የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በምስራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮች ኤክስፖ East Africa Pastoralist Expo ላይ በመገኘት የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለኤክሰፖው ተሳታፊዎች ገለጻ አድርገዋል።
በተለይም አካዳሚው በልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሙ ውስጥ የአርብቶ አደር ፕሮግራም ማካተቱን እና የዘርፉን አመራርና ባለሙያ አቅም ለመገንባት እየተሰራ እንደሆነ አቶ ዛዲግ አብራርተዋል።
ከአርብቶ አደር ጋር በተያያዘ ያለውን የጥናት እና ምርምር ስራዎች ለማስፋት እና የዘርፉ አመራር በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ውስጥ ሆነው ጥናትና ምርምር ለማድረግ እንዲችሉም በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ Center for Pastoralist Economic Transformation (CPET) እንዲገነባ ሀሳብ አቶ ዛዲግ ሀሳብ አቅርበዋል።
በዘርፉ የተሻለ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎችም ሀገር አቀፍ ሽልማት እና ዕውቅና የሚሰጥበት የአፍሌክስ አዋርድ ፕሮግራም እንደሚኖርም አቶ ዛዲግ ገልጸዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ባቀረቧቸው ሶስቱም ፕሮጀክቶች ላይ የጋራ መግባባት የተፈጠረ ሲሆን በቀጣይ ሳምንታት ለሀሳብ ማመንጫ ማዕከሉ ስራ እንደሚጀመር ታውቋል።
በተለይም አካዳሚው በልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሙ ውስጥ የአርብቶ አደር ፕሮግራም ማካተቱን እና የዘርፉን አመራርና ባለሙያ አቅም ለመገንባት እየተሰራ እንደሆነ አቶ ዛዲግ አብራርተዋል።
ከአርብቶ አደር ጋር በተያያዘ ያለውን የጥናት እና ምርምር ስራዎች ለማስፋት እና የዘርፉ አመራር በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ውስጥ ሆነው ጥናትና ምርምር ለማድረግ እንዲችሉም በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ Center for Pastoralist Economic Transformation (CPET) እንዲገነባ ሀሳብ አቶ ዛዲግ ሀሳብ አቅርበዋል።
በዘርፉ የተሻለ የስራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎችም ሀገር አቀፍ ሽልማት እና ዕውቅና የሚሰጥበት የአፍሌክስ አዋርድ ፕሮግራም እንደሚኖርም አቶ ዛዲግ ገልጸዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ባቀረቧቸው ሶስቱም ፕሮጀክቶች ላይ የጋራ መግባባት የተፈጠረ ሲሆን በቀጣይ ሳምንታት ለሀሳብ ማመንጫ ማዕከሉ ስራ እንደሚጀመር ታውቋል።
የአርብቶ አደር ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል (Center for Pastoralist Economic Transformation) (CPET) በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ ሊቋቋም ነው::
የአርብቶአደሩን ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስና በአጠቃላይ በዘርፉ ልማት ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል የአርብቶአደር ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል በአፍሪካ አመራር ልኅቀት አካዳሚ ሊቋቋም ነው፡፡
የአርብቶአደሩን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ራሱን የቻለ ፖሊሲና ተቋም በማስፈለጉ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የተቋቋመና የኢትዮጵያ አርብቶአደር ፖሊሲና ማስፈፀሚያ ስትራቴጂ ጸድቆ ተግባር ላይ መዋሉ በተገለፀበት በዛሬው የምስራቅ አፍሪካ አርብቶአደሮች ኤክስፖ የፓናል ውይይት፣ መሠረታዊ የሚባሉ ችግሮች የተፈቱ ቢሆንም የአርብቶአደር አመራር ልማት፣ የድርቅ ተደጋጋሚ ክስተት፣ አካባቢያዊ ግጭቶች፣ ባህላዊና ዘመናዊውን የአስተዳደር ዘይቤዎች ቀላቅሎ መጠቀም፣ ክፍተቶች መኖራቸው ተመላክቷል፡፡
አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሪካ አመራር ልኅቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ እንደተናገሩት የአርብቶአደሩንና ሌሎች ተዋናዮችን በአጠቃላይ ወደ አንድ ማዕቀፍ የሚያሰባስብ፣ ለጥናትና ምርምር፣ ለዘርፉ ልማት አመራር በማፍራትም ጭምር ድርሻውን ሊወጣ የሚችል ማዕከል ይሆናል፡፡
በሌላ በኩል ፓናል ውይይቱ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ምክትል ፕሬዘዳንት ክቡር አቶ ኤለማ አቡበከር የአፍሪካ አመራር ልኅቀት አካዳሚ ሊያቋቁም ስላሰበው የአርብቶአደር ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል አመስግነው በዘርፉ ያለውን የአመራር ክፍተት ለመሙላት የሚደረግ ጥረት አካል ስለሆነ ዘላቂነት ያለው ልማት ለማረጋገጥ የጎላ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የአርብቶአደሩን ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመመለስና በአጠቃላይ በዘርፉ ልማት ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል የአርብቶአደር ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል በአፍሪካ አመራር ልኅቀት አካዳሚ ሊቋቋም ነው፡፡
የአርብቶአደሩን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል ራሱን የቻለ ፖሊሲና ተቋም በማስፈለጉ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የተቋቋመና የኢትዮጵያ አርብቶአደር ፖሊሲና ማስፈፀሚያ ስትራቴጂ ጸድቆ ተግባር ላይ መዋሉ በተገለፀበት በዛሬው የምስራቅ አፍሪካ አርብቶአደሮች ኤክስፖ የፓናል ውይይት፣ መሠረታዊ የሚባሉ ችግሮች የተፈቱ ቢሆንም የአርብቶአደር አመራር ልማት፣ የድርቅ ተደጋጋሚ ክስተት፣ አካባቢያዊ ግጭቶች፣ ባህላዊና ዘመናዊውን የአስተዳደር ዘይቤዎች ቀላቅሎ መጠቀም፣ ክፍተቶች መኖራቸው ተመላክቷል፡፡
አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሪካ አመራር ልኅቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ እንደተናገሩት የአርብቶአደሩንና ሌሎች ተዋናዮችን በአጠቃላይ ወደ አንድ ማዕቀፍ የሚያሰባስብ፣ ለጥናትና ምርምር፣ ለዘርፉ ልማት አመራር በማፍራትም ጭምር ድርሻውን ሊወጣ የሚችል ማዕከል ይሆናል፡፡
በሌላ በኩል ፓናል ውይይቱ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ምክትል ፕሬዘዳንት ክቡር አቶ ኤለማ አቡበከር የአፍሪካ አመራር ልኅቀት አካዳሚ ሊያቋቁም ስላሰበው የአርብቶአደር ኢኮኖሚ ሽግግር ማዕከል አመስግነው በዘርፉ ያለውን የአመራር ክፍተት ለመሙላት የሚደረግ ጥረት አካል ስለሆነ ዘላቂነት ያለው ልማት ለማረጋገጥ የጎላ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የ19ኛው የአርብቶአደር ቀንን በማስመልከትና ቀጠናዊ ትስስርን ለማሳደግ ታስቦ ‘‘አርብቶ አደርነት: የምስራቅ አፍሪካ ኅብረ-ቀለም’’ በሚል መሪ ቃል በሚሊኒየም አዳራሽ የምስራቅ አፍሪካ የአርብቶአደሮች ኤክስፖ በይፋ የተከፈተው ባለፈው አርብ ጥር 17/2016 ዓ.ም ነው፡፡
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከቢል ኤንድ ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን Bill & Melinda Gates Foundation ካንትሪ ዳይሬክተር ሀዲስ ታደሰ ጋር ተወያዩ።
አቶ ዛዲግ አብርሃ በአፍሌክስ ሪፎርም(Reform)፤ ማስፋት (Scaling Up) እና ሽግግር (Transformation) ዙሪያ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ ገለጻ አድርገዋል።
ርዕሰ አካዳሚው እንደገለጹት አፍሌክስ የጀመረውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳካት መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እና ፋውንዴሽኖች ጋር በመሆን ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነም አቶ ዛዲግ ገልጸዋል።
አፍሌክስን የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተሰራ እንደሆነ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ይህንኑ ዓላማ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የፋውንዴሽኑ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲደረጉ አቶ ዛዲግ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ካንትሪ ዳይሬክተሩ ሀዲስ ታደሰ ስለ አፍሌክስ በተደረገላቸው ገለጻ አመስግነው ከአፍሌክስ ጋር አብረው ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ሰጥተዋል።
ቢል ኤንድ ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን Bill & Melinda Gates Foundation የሚሰራባቸውን ዘርፎች ያብራሩት ካንትሪ ዳይሬክተሩ ከአፍሌክስ ጋር ሊሰሩ የሚችሉባቸውን ዘርፎች በመለየት አብረው ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑ ጠቅሰው በተለይም በሴቶች ጤና፤ በግብርና በምግብ ዋስትና እና ዲጂታል ፋይናንስ ዙሪያ የአመራሩን አቅም መገንባት
አቶ ዛዲግ አብርሃ በአፍሌክስ ሪፎርም(Reform)፤ ማስፋት (Scaling Up) እና ሽግግር (Transformation) ዙሪያ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ ገለጻ አድርገዋል።
ርዕሰ አካዳሚው እንደገለጹት አፍሌክስ የጀመረውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳካት መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እና ፋውንዴሽኖች ጋር በመሆን ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነም አቶ ዛዲግ ገልጸዋል።
አፍሌክስን የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተሰራ እንደሆነ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ይህንኑ ዓላማ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የፋውንዴሽኑ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲደረጉ አቶ ዛዲግ ለካንትሪ ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ካንትሪ ዳይሬክተሩ ሀዲስ ታደሰ ስለ አፍሌክስ በተደረገላቸው ገለጻ አመስግነው ከአፍሌክስ ጋር አብረው ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብ ሰጥተዋል።
ቢል ኤንድ ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን Bill & Melinda Gates Foundation የሚሰራባቸውን ዘርፎች ያብራሩት ካንትሪ ዳይሬክተሩ ከአፍሌክስ ጋር ሊሰሩ የሚችሉባቸውን ዘርፎች በመለየት አብረው ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑ ጠቅሰው በተለይም በሴቶች ጤና፤ በግብርና በምግብ ዋስትና እና ዲጂታል ፋይናንስ ዙሪያ የአመራሩን አቅም መገንባት
በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ በረጅም እና በመካከለኛ ጊዜ ውስጥ የሚሰሩ ስራዎችን በመለየት ወደ ስራ መግባት እንደሚቻል ተናግረዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ ሚኒስትር ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ስለ አካዳሚው የሶስት ዓመት ስትራቴጂ እና ፕሮግራም ገለጻ አድርገዋል።
አቶ ዛዲግ እንደጠቀሱት አፍሌክስ የአህጉሪቱን እና የሀገራችንን አመራሮች ለማብቃት ስልጠና ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በማመኑ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ ተናግረዋል። በእነዚህ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎች ውስጥም ከፍተኛ አመራሮች አቅማቸውን እንደሚገነቡ እና ሀሳብ እያፈለቁ የምርምር ስራዎችን እንደሚያበረክቱ ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አለሙ ስሜ (ዶ/ር) አፍሌክስ ይዞ የተነሳው የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የሚኖረውን ጥቅም አስታውሰው፤ በተለይም ከመንግስት ልማት አቅጣጫ እና የብልጽግና መስመር ጋር በተናበበ መልኩ የተቀረጹት የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ለሀገር እድገት ግብዓት እንደሚሆን ተናግረዋል። ተቋማቸውም ለዚህ ፕሮግራም መሳካት ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እንደሚያደርግ ክቡር ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ለሀሳብ ማመንጫ ማዕከል የሚሆን የመሰረተ ልማት ግንባታም በአፍሌክስ ውስጥ ለመስራት ውይይት እንደሚያስፈልግ የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ላይ እንደሚደርሱም አሳውቀዋል።
አቶ ዛዲግ እንደጠቀሱት አፍሌክስ የአህጉሪቱን እና የሀገራችንን አመራሮች ለማብቃት ስልጠና ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በማመኑ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ ተናግረዋል። በእነዚህ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎች ውስጥም ከፍተኛ አመራሮች አቅማቸውን እንደሚገነቡ እና ሀሳብ እያፈለቁ የምርምር ስራዎችን እንደሚያበረክቱ ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አለሙ ስሜ (ዶ/ር) አፍሌክስ ይዞ የተነሳው የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የሚኖረውን ጥቅም አስታውሰው፤ በተለይም ከመንግስት ልማት አቅጣጫ እና የብልጽግና መስመር ጋር በተናበበ መልኩ የተቀረጹት የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ለሀገር እድገት ግብዓት እንደሚሆን ተናግረዋል። ተቋማቸውም ለዚህ ፕሮግራም መሳካት ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እንደሚያደርግ ክቡር ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ለሀሳብ ማመንጫ ማዕከል የሚሆን የመሰረተ ልማት ግንባታም በአፍሌክስ ውስጥ ለመስራት ውይይት እንደሚያስፈልግ የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ላይ እንደሚደርሱም አሳውቀዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለሴቶች እና ማሕበራዊ ጉዳይ ክብርት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ጋር የአፍሌክስን ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ስትራቴጂ ገለጹ።
የአካዳሚው የሪፎርም የማስፋት እና የሽግግር ስራዎች ላይ ከሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ጋር አብረው ለመስራት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
ክብርት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሶስት ዓመታት ውስጥ ሊፈጽም ያቀዳቸው የአመራር ልማት ፕሮግራሞች የሀገራችንን አመራር ወደ ታላቅ ከፍታ የሚያሸጋግሩ እና ትውልድን የሚቀርጹ ናቸው ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) የአፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍም ከሀገር አልፎ በአፍሪካ ላይ ተጽእኖ በመፍጠር ከአፍሪካውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ጋር የሚያገናኝ ድልድይ በመሆኑ የሚኒስትር መስሪያ ቤታቸው ድጋፍ ባስፈለገበት ሁሉ አብረው ለመስራት ቃል ገብተዋል።
በአፍሌክስ ውስጥም የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ለመገንባትም ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹት ክብርት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ሰፊ ውይይት እና ዝርዝር ጥናቶችን በማድረግ ወደ ስራ ለመግባት የቴክኒክ ኮሚቴ አቋቁመዋል።
የአካዳሚው የሪፎርም የማስፋት እና የሽግግር ስራዎች ላይ ከሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ጋር አብረው ለመስራት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
ክብርት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሶስት ዓመታት ውስጥ ሊፈጽም ያቀዳቸው የአመራር ልማት ፕሮግራሞች የሀገራችንን አመራር ወደ ታላቅ ከፍታ የሚያሸጋግሩ እና ትውልድን የሚቀርጹ ናቸው ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) የአፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍም ከሀገር አልፎ በአፍሪካ ላይ ተጽእኖ በመፍጠር ከአፍሪካውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ጋር የሚያገናኝ ድልድይ በመሆኑ የሚኒስትር መስሪያ ቤታቸው ድጋፍ ባስፈለገበት ሁሉ አብረው ለመስራት ቃል ገብተዋል።
በአፍሌክስ ውስጥም የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ለመገንባትም ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹት ክብርት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ሰፊ ውይይት እና ዝርዝር ጥናቶችን በማድረግ ወደ ስራ ለመግባት የቴክኒክ ኮሚቴ አቋቁመዋል።
የሳውዘርን ኮፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን ሴክሬተሪ ጄኔራል መንሱር ቢን ሙሳላም Mansssour Bin Mussallam Secretary General of the Organization of Southeren Cooperation በበኩላቸው በቀረቡት ፕሮጀክቶች እና በአመራር ልማት ፕሮግራሞቹ ላይ ደስተኛ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራምን በቴክኒክ ለመደገፍ እና በመሰረተ ልማት ላይ አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝርዝር ውይይት እንደሚያስፈልግ ተናግረው የቴክኒክ ኮሚቴው በሚያቀርበው ምክረ ሀሳብ መሰረት አጋርነታቸውን እንደሚገልጹ ተናግረዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ ከሳውዘርን ኮፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን ሴክሬተሪ ጄኔራል መንሱር ቢን ሙሳላም Mansssour Bin Mussallam Secretary General of the Organization of Southeren Cooperation (OSC)ጋር ተወያዩ።
ለሴክሬተሪ ጄኔራሉ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ ሰፊ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመው፤ ለዚህም የሚሆን አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው አፍሪካዊ መልክና ይዘት እንዲኖረውም እየተሰራ እንደሆነ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ፤ የታቀደውን ለመፈጸም የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።
አፍሌክስን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት መቀረጹን ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ሸገር ሲቲን ከዳቮስ ከተማ ጋር በእህትማማች ከተማ ለማገናኘት ስራ መጀመሩንም ተናግረዋል።
ሳውዘርን ኮፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን በአፍሪካ ፕሮግራሞች ላይ በዲዛይን እና ፕሮግራም ቀረጻ ፤ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርጉ እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ ከአፍሌክስ ጋር በትብብር እንዲሰራ አቶ ዛዲግ ግብዣ አቅርበዋል።
ለሴክሬተሪ ጄኔራሉ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ ሰፊ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመው፤ ለዚህም የሚሆን አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው አፍሪካዊ መልክና ይዘት እንዲኖረውም እየተሰራ እንደሆነ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ፤ የታቀደውን ለመፈጸም የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።
አፍሌክስን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት መቀረጹን ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ሸገር ሲቲን ከዳቮስ ከተማ ጋር በእህትማማች ከተማ ለማገናኘት ስራ መጀመሩንም ተናግረዋል።
ሳውዘርን ኮፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን በአፍሪካ ፕሮግራሞች ላይ በዲዛይን እና ፕሮግራም ቀረጻ ፤ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርጉ እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ ከአፍሌክስ ጋር በትብብር እንዲሰራ አቶ ዛዲግ ግብዣ አቅርበዋል።