት በሽታ የሚሰቃይ ከሆነ ይህ ጥበብ እለው ዘንድ እንዴት እደፍራለሁ? እንግዲያውስ ጥበባችሁ ጥበብ ይሁንላችሁ፡፡ ጥበባችሁ ለሥጋችሁም ለነፍሳችሁም የሚጠቅም እንጂ በዚህ ዓለምም ይሁን በሚመጣው ዓለም የሚጎዳችሁ አይሁን፡፡”
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
Forwarded from የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጽሑፎች በPDF እና በድምጽ
❖♥ ታቦተ ጽዮን የአምላክ እናት♥❖
[በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
❖✔♥ የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ የኾነቺው በወርቅ የተለበጠችው ይቺ የእግዚአብሔር ታቦት፤ በንጽሕና በቅድስና የተጌጠችው የእግዚአብሔር ወልድ እናት የኾነቺው የአማናዊት ታቦት የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡
❖✔♥ በመጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ ፪ ቊጥር ፲፪ትን እንደምናነበው፤ ታቦተ ጽዮንን ያገለግሉ የነበሩት የካህኑ የኤሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ በሠሩት ታላቅ ኀጢአት ምክንያት እግዚአብሔር ዐዝኖባቸው የክብሩ መገለጫ የኾነችው ታቦት በፍልስጤማውያን እጅ እንድትማረክ አደረገ፤ ፍልስጤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቤንኤዘር ወደ አዛጦን በመውሰድ በድፍረት ከዳጎን አጠገብ አኖሯት፤ ነገር ግን ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ወድቆ ተገኘ፤ እነሱም እንደገና ዳጎንን ወደ ስፍራው መልሰው ኼዱ፤ በነጋታው ለማየት ሲመጡ የዳጎን እጅ እግሩ ተቆራርጠው ደረቱ ለብቻው ወድቆ ተገኘ፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይኽነን ታሪክ ይዞ ‹‹የእግዚአብሔር ታቦትንስ በጣዖት ቤት ውስጥ የሚያኖር ማን ነው?›› (፪ቆሮ ፮፥፲፮) በማለት የታቦትን ክብር አስተምሮበታል፡፡
❖✔♥ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅም በሰቈቃወ ድንግል መጽሐፉ ላይ የአምላክ ማደሪያ የኾነችው ታቦት ወደ ፍልስጤም ሀገር ኼዳ ዳጎንን ሰባብራ እንዳጠፋች ኹሉ፤ አማናዊት የጌታ ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታን ይዛ ወደ ግብጽ በተሰደደች ጊዜ የግብጽ ጣዖታት ኹሉ እየተሰባበሩ መውደቃቸውን ሲገልጹ፡-
"ታቦተ አምላከ እስራኤል ጽዮን ዘነገደት ምድረ ኢሎፍሊ
ወቀጥቀጠቶ ለዳጎን ነፍሳተ ብዙኃን ማህጎሊ
አመ ነገደት ቊስቋመ በኀይለ ወልዳ ከሃሊ
ወድቁ አማልክተ ግብጽ መናብርተ ሰይጣን ሐባሊ
ወተኀፍሩ ኲሎሙ ዘቦሙ አስጋሊ"
(ወደ ኢሎፍሊ ምድር ተማርካ የኼደች የእስራኤል አምላክ የቃል ኪዳኑ ታቦት ታቦተ ጽዮን፤ የብዙዎችን ነፍሳት ያጠፋ ዳጎንን ሰባበረችው፤ በዚች ታቦት የተመሰለች ድንግል ማርያምም ኹሉን ማድረግ ከሚችል ከልጇ ጋር ግብጽ ወደሚባል አገር በኼደች ጊዜ፤የሐሰተኛ ሰይጣን ዘፋኖች የኾኑ የግብጽ ጣዖታት ፈረሱ፤ ጠንቋይ አስጠንቋይ ያላቸው ኹሉ ዐፈሩ) በማለት አነጻጽሯል፡፡
❖✔♥ በእግዚአብሔር ታቦት ላይ ስለሠሩት ታላቅ የድፍረት ኀጢአት እግዚአብሔር ቀጣቸው ብዙዎቹ ሞቱ፤ ያልሞቱትም በእባጭ ተመቱ፤ የአይጥ መንጋም ምድራቸውን አጠፋባቸው፤ ያን ጊዜ በእግዚአብሔር ታቦት ላይ ምን እናድርግ? ወደ ስፍራው በምን እንስደደው? ብለው በመማከር፤ የሚያጠቡ ቀንበር ያልተጫነባቸው ኹለት ላሞችን በመውሰድ፤ በዐዲስ ሠረገላ ጠምደው እንቦሶቻቸውን (ጥጆቻቸውን) ከቤት ዘግተው በማስቀረት፤ ታቦተ ጽዮንን እጅ መንሻውን በሠረገላው ላይ ጫኑ፤ ያን ጊዜ እነዚኽ ላሞች ጥጆቻቸውን ሳይናፍቁ ወደቀኝ ወደግራ ሳይሉ እምቧ እያሉ ወደ ቤተ ሳሚስ ወደሚወስደው መንገድ ታቦተ ጽዮንን ይዘው ገሠገሡ፤ ሠረገላውም ወደ ቤትሳሚሳዊው ወደ ኢያሱ እርሻ ሲደርስ ያን ጊዜ ሌዋውያን ታቦት ጽዮንና ዐብሮ የነበረውን የወርቅ ዕቃ አውርደው በታላቅ ደንጊያ ላይ በማኖር፤ ሠረገላውን ፈልጠው ጊደሮቹን ሠውተዋቸዋል፡፡
❖✔♥ ይኽም ለጊዜው ቢደረግም ለኋላው ግን ምሳሌ ነበር፤ ላሞቹ የሰማዕታት፤ ልጆች የልጆቻቸው፤ ሠረገላ የመስቀል፤ ልጆቻቸውን ከወደኋላ እንዳስቀሩ፤ ሰማዕታትም የልጅ የገንዘብ ፍቅር አያስቀራቸውምና፣ ሠረገላውን ፈልጠው እንደሠዋቸው ራሳቸውን በመስቀል ይሠዋሉና በማለት የብሉይ ኪዳን መተርጒማን ያመሰጥሩታል፡፡
❖✔♥ የመልክአ ማርያም ደራሲ የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ የኾነችውን የኻያ መንፈቅ ማለት ዐሥሩ ቃላት የተጻፉባቸው ጽላት የተቀመጡባትን የእግዚአብሔርን ታቦት ጊደሮቹ ከልጆቻቸው ይልቅ በማስበለጥና በመውደድ ይዘዋት ወደፊት እንደነጎዱ፤ ርሱም የልዑል ማደሪያ ለኾነችው ለቅድስት ድንግል ማርያም ያለውን ጥልቅ ፍቅር በድርሰቱ ላይ፡-
"ማርያም ጽዮን ታቦት ቃለ ጽድቅ መንፈቀ ዕሥራ
ዕጐላት እምዕጐሊሆን ከመ ኪያኪ አፍቀራ
አፍቀርኩኪ አፍቅርኒ እምይእዜ ለግሙራ"
(የኻያ እኩሌታ የሚኾን የእውነት ቃል ማደሪያ ጽዮን ማርያም ሆይ፤ ጊደሮች ከጥጆቻቸው ይልቅ አንቺን እንደአፈቀሩ፤ ወድጄሻለኹና ከዛሬ ዠምሮ ፈጽሞ ውደጅኝ) በማለት ገልጦታል፡፡
❖✔♥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በምስጢር በመራቀቅ "አንቲ ውእቱ ጽዮን ታቦተ አምላከ እስራኤል እንተ ነገደት ምድረ ኢሎፍሊ፤ ወበህየ አውደቀቶ ለዳጎን..." (ወደ ኢሎፍሊ ምድር የኼደች የእስራኤል አምላክ ታቦት (ማደሪያ) ጽዮን አንቺ ነሽ፤ በዚያም ዳጎንን የጣለችው ጣዖት አምላኪዎቹንም የቀሠፈቻቸው፤ በአመጣጧም ከአዛጦን ሰዎች ካሳን የተቀበለች፤ ከካሳዋም ጋር እንቦሳ ባላቸው ላሞች አስጭነው የሸኟት፤ ከርሷም ጋር የወርቅ ሳጥኖችን በጐኗም፤ የበድን ሣጥን ሥርዐትን አልሠሩም፤ ነገር ግን በርሷ ዘንድ ካለ ከወርቅ መሣሪያና ከሣጥን ጋራ ላኳት፤ በእንግድነቷ ወቅትም በአሳደራት ጊዜ ወደ ቤቱ በመግባቷ እግዚአብሔር የአቢዳራን ቤት ባረከ) በማለት የምሳሌዋን እሙንነት በሰፊው ገልጧል፡፡
❖✔♥ ይኽቺም የእግዚአብሔር ታቦት በቤተ ዐሚናዳብ ኻያ ዓመት ተቀምጣለች፤ ከዚያም የሳኦል ዘመን ዐልፎ የእግዚአብሔር ወዳጅ ዳዊት በነገሠ ጊዜ በዐዲስ ሠረገላ አድርገው ከቤተ ዐሚናዳብ አውጥተው በበገና፣ በመሰንቆ፣ በከበሮ፣ በነጋሪት፣ በጸናጽል እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ይዘዋት ሲመጡ፤ የእግዚአብሔርን ታቦት ኦዛ በድፍረት በመያዙ እግዚአብሔር ቀሥፎት ወዲያውኑ በታቦቷ አጠገብ ሕይወቱ አልፏል፤ ያን ጊዜ ነቢዩ ዳዊት የእግዚአብሔር ታቦት ያደረገችውን ተአምራት ተመልክቶ፤ እግዚአብሔር በርሷ እንዳደረ በማመን በፍርሃት ተውጦ "የእግዚአብሔር ታቦት ወደ እኔ እንዴት ይመጣል?" በማለት ለታቦቷ ያለውን ታላቅ ክብር ገልጧል (፪ ሳሙ ፮፥፱-፲)።
❖✔♥ በዘመነ ሐዲስም በተመሳሳይ መልኩ ጌታን በማሕፀኗ የተሸከመች የልዑል እግዚአብሔር ማደሪያ አማናዊት ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ኤልሳቤጥ ቤት በኼደች ጊዜ፤ ኤልሳቤጥ ልክ እንደ ዳዊት መንፈስ ቅዱስ መልቶባት፤ የጌታ ታቦት (ማደሪያው) መኾኗን ተረድታ፤ ድምፅዋን አሰምታ "የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይኾንልኛል?" በማለት ለቅድስት ድንግል ማርያም ያላትን ታላቅ አክብሮት እንደ ዳዊት ገልጣለች (ሉቃ ፩፥፵፫-፵፮) ፡፡
❖✔♥ ከዚያም ዳዊት ይኽነን ታላቅ ቃል ከተናገረ በኋላ የእግዚአብሔር ታቦት በአቢዳራ ቤት ለሦስት ወር ያኽል እንደተቀመጠች (፪ ሳሙ ፮፥፲፩)፤ በተመሳሳይ መልኩ የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያምም በካህኑ በዘካርያስ ቤት ለሦስት ወር ተቀምጣለች (ሉቃ ፩፥፶፮)፡፡ ኦዛ ተቀሥፎ ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር ታቦት ወደ አቢዳራ ቤት ገብታ ቤቱ ለሦስት ወር በበረከት እንደተመላ ኹሉ፤ በተመሳሳይ መልኩ ዘካርያስም የመልአኩን ቃል ባለመቀበሉ ከተረገመ በኋላ (ሉቃ ፩፥፳)፤ እውነተኛዪቱ የአምላክ ታቦት ድንግል ማርያም ቤቱ ለሦስት ወር ተቀምጣለች፡፡
❖✔ ♥ እግዚአብሔር በታቦቷ ምክንያት የአቢዳራን ቤት እንደባረከ ኹሉ የዘካርያስንም ቤት በእመቤታችን ምክንያት የባረከው መኾኑን ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በመጽሐፉ ሲገልጽ ‹‹ድንግል በምስጢር የተመላ ታቦትን ኾና ትኖራለች፣ የካህናት ወገኖችም ደስ ይላቸዋል፣ ያከብሯታልም›› በማለት ታቦትነቷን አጒልቶ አስተ ❖✔♥ በተጨማሪም የእግዚአብሔር ታቦት ከቤተ አቢዳራ ወደ ዳዊት ከተማ ስትገባ፤ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ከደስታው ብዛት የተነሣ የጌታ የክብሩ መገለጫ በኾነችው በታቦቷ ፊት እየዘለ
[በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
❖✔♥ የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ የኾነቺው በወርቅ የተለበጠችው ይቺ የእግዚአብሔር ታቦት፤ በንጽሕና በቅድስና የተጌጠችው የእግዚአብሔር ወልድ እናት የኾነቺው የአማናዊት ታቦት የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡
❖✔♥ በመጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ ፪ ቊጥር ፲፪ትን እንደምናነበው፤ ታቦተ ጽዮንን ያገለግሉ የነበሩት የካህኑ የኤሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ በሠሩት ታላቅ ኀጢአት ምክንያት እግዚአብሔር ዐዝኖባቸው የክብሩ መገለጫ የኾነችው ታቦት በፍልስጤማውያን እጅ እንድትማረክ አደረገ፤ ፍልስጤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቤንኤዘር ወደ አዛጦን በመውሰድ በድፍረት ከዳጎን አጠገብ አኖሯት፤ ነገር ግን ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ወድቆ ተገኘ፤ እነሱም እንደገና ዳጎንን ወደ ስፍራው መልሰው ኼዱ፤ በነጋታው ለማየት ሲመጡ የዳጎን እጅ እግሩ ተቆራርጠው ደረቱ ለብቻው ወድቆ ተገኘ፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይኽነን ታሪክ ይዞ ‹‹የእግዚአብሔር ታቦትንስ በጣዖት ቤት ውስጥ የሚያኖር ማን ነው?›› (፪ቆሮ ፮፥፲፮) በማለት የታቦትን ክብር አስተምሮበታል፡፡
❖✔♥ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅም በሰቈቃወ ድንግል መጽሐፉ ላይ የአምላክ ማደሪያ የኾነችው ታቦት ወደ ፍልስጤም ሀገር ኼዳ ዳጎንን ሰባብራ እንዳጠፋች ኹሉ፤ አማናዊት የጌታ ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታን ይዛ ወደ ግብጽ በተሰደደች ጊዜ የግብጽ ጣዖታት ኹሉ እየተሰባበሩ መውደቃቸውን ሲገልጹ፡-
"ታቦተ አምላከ እስራኤል ጽዮን ዘነገደት ምድረ ኢሎፍሊ
ወቀጥቀጠቶ ለዳጎን ነፍሳተ ብዙኃን ማህጎሊ
አመ ነገደት ቊስቋመ በኀይለ ወልዳ ከሃሊ
ወድቁ አማልክተ ግብጽ መናብርተ ሰይጣን ሐባሊ
ወተኀፍሩ ኲሎሙ ዘቦሙ አስጋሊ"
(ወደ ኢሎፍሊ ምድር ተማርካ የኼደች የእስራኤል አምላክ የቃል ኪዳኑ ታቦት ታቦተ ጽዮን፤ የብዙዎችን ነፍሳት ያጠፋ ዳጎንን ሰባበረችው፤ በዚች ታቦት የተመሰለች ድንግል ማርያምም ኹሉን ማድረግ ከሚችል ከልጇ ጋር ግብጽ ወደሚባል አገር በኼደች ጊዜ፤የሐሰተኛ ሰይጣን ዘፋኖች የኾኑ የግብጽ ጣዖታት ፈረሱ፤ ጠንቋይ አስጠንቋይ ያላቸው ኹሉ ዐፈሩ) በማለት አነጻጽሯል፡፡
❖✔♥ በእግዚአብሔር ታቦት ላይ ስለሠሩት ታላቅ የድፍረት ኀጢአት እግዚአብሔር ቀጣቸው ብዙዎቹ ሞቱ፤ ያልሞቱትም በእባጭ ተመቱ፤ የአይጥ መንጋም ምድራቸውን አጠፋባቸው፤ ያን ጊዜ በእግዚአብሔር ታቦት ላይ ምን እናድርግ? ወደ ስፍራው በምን እንስደደው? ብለው በመማከር፤ የሚያጠቡ ቀንበር ያልተጫነባቸው ኹለት ላሞችን በመውሰድ፤ በዐዲስ ሠረገላ ጠምደው እንቦሶቻቸውን (ጥጆቻቸውን) ከቤት ዘግተው በማስቀረት፤ ታቦተ ጽዮንን እጅ መንሻውን በሠረገላው ላይ ጫኑ፤ ያን ጊዜ እነዚኽ ላሞች ጥጆቻቸውን ሳይናፍቁ ወደቀኝ ወደግራ ሳይሉ እምቧ እያሉ ወደ ቤተ ሳሚስ ወደሚወስደው መንገድ ታቦተ ጽዮንን ይዘው ገሠገሡ፤ ሠረገላውም ወደ ቤትሳሚሳዊው ወደ ኢያሱ እርሻ ሲደርስ ያን ጊዜ ሌዋውያን ታቦት ጽዮንና ዐብሮ የነበረውን የወርቅ ዕቃ አውርደው በታላቅ ደንጊያ ላይ በማኖር፤ ሠረገላውን ፈልጠው ጊደሮቹን ሠውተዋቸዋል፡፡
❖✔♥ ይኽም ለጊዜው ቢደረግም ለኋላው ግን ምሳሌ ነበር፤ ላሞቹ የሰማዕታት፤ ልጆች የልጆቻቸው፤ ሠረገላ የመስቀል፤ ልጆቻቸውን ከወደኋላ እንዳስቀሩ፤ ሰማዕታትም የልጅ የገንዘብ ፍቅር አያስቀራቸውምና፣ ሠረገላውን ፈልጠው እንደሠዋቸው ራሳቸውን በመስቀል ይሠዋሉና በማለት የብሉይ ኪዳን መተርጒማን ያመሰጥሩታል፡፡
❖✔♥ የመልክአ ማርያም ደራሲ የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ የኾነችውን የኻያ መንፈቅ ማለት ዐሥሩ ቃላት የተጻፉባቸው ጽላት የተቀመጡባትን የእግዚአብሔርን ታቦት ጊደሮቹ ከልጆቻቸው ይልቅ በማስበለጥና በመውደድ ይዘዋት ወደፊት እንደነጎዱ፤ ርሱም የልዑል ማደሪያ ለኾነችው ለቅድስት ድንግል ማርያም ያለውን ጥልቅ ፍቅር በድርሰቱ ላይ፡-
"ማርያም ጽዮን ታቦት ቃለ ጽድቅ መንፈቀ ዕሥራ
ዕጐላት እምዕጐሊሆን ከመ ኪያኪ አፍቀራ
አፍቀርኩኪ አፍቅርኒ እምይእዜ ለግሙራ"
(የኻያ እኩሌታ የሚኾን የእውነት ቃል ማደሪያ ጽዮን ማርያም ሆይ፤ ጊደሮች ከጥጆቻቸው ይልቅ አንቺን እንደአፈቀሩ፤ ወድጄሻለኹና ከዛሬ ዠምሮ ፈጽሞ ውደጅኝ) በማለት ገልጦታል፡፡
❖✔♥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በምስጢር በመራቀቅ "አንቲ ውእቱ ጽዮን ታቦተ አምላከ እስራኤል እንተ ነገደት ምድረ ኢሎፍሊ፤ ወበህየ አውደቀቶ ለዳጎን..." (ወደ ኢሎፍሊ ምድር የኼደች የእስራኤል አምላክ ታቦት (ማደሪያ) ጽዮን አንቺ ነሽ፤ በዚያም ዳጎንን የጣለችው ጣዖት አምላኪዎቹንም የቀሠፈቻቸው፤ በአመጣጧም ከአዛጦን ሰዎች ካሳን የተቀበለች፤ ከካሳዋም ጋር እንቦሳ ባላቸው ላሞች አስጭነው የሸኟት፤ ከርሷም ጋር የወርቅ ሳጥኖችን በጐኗም፤ የበድን ሣጥን ሥርዐትን አልሠሩም፤ ነገር ግን በርሷ ዘንድ ካለ ከወርቅ መሣሪያና ከሣጥን ጋራ ላኳት፤ በእንግድነቷ ወቅትም በአሳደራት ጊዜ ወደ ቤቱ በመግባቷ እግዚአብሔር የአቢዳራን ቤት ባረከ) በማለት የምሳሌዋን እሙንነት በሰፊው ገልጧል፡፡
❖✔♥ ይኽቺም የእግዚአብሔር ታቦት በቤተ ዐሚናዳብ ኻያ ዓመት ተቀምጣለች፤ ከዚያም የሳኦል ዘመን ዐልፎ የእግዚአብሔር ወዳጅ ዳዊት በነገሠ ጊዜ በዐዲስ ሠረገላ አድርገው ከቤተ ዐሚናዳብ አውጥተው በበገና፣ በመሰንቆ፣ በከበሮ፣ በነጋሪት፣ በጸናጽል እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ይዘዋት ሲመጡ፤ የእግዚአብሔርን ታቦት ኦዛ በድፍረት በመያዙ እግዚአብሔር ቀሥፎት ወዲያውኑ በታቦቷ አጠገብ ሕይወቱ አልፏል፤ ያን ጊዜ ነቢዩ ዳዊት የእግዚአብሔር ታቦት ያደረገችውን ተአምራት ተመልክቶ፤ እግዚአብሔር በርሷ እንዳደረ በማመን በፍርሃት ተውጦ "የእግዚአብሔር ታቦት ወደ እኔ እንዴት ይመጣል?" በማለት ለታቦቷ ያለውን ታላቅ ክብር ገልጧል (፪ ሳሙ ፮፥፱-፲)።
❖✔♥ በዘመነ ሐዲስም በተመሳሳይ መልኩ ጌታን በማሕፀኗ የተሸከመች የልዑል እግዚአብሔር ማደሪያ አማናዊት ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ኤልሳቤጥ ቤት በኼደች ጊዜ፤ ኤልሳቤጥ ልክ እንደ ዳዊት መንፈስ ቅዱስ መልቶባት፤ የጌታ ታቦት (ማደሪያው) መኾኗን ተረድታ፤ ድምፅዋን አሰምታ "የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይኾንልኛል?" በማለት ለቅድስት ድንግል ማርያም ያላትን ታላቅ አክብሮት እንደ ዳዊት ገልጣለች (ሉቃ ፩፥፵፫-፵፮) ፡፡
❖✔♥ ከዚያም ዳዊት ይኽነን ታላቅ ቃል ከተናገረ በኋላ የእግዚአብሔር ታቦት በአቢዳራ ቤት ለሦስት ወር ያኽል እንደተቀመጠች (፪ ሳሙ ፮፥፲፩)፤ በተመሳሳይ መልኩ የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያምም በካህኑ በዘካርያስ ቤት ለሦስት ወር ተቀምጣለች (ሉቃ ፩፥፶፮)፡፡ ኦዛ ተቀሥፎ ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር ታቦት ወደ አቢዳራ ቤት ገብታ ቤቱ ለሦስት ወር በበረከት እንደተመላ ኹሉ፤ በተመሳሳይ መልኩ ዘካርያስም የመልአኩን ቃል ባለመቀበሉ ከተረገመ በኋላ (ሉቃ ፩፥፳)፤ እውነተኛዪቱ የአምላክ ታቦት ድንግል ማርያም ቤቱ ለሦስት ወር ተቀምጣለች፡፡
❖✔ ♥ እግዚአብሔር በታቦቷ ምክንያት የአቢዳራን ቤት እንደባረከ ኹሉ የዘካርያስንም ቤት በእመቤታችን ምክንያት የባረከው መኾኑን ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በመጽሐፉ ሲገልጽ ‹‹ድንግል በምስጢር የተመላ ታቦትን ኾና ትኖራለች፣ የካህናት ወገኖችም ደስ ይላቸዋል፣ ያከብሯታልም›› በማለት ታቦትነቷን አጒልቶ አስተ ❖✔♥ በተጨማሪም የእግዚአብሔር ታቦት ከቤተ አቢዳራ ወደ ዳዊት ከተማ ስትገባ፤ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ከደስታው ብዛት የተነሣ የጌታ የክብሩ መገለጫ በኾነችው በታቦቷ ፊት እየዘለ
Forwarded from የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጽሑፎች በPDF እና በድምጽ
ለ እንዳመሰገነ ኹሉ (፪ሳሙ ፮፥፲፪-፲፭)፤ አካላዊ ቃልን በማሕፀኗ የተሸከመች የአምላክ ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያምም ወደ ተራራማው ሀገር ወደ ይሁዳ ከተማ ወደ ኤልሳቤጥ ቤት በኼደች ጊዜ፤ ታላቁ ነቢይ መጥምቁ ዮሐንስ በእናቱ ማሕፀን ኾኖ ከደስታው ብዛት የተነሣ እየዘለለ አመስግኗል (ሉቃ ፩፥፵፩-፵፭)፡፡
❖✔♥ ይኽነን ምስጢር ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ሲያብራራ፦ "ንጉሡ ዳዊት በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት ይዘል ነበር፤ ከልቡ ደስታ የተነሣ ለንጉሣውያኑ ደንብ አልታዘዘም፤ እንዲኹ ዮሐንስ ደግሞ ገና ፅንስ ሣለ ከደስታው የተነሣ ከዳዊትም በላቀ ኹኔታ ዘለለ፤ ፅንስ ቢኾንም የእርሱ ባልኾነው በዚኽ ዕድሜ አልተገታም፤ ድንግል እና ቡርክት የኾነችው እናት የእግዚአብሔር ቤት ምስጢራት ከመሉባት ታቦትም በላይ ውብ ነበረች፤ ዳዊትም በአክብሮት በታቦቱ ፊት ዘለለ፤ ይኽም ዮሐንስ በማርያም ፊት ሊዘል እንዳለ አስቀድሞ ያሳይ ነበርና፤ ከዳዊት በቀር ንጉሥ መዝለሉ ተሰምቶ አይታወቅም፤ ሕፃን መዝለሉም እንዲኹ፤ ነቢያት ካህናት የእግዚአብሔርን ልጅ መንገድ አስቀድመው አመለከቱ፤ ርሱም በመጣ ጊዜ ይሹት የነበሩትን ምልክቶች ፈጸማቸው፤ የጌታውን የንጉሡን ምልክት ይጠቁም ዘንድ፤ ዳዊት በደስታ በታቦቱ ፊት ዘለለ፤ዮሐንስ በማርያም ፊት የሚያደርገውን ነገር ምሳሌ በመኾን አሳየ፤ ያቺም ብላቴና እንዲኹ የእግዚአብሔር ታቦት ነበረችና፤ የምስጢራት ጌታ በርሷ ዐደረ፤ ከዚኽም የተነሣ ልክ እንደዚያ ጀግና ንጉሥ ሕፃኑ በርሷ ፊት በደስታ ዘለለ፤ ርሷ በቅዱስ ቃል እንደተመላ ታቦት የተሸከሟት ነበረች፤ የትንቢት ምስጢራት ፍቺ በርሷ ዐደረ) በማለት ይኽ ምሁር ቅድስት ድንግል ማርያምን በምስጢር የተመላች የአምላክ ታቦት መኾኗን በማብራራት ገልጦታል፡፡
❖✔ ዳግመኛም ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በደስታ ሲያመሰግን አይታ የሳኦል ልጅ ሜልኮል ብትንቀው እግዚአብሔር ተቈጥቷት በሕይወቷ ዘመን ኹሉ የልጅ ጸጋ እንዳታገኝ በምክነት ቀጥቷታል (፪ሳሙ ፮፥፳-፳፫)፡፡ ይኸውም ማደሪያው የኾነች ታቦቷን በድፍረት ሊነካት የሞከረውን ኦዛን የቀሠፈ፤ ዳግመኛ የጌትነቱ መገለጫ በኾነች በታቦቷ ፊት ያመሰገነ ዳዊትን የናቀች ሜልኮልን በምክነት የቀጣ አምላክ፤ ዛሬም ፱ ወር ከ፭ ቀን በማሕፀኗ የተሸከመችውን፤ የድንግልና ጡቶቿን የመገበችውን፤ በዠርባዋ ያዘለችውና በደረቷ የታቀፈችውን ቅድስት እናቱን በድፍረት የሚነቅፉ፤ ሔዋንን ያሳተ እባብ መርዝ ክሕደቱን በአፋቸው የረጨባቸው በልቡናቸው ያሳደረባቸው፤ ነቢያት ሐዋርያት ያስተማሩትን የሚያጣምሙ ፀረ ማርያሞች ለዚኽ ድፍረታቸው ንስሓ ካልገቡ የዘላለም ቅጣትና፤ በዚኽ ዓለምም ከድንግል ማርያም አማላጅነት የሚገኘውን ታላቅ በረከት በማጣት እንደ ሜልኮል የበረከትና የጸጋ ምክነት ያጋጥማቸዋል፡፡
❖✔ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ጽዮንን የሚጠሉ ኹሉ ስለሚደርስባቸው ዘላለማዊ ምክነት በመዝ ፻፳፰፥፭-፰ ላይ ‹‹ጽዮንን የሚጠሉ ኹሉ ይፈሩ፤ ወደ ኋላቸውም ይመለሱ፤ በሰገነት ላይ እንደበቀለ ሣር ሳይነቀል እንደሚደርቅ ለሚያጭደው እጁን፤ ነዶዎቹን ለሚሰበስብ ዕቅፉን እንደማይመላ ይኹኑ፤ በመንገድም የሚያልፉ የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይኹን በእግዚአብሔር ስም እንመርቃችኋለን አይሉም›› በማለት እንደተናገረ ጽዮን የተባለች የድንግል ማርያም አማላጅነት የሚቀዋወሙ የዲያብሎስ የግብር ልጆች መናፍቃን እንደ ሜልኮል ከእግዚአብሔር ጸጋ የራቁ ናቸው።
❖✔ ከሊቃውንትም አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም በማሕሌተ ጽጌ፡-
"እስከ መነነቶ ሜልኮል ቅድመ ታቦት ሕግ ከመ ዘፈነ
ንጉሠ እስራኤል ኪያኪ ዘጸገየ ሥነ
ቅድመ ገጸ ሥዕልኪ ድንግል እዘፍን አነ
ዘይሜንን ተአምረኪ ወስብሐተኪ ቊርባነ
በአፈ መላእክት ወሰብእ ለይኩን ምኑነ ››
(አንቺን ያስገኘ የእስራኤል ንጉሥ ዳዊት ሜልኮል እስከናቀችው ድረስ በእግዚአብሔር የሕግ ታቦት ፊት እንዳመሰገነ፤ ድንግል ሆይ እኔም በሥዕልሽ ፊት እዘምራለኍ፤ ድንቅ ታምርሽንና የቀረበ መንፈሳዊ ምስጋናሽን የሚንቅ በመላእክትና በሰው አንደበት የተረገመ ይኹን) በማለት ገልጿል፨
❖✔ በተጨማሪም ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በምስጢር በመራቀቅ ቅድስት ድንግል ማርያምን “በምስጢር የተመላች ታቦት፣ የቃል ኪዳን ታቦት፣ እሳትን የተመላች ታቦት፣ የቅዱስ ቃል ታቦት” በማለት እያብራራ ያስተማረው የነገረ መለኮት ትምህርት እጅግ ጥልቅ ነው ፡፡
[የአምላክ ታቦት እመቤታችን ሆይ እንወድሻለን]
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉@ethiopianorthodoxbooks 👈
👉@ethiopianorthodoxbooks👈
👉@ethiopianorthodoxbooks 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
❖✔♥ ይኽነን ምስጢር ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ሲያብራራ፦ "ንጉሡ ዳዊት በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት ይዘል ነበር፤ ከልቡ ደስታ የተነሣ ለንጉሣውያኑ ደንብ አልታዘዘም፤ እንዲኹ ዮሐንስ ደግሞ ገና ፅንስ ሣለ ከደስታው የተነሣ ከዳዊትም በላቀ ኹኔታ ዘለለ፤ ፅንስ ቢኾንም የእርሱ ባልኾነው በዚኽ ዕድሜ አልተገታም፤ ድንግል እና ቡርክት የኾነችው እናት የእግዚአብሔር ቤት ምስጢራት ከመሉባት ታቦትም በላይ ውብ ነበረች፤ ዳዊትም በአክብሮት በታቦቱ ፊት ዘለለ፤ ይኽም ዮሐንስ በማርያም ፊት ሊዘል እንዳለ አስቀድሞ ያሳይ ነበርና፤ ከዳዊት በቀር ንጉሥ መዝለሉ ተሰምቶ አይታወቅም፤ ሕፃን መዝለሉም እንዲኹ፤ ነቢያት ካህናት የእግዚአብሔርን ልጅ መንገድ አስቀድመው አመለከቱ፤ ርሱም በመጣ ጊዜ ይሹት የነበሩትን ምልክቶች ፈጸማቸው፤ የጌታውን የንጉሡን ምልክት ይጠቁም ዘንድ፤ ዳዊት በደስታ በታቦቱ ፊት ዘለለ፤ዮሐንስ በማርያም ፊት የሚያደርገውን ነገር ምሳሌ በመኾን አሳየ፤ ያቺም ብላቴና እንዲኹ የእግዚአብሔር ታቦት ነበረችና፤ የምስጢራት ጌታ በርሷ ዐደረ፤ ከዚኽም የተነሣ ልክ እንደዚያ ጀግና ንጉሥ ሕፃኑ በርሷ ፊት በደስታ ዘለለ፤ ርሷ በቅዱስ ቃል እንደተመላ ታቦት የተሸከሟት ነበረች፤ የትንቢት ምስጢራት ፍቺ በርሷ ዐደረ) በማለት ይኽ ምሁር ቅድስት ድንግል ማርያምን በምስጢር የተመላች የአምላክ ታቦት መኾኗን በማብራራት ገልጦታል፡፡
❖✔ ዳግመኛም ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በደስታ ሲያመሰግን አይታ የሳኦል ልጅ ሜልኮል ብትንቀው እግዚአብሔር ተቈጥቷት በሕይወቷ ዘመን ኹሉ የልጅ ጸጋ እንዳታገኝ በምክነት ቀጥቷታል (፪ሳሙ ፮፥፳-፳፫)፡፡ ይኸውም ማደሪያው የኾነች ታቦቷን በድፍረት ሊነካት የሞከረውን ኦዛን የቀሠፈ፤ ዳግመኛ የጌትነቱ መገለጫ በኾነች በታቦቷ ፊት ያመሰገነ ዳዊትን የናቀች ሜልኮልን በምክነት የቀጣ አምላክ፤ ዛሬም ፱ ወር ከ፭ ቀን በማሕፀኗ የተሸከመችውን፤ የድንግልና ጡቶቿን የመገበችውን፤ በዠርባዋ ያዘለችውና በደረቷ የታቀፈችውን ቅድስት እናቱን በድፍረት የሚነቅፉ፤ ሔዋንን ያሳተ እባብ መርዝ ክሕደቱን በአፋቸው የረጨባቸው በልቡናቸው ያሳደረባቸው፤ ነቢያት ሐዋርያት ያስተማሩትን የሚያጣምሙ ፀረ ማርያሞች ለዚኽ ድፍረታቸው ንስሓ ካልገቡ የዘላለም ቅጣትና፤ በዚኽ ዓለምም ከድንግል ማርያም አማላጅነት የሚገኘውን ታላቅ በረከት በማጣት እንደ ሜልኮል የበረከትና የጸጋ ምክነት ያጋጥማቸዋል፡፡
❖✔ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ጽዮንን የሚጠሉ ኹሉ ስለሚደርስባቸው ዘላለማዊ ምክነት በመዝ ፻፳፰፥፭-፰ ላይ ‹‹ጽዮንን የሚጠሉ ኹሉ ይፈሩ፤ ወደ ኋላቸውም ይመለሱ፤ በሰገነት ላይ እንደበቀለ ሣር ሳይነቀል እንደሚደርቅ ለሚያጭደው እጁን፤ ነዶዎቹን ለሚሰበስብ ዕቅፉን እንደማይመላ ይኹኑ፤ በመንገድም የሚያልፉ የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይኹን በእግዚአብሔር ስም እንመርቃችኋለን አይሉም›› በማለት እንደተናገረ ጽዮን የተባለች የድንግል ማርያም አማላጅነት የሚቀዋወሙ የዲያብሎስ የግብር ልጆች መናፍቃን እንደ ሜልኮል ከእግዚአብሔር ጸጋ የራቁ ናቸው።
❖✔ ከሊቃውንትም አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም በማሕሌተ ጽጌ፡-
"እስከ መነነቶ ሜልኮል ቅድመ ታቦት ሕግ ከመ ዘፈነ
ንጉሠ እስራኤል ኪያኪ ዘጸገየ ሥነ
ቅድመ ገጸ ሥዕልኪ ድንግል እዘፍን አነ
ዘይሜንን ተአምረኪ ወስብሐተኪ ቊርባነ
በአፈ መላእክት ወሰብእ ለይኩን ምኑነ ››
(አንቺን ያስገኘ የእስራኤል ንጉሥ ዳዊት ሜልኮል እስከናቀችው ድረስ በእግዚአብሔር የሕግ ታቦት ፊት እንዳመሰገነ፤ ድንግል ሆይ እኔም በሥዕልሽ ፊት እዘምራለኍ፤ ድንቅ ታምርሽንና የቀረበ መንፈሳዊ ምስጋናሽን የሚንቅ በመላእክትና በሰው አንደበት የተረገመ ይኹን) በማለት ገልጿል፨
❖✔ በተጨማሪም ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በምስጢር በመራቀቅ ቅድስት ድንግል ማርያምን “በምስጢር የተመላች ታቦት፣ የቃል ኪዳን ታቦት፣ እሳትን የተመላች ታቦት፣ የቅዱስ ቃል ታቦት” በማለት እያብራራ ያስተማረው የነገረ መለኮት ትምህርት እጅግ ጥልቅ ነው ፡፡
[የአምላክ ታቦት እመቤታችን ሆይ እንወድሻለን]
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉@ethiopianorthodoxbooks 👈
👉@ethiopianorthodoxbooks👈
👉@ethiopianorthodoxbooks 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Forwarded from የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጽሑፎች በPDF እና በድምጽ
✦ እውነተኛ ታሪክ✦
የተወሰኑ መነኮሳት ወደ ታላቁ መቃርስ በመሄድ ከገዳማውያኑ መካከል አንዱ ወደ ባዕቱ እየመጣች የምትጎበኘው ሴት እንዳለችና ከእርሷም ጋር በኃጢአት መውደቁን ገልጸው ነገሩት። ቅዱስ መቃርስም ጊዜ በመውሰድ ወደ ባዕታቸው በመመለስ መነኩሴውን በጸሎት እንድያስቡ ነገራቸው።
ገዳማውያኑም ዳግመኛ በመመለስ ሴቲቱ በመነኩሴው ባዕት በዚህ ምሽት ሰዓት እንደምትገኝና ከነርሱም ጋር ወደ መነኩሴው ባዕት በመሄድ ይህንኑ እንዲመለከት ነገሩት።
ታላቁ መቃርስም ከገዳማውያኑ ጋር ወደ መነኩሴው ባዕት በመሄድ በሩን በማንኳኳት በስሙ ጠሩት። መነኩሴውም የሆነውን ነገር ስለተረዳ ሴቲቱን በጠረጴዛ
/ቅርጫት/ ውስጥ ደበቃት።
ቅዱስ መቃርስም ሰላምታ ሰጥቶ በጸጥታ ወደ ባዕቱ በመግባት በቅርጫቱ ላይ በመቀመጥ መነኩሴውን ወዳጄ ሆይ ሌሎቹ ሳይፈርዱብህ አስቀድመህ በራስ ላይ ፍረድ አሉት። ቅዱስ መቃርስ ከመነኩሴው ባዕት ሲወጣም የሰዎችን ኃጢአት በመሰወር ጌታህን አምላክህን ኢየሱስ ክርስቶስን መስለኽዋልና ሰላምታ ይገባሃል የሚል ድምጽ ሰማ።
📌መልዕክቱ
በዚህ ታሪክ ቅዱስ መቃርስ መነኩሴውን ሳያስቆጣው ሳያበሳጨውም ፈጽሞ በጽንአት በመታገስ አሸንፎት በንስሐ ወደ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲመለስ የረዳው መሆኑን እንመለከታለን።
በትዕግሥት ሕይወት ቢገኝ ወደ ፍጹምነት ተፈጽሞ የማያደርስ እንደሆነ ነገር ግን የትዕግስት ሕይወት አስፈላጊነት በጥልቀት እየተረዳን በሄድን ቁጥር ብዙ የሚቀረው መሆኑን እየተረዳን እንደሚሄድ ነው።
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
የተወሰኑ መነኮሳት ወደ ታላቁ መቃርስ በመሄድ ከገዳማውያኑ መካከል አንዱ ወደ ባዕቱ እየመጣች የምትጎበኘው ሴት እንዳለችና ከእርሷም ጋር በኃጢአት መውደቁን ገልጸው ነገሩት። ቅዱስ መቃርስም ጊዜ በመውሰድ ወደ ባዕታቸው በመመለስ መነኩሴውን በጸሎት እንድያስቡ ነገራቸው።
ገዳማውያኑም ዳግመኛ በመመለስ ሴቲቱ በመነኩሴው ባዕት በዚህ ምሽት ሰዓት እንደምትገኝና ከነርሱም ጋር ወደ መነኩሴው ባዕት በመሄድ ይህንኑ እንዲመለከት ነገሩት።
ታላቁ መቃርስም ከገዳማውያኑ ጋር ወደ መነኩሴው ባዕት በመሄድ በሩን በማንኳኳት በስሙ ጠሩት። መነኩሴውም የሆነውን ነገር ስለተረዳ ሴቲቱን በጠረጴዛ
/ቅርጫት/ ውስጥ ደበቃት።
ቅዱስ መቃርስም ሰላምታ ሰጥቶ በጸጥታ ወደ ባዕቱ በመግባት በቅርጫቱ ላይ በመቀመጥ መነኩሴውን ወዳጄ ሆይ ሌሎቹ ሳይፈርዱብህ አስቀድመህ በራስ ላይ ፍረድ አሉት። ቅዱስ መቃርስ ከመነኩሴው ባዕት ሲወጣም የሰዎችን ኃጢአት በመሰወር ጌታህን አምላክህን ኢየሱስ ክርስቶስን መስለኽዋልና ሰላምታ ይገባሃል የሚል ድምጽ ሰማ።
📌መልዕክቱ
በዚህ ታሪክ ቅዱስ መቃርስ መነኩሴውን ሳያስቆጣው ሳያበሳጨውም ፈጽሞ በጽንአት በመታገስ አሸንፎት በንስሐ ወደ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲመለስ የረዳው መሆኑን እንመለከታለን።
በትዕግሥት ሕይወት ቢገኝ ወደ ፍጹምነት ተፈጽሞ የማያደርስ እንደሆነ ነገር ግን የትዕግስት ሕይወት አስፈላጊነት በጥልቀት እየተረዳን በሄድን ቁጥር ብዙ የሚቀረው መሆኑን እየተረዳን እንደሚሄድ ነው።
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አንድ ትንሽ ወንድ ልጅና ሴት ልጅ አብረዉ እየተጫወቱ ነበር። ልጁ ደሳስ የሚሉ ብዮች ነበሩት። ልጅቷ ደግሞ ጣፋጭ ከረሜላዎች ነበሯት።
“የኔን ብዮች ልስጥሽና ያንቺን ከረሜላዎች ስጪኝ” አላት። ልጅቷ በመቀያየሩ ሃሳብ ተስማማች። ልጁ ካሉት ብዮች ውስጥ ትልቅና ቆንጆ የሆነዉን ደብቆ አስቀርቶ ሌሎቹን ሰጣት።
ልጅቷ ግን ቃል እንደገባችዉ ያሏትን ሁሉ ከረሜላዎች ሰጠችዉ። ያን ቀን ማታ ልጅቷ ሰላማዊ እንቅልፏን ተኛች። ልጁ ግን “እኔ ደብቄ ቆንጆዉን ብይ እንዳስቀረሁት እሷም የሚጣፍጠዉን ከረሜላ መርጣ አስቀርታ ይሆን እንዴ?” የሚል ሃሳብ ይዞት እንዲሁ ሲገላበጥ አደረ።
💖💝💖💝💖💝💖💝💖💝💖💝
ህሊናችንን በመጥፎ ሥራ ስንሞላው ሰዎችም እንደኛ ይመስሉናል። በእኛ ልክ እንመዝናቸዋለን፣ መጥፎና ክፉ ስንሆን ሰው ሁሉ መጥፎና ክፉ የሆኑ ይመስለናል። ስለዚህም መጀመርያ እራሳችንን እናጥራ።
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
“የኔን ብዮች ልስጥሽና ያንቺን ከረሜላዎች ስጪኝ” አላት። ልጅቷ በመቀያየሩ ሃሳብ ተስማማች። ልጁ ካሉት ብዮች ውስጥ ትልቅና ቆንጆ የሆነዉን ደብቆ አስቀርቶ ሌሎቹን ሰጣት።
ልጅቷ ግን ቃል እንደገባችዉ ያሏትን ሁሉ ከረሜላዎች ሰጠችዉ። ያን ቀን ማታ ልጅቷ ሰላማዊ እንቅልፏን ተኛች። ልጁ ግን “እኔ ደብቄ ቆንጆዉን ብይ እንዳስቀረሁት እሷም የሚጣፍጠዉን ከረሜላ መርጣ አስቀርታ ይሆን እንዴ?” የሚል ሃሳብ ይዞት እንዲሁ ሲገላበጥ አደረ።
💖💝💖💝💖💝💖💝💖💝💖💝
ህሊናችንን በመጥፎ ሥራ ስንሞላው ሰዎችም እንደኛ ይመስሉናል። በእኛ ልክ እንመዝናቸዋለን፣ መጥፎና ክፉ ስንሆን ሰው ሁሉ መጥፎና ክፉ የሆኑ ይመስለናል። ስለዚህም መጀመርያ እራሳችንን እናጥራ።
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
አንድ እምነት የነበረው እረኛ ነበረ ይባላል፡፡ ምሳ ለመብላት ሲፈልግ ያሰማራቸውን በጎች ለቅዱሳን፣ ለመላእክት አደራ ሰጥቶ ይሔዳል፡፡ "ቅዱስ ገብርኤል ሆይ! እነዚህን በጎቼ ከተኩላ ጠብቅልኝ" ብሎት ይሔዳል፡፡ እንደ እምነቱም በጎቹ ተጠብቀዉለት ያገኛቸዋል፡፡ ሌላ ቀን ደግሞ "ቅዱስ ሚካኤል ሆይ! አንተ ጠብቅልኝ" ይሏል፡፡ እንዲህ በቅዱሳን እያስጠበቀ ምሳውን በልቶ ይመጣል፡፡ አንድ ቀን፦ "እመበቴ ሆይ! ዛሬ አንቺ ጠብቂልኝ" ብሎ ወደ ቤቱ ይሔዳል፡፡ አባቱ አገኙትና፦ "ዛሬ ለማን አስጠብቀህ መጣህ?" አሉት፡፡ "ለእመቤታችን አስጠብቄ መጣሁ" አላቸው፡፡ እርሳቸውም፦ "አዪ! እርሷ'ማ ታስበላብሃለች" አሉት፡፡ "ለምን? ቅዱሳን፣ ጻድቃን፣ መላእክት የጠበቁትን እርሷ አትጠብቅምን? ይላቸዋል፡፡ "አይ ልጄ! የተጠማን ውሻ በወርቅ ጫማዋ ያጠጣች፡ የተራበ አውሬ መጥቶ ቢበላ ትከለክለዋለችን? ታስበላብሃለች" ሲሉት "እውነትም" ብሎ ወደ መንጎቹ ሮጠ ይባላል፡፡
ርህርህተ ሕሊና ሆይ! ዘወትር በምልጃሽ በቃል ኪዳንሽ ጠብቂን፡፡ አሜን!!!
#Samuel_Ayalneh.
🙏🙏🙏🙏መልካም ሰንበት 🙏🙏🙏🙏
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
ርህርህተ ሕሊና ሆይ! ዘወትር በምልጃሽ በቃል ኪዳንሽ ጠብቂን፡፡ አሜን!!!
#Samuel_Ayalneh.
🙏🙏🙏🙏መልካም ሰንበት 🙏🙏🙏🙏
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
ዛሬ በዳዊት ከተማ ኅፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና:አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም÷ኃያል:ድንቅ: መካር:የሰላም አለቃ የዘላአለም አባት ተብሎ ይጠራል፡፡
ማቴ ፪÷፩
መልካም በዓል
ማቴ ፪÷፩
መልካም በዓል
ጥር 7 - ቅድስት ሥላሴ
በዚህች ቀን ቅድስት ሥላሴ በኃጢያት የተገነባውን የሰናኦር ግንብ ያፈረሱበት አንድነታቸውንና ሶስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት ቀን ነው፤ (ዘፍጥረት 11÷1) እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። እግዚአብሔርም አለ። "ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።" እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተዉ። ስለዚህም ስምዋ ባቢሎን ተባለ ይላል።
“እግዚአብሔርም አለ” አንድነታቸውን ሲያጠይቅ ኑ እንውረድ ሶስትነታቸውን፤ ሥላሴ በስም አአካል በግብር ሶስት ናቸው፤ የስም ሶስትነታቸው እንደምን ነው ቢሉ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው፤ የግብር ሶስትነታቸውስ እንደምን ነው ቢሉ አብ ወላዲ ወልድ ተወላዲ መንፈስ ቅዱስ ሰራጺ፤ የአካል ሶስትነታቸውስ እንዴት ነው ቢሉ ለአብ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው ለወልድም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው ለመንፈስ ቅዱስም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው፤ ለመሆኑ የሥላሴ ገጽ አካል ፊት እንደ ሰው ነውን ቢሉ አዎን እንደ ሰው ነው ነገር ግን የሰው ውሱን ጠባብ ፈራሽና በስባሽ ነው የሥላሴ ግን እንዲህ አይደለም በሰማይና በምድር በአየርና በእመቅ የመላ ረቂቅ ህያው ባህርይ ነው ኢሳ 66÷1። የሥላሴ አንድነታቸው በመለኮት በፈቃድ በስልጣን በምክር ወዘተ በመሳሰሉት ነው።
ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን
በዚህች ቀን ቅድስት ሥላሴ በኃጢያት የተገነባውን የሰናኦር ግንብ ያፈረሱበት አንድነታቸውንና ሶስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት ቀን ነው፤ (ዘፍጥረት 11÷1) እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። እግዚአብሔርም አለ። "ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።" እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተዉ። ስለዚህም ስምዋ ባቢሎን ተባለ ይላል።
“እግዚአብሔርም አለ” አንድነታቸውን ሲያጠይቅ ኑ እንውረድ ሶስትነታቸውን፤ ሥላሴ በስም አአካል በግብር ሶስት ናቸው፤ የስም ሶስትነታቸው እንደምን ነው ቢሉ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው፤ የግብር ሶስትነታቸውስ እንደምን ነው ቢሉ አብ ወላዲ ወልድ ተወላዲ መንፈስ ቅዱስ ሰራጺ፤ የአካል ሶስትነታቸውስ እንዴት ነው ቢሉ ለአብ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው ለወልድም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው ለመንፈስ ቅዱስም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው፤ ለመሆኑ የሥላሴ ገጽ አካል ፊት እንደ ሰው ነውን ቢሉ አዎን እንደ ሰው ነው ነገር ግን የሰው ውሱን ጠባብ ፈራሽና በስባሽ ነው የሥላሴ ግን እንዲህ አይደለም በሰማይና በምድር በአየርና በእመቅ የመላ ረቂቅ ህያው ባህርይ ነው ኢሳ 66÷1። የሥላሴ አንድነታቸው በመለኮት በፈቃድ በስልጣን በምክር ወዘተ በመሳሰሉት ነው።
ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን
ከተራ ምንድን ነው?
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡
በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።
በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡
መልካም የከተራ በዓል
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡
በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።
በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡
መልካም የከተራ በዓል
ጌታችን ለምን በውሃ ተጠመቀ?
እግዚአብሔር አምላክ በዘመነ ኦሪት ሰብዐ ትካትን በንፍር ውሃ ፈርኦንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ካጠፋ በኋላ ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረ ለማጠየቅ በውሃ ተጠመቀ ( ዘፍ 7÷17፤ ዘጸ 14÷1-29)
አንድም ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከገሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ውሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ መልክዓ ሥላሴን የአምላክን ቸርነት ርህራሔ ታያላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም በማር በወተት ቢጠመቅ ኖሮ እነዚህ ለባለጸጎች እንጂ ለድሆች አይገኝም ውሃ ግን በሁሉ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ጥምቀት የታዘዘ ለሁሉ ነው ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ቢታጠብበት ያቆሽሻል እንጂ አያነጣም ውሃ ግን እድፍን ያስለቅቃል እናንተም በማየ ገቦ ብትጠመቁ ከኃጢአት ትጠራላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ተክል ላይ ቢያፈሱት ያደርቃሉ እንጂ አያለመልሙም ውሃ ግን ያለመልማል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋ ወነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ (ዮሐ 19÷35)
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር
እግዚአብሔር አምላክ በዘመነ ኦሪት ሰብዐ ትካትን በንፍር ውሃ ፈርኦንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ካጠፋ በኋላ ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረ ለማጠየቅ በውሃ ተጠመቀ ( ዘፍ 7÷17፤ ዘጸ 14÷1-29)
አንድም ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከገሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ውሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ መልክዓ ሥላሴን የአምላክን ቸርነት ርህራሔ ታያላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም በማር በወተት ቢጠመቅ ኖሮ እነዚህ ለባለጸጎች እንጂ ለድሆች አይገኝም ውሃ ግን በሁሉ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ጥምቀት የታዘዘ ለሁሉ ነው ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ቢታጠብበት ያቆሽሻል እንጂ አያነጣም ውሃ ግን እድፍን ያስለቅቃል እናንተም በማየ ገቦ ብትጠመቁ ከኃጢአት ትጠራላችሁ ሲል ነው፡፡
አንድም ማርና ወተት ተክል ላይ ቢያፈሱት ያደርቃሉ እንጂ አያለመልሙም ውሃ ግን ያለመልማል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋ ወነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ (ዮሐ 19÷35)
Send this to your telegram friends
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
@ethiopianorthodoxbooks
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
To join our channel click the one in blue
ተዋሕዶ ለዘላለም ትኑር