የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን-ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ያለው በበኩላቸው ስለ አፍሌክስ በተደረገላቸው ማብራሪያ አመስግነው በሌሎች ሀገራት የሚገኝ የአመራር ማሰልጠኛ ማዕከል እና መሰረተ ልማት አይነት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለመስራት መታቀዱ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው አፍሌክስ የጀመረው ሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ኢትዮጵያን እና አፍሪካን የሚያጎላ በመሆኑ በወጣቶች ስራ ፈጠራ እና ልማት፤ በሴቶች አቅም ግንባታ፤ በሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዙሪያ ከፋውንዴሽኑን ተልዕኮ እና ዓላማ ጋር በተናበበ መልኩ ከአፍሌክስ ጋር ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የአፍሪካ አመራር ለህቀት አካዳሚ እና ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን-ኢትዮጵያ በጋራ ሊሰሩ በሚችሉባቸው መስኮች ዙሪያ ተወያዩ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለማስተር ካርድ ፋውንዴሽን-ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ያለው የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እና የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ሰፊ ገለጻ ያቀረቡ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎችም አብራርተዋል።
ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን-ኢትዮጵያ በወጣቶች ልማት እና ስራ ፈጠራ ዙሪያ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ዛዲግ በአፍሌክስ ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ላይ ተተኪ እና ሴት አመራሮችን አቅም ለመገንባት በተያዘው ዕቅድ ውስጥ ፋውንዴሽኑ በፕሮግራም ቀረጻ እና በቴክኒክ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እንደ ስሙ አፍሪካዊ ቅርጽ እና ይዘት እንዲኖረው በተሰራው ሪፎርም ውስጥም አፍሪካውያን ወጣቶች የሚገናኙበት እና ስለ አህጉሪቱ ልማት በሰፊው ተወያይተው የስራ ፈጠራ ችሎታቸውን የሚያዳብሩበት ተቋም እንዲሆን ፋውንዴሽኑ የመሰረተ ልማት፤ የማስተርስ ትምህርት እና የአመራር ልማት ፕሮግራም ዲዛይን ላይ ከአፍሌክስ ጋር ሊሰራ የሚችልበት መንገድ እንዳለ የጠቆሙት አቶ ዛዲግ የፋውንዴሽኑ ጉባኤዎችም በአፍሌክስ ማዕከል ውስጥ በሚደረጉበት ሁኔታ ላይ ሀሳብ አቅርበዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለማስተር ካርድ ፋውንዴሽን-ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ያለው የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እና የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ሰፊ ገለጻ ያቀረቡ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎችም አብራርተዋል።
ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን-ኢትዮጵያ በወጣቶች ልማት እና ስራ ፈጠራ ዙሪያ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ዛዲግ በአፍሌክስ ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ላይ ተተኪ እና ሴት አመራሮችን አቅም ለመገንባት በተያዘው ዕቅድ ውስጥ ፋውንዴሽኑ በፕሮግራም ቀረጻ እና በቴክኒክ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እንደ ስሙ አፍሪካዊ ቅርጽ እና ይዘት እንዲኖረው በተሰራው ሪፎርም ውስጥም አፍሪካውያን ወጣቶች የሚገናኙበት እና ስለ አህጉሪቱ ልማት በሰፊው ተወያይተው የስራ ፈጠራ ችሎታቸውን የሚያዳብሩበት ተቋም እንዲሆን ፋውንዴሽኑ የመሰረተ ልማት፤ የማስተርስ ትምህርት እና የአመራር ልማት ፕሮግራም ዲዛይን ላይ ከአፍሌክስ ጋር ሊሰራ የሚችልበት መንገድ እንዳለ የጠቆሙት አቶ ዛዲግ የፋውንዴሽኑ ጉባኤዎችም በአፍሌክስ ማዕከል ውስጥ በሚደረጉበት ሁኔታ ላይ ሀሳብ አቅርበዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራር እና ሰራተኞች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ኤግዚቢሽን ጎበኙ።
በኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) የተመራው ቡድን በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ኤግዚቢሽን ጎብኝቷል።
ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በጉብኝቱ ላይ እንደተናገሩት ኤግዚቢሽኑ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም ሰላም ያበረከተቸውን አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ እንደሆነ ጠቁመው፤ የአሁኑ ትውልድም ቀደምት አባቶቹ በዓለም ዲፕሎማሲ መስክ ያስመዘገቡትን ድል እያስቀጠለ እንደሚገኝ ተመልክተናል ብለዋል።
ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) አያይዘውም የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራርና ሰራተኞች ለሀገር ልማት እና ብልጽግና የሚያበረክቱትን ድርሻ በጉልህ እንዲወጡ ጉብኝቱ የራሱን በጎ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉ አመራሮች እና ሰራተኞች በበኩላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገራችንን የዲፕሎማሲ ታሪክ ሌሎች እንዲያውቁ ማድረጉ ትላንት የት እንደነበር እና ወደፊት የምንደርስበትን መንገድ ያመላከተ በመሆኑ ለአካዳሚው ተልዕኮ ስኬታማነት የስራ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
በኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) የተመራው ቡድን በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ኤግዚቢሽን ጎብኝቷል።
ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በጉብኝቱ ላይ እንደተናገሩት ኤግዚቢሽኑ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም ሰላም ያበረከተቸውን አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ እንደሆነ ጠቁመው፤ የአሁኑ ትውልድም ቀደምት አባቶቹ በዓለም ዲፕሎማሲ መስክ ያስመዘገቡትን ድል እያስቀጠለ እንደሚገኝ ተመልክተናል ብለዋል።
ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) አያይዘውም የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራርና ሰራተኞች ለሀገር ልማት እና ብልጽግና የሚያበረክቱትን ድርሻ በጉልህ እንዲወጡ ጉብኝቱ የራሱን በጎ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉ አመራሮች እና ሰራተኞች በበኩላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገራችንን የዲፕሎማሲ ታሪክ ሌሎች እንዲያውቁ ማድረጉ ትላንት የት እንደነበር እና ወደፊት የምንደርስበትን መንገድ ያመላከተ በመሆኑ ለአካዳሚው ተልዕኮ ስኬታማነት የስራ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከ Global Center for Gender Equality ከመጡ ከፍተኛ የስራ ሀላፊ ጋር ተወያዩ:: Alex Munive በማዕከሉ Feminist Leadership ዳይሬክተር ሲሆኑ ስለ አፍሌክስ ሪፎርም: ሽግግር እና ማስፋት ፕሮግራም ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በጠቅላላ የአመራር ልማት ፕሮግራሙ ከቀረፃቸው አራት ፕሮግራሞች ውስጥ የሴቶች የአመራር ልማት ፕሮግራም አንዱ በመሆኑ ከማዕከሉ ጋር በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ አቶ ዛዲግ ተናግረዋል::
Alex Munive በበኩላቸው ማዕከላቸው የአፍሌክስን የሴቶች የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመደገፍ እና አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከሚገኘው ተቋማቸው ጋር ውይይት በማድረግ ሁለቱ ተቋማት በትብብር የሚሰሩባቸውን መስኮች በመለየት ወደ ስራ እንደሚገቡ ገልጸዋል::
Alex Munive በበኩላቸው ማዕከላቸው የአፍሌክስን የሴቶች የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመደገፍ እና አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው በፊንላንድ ሄልሲንኪ ከሚገኘው ተቋማቸው ጋር ውይይት በማድረግ ሁለቱ ተቋማት በትብብር የሚሰሩባቸውን መስኮች በመለየት ወደ ስራ እንደሚገቡ ገልጸዋል::