ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃት የሚያስከትለውን ማህበራዊ፤ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንደሚያስፈልጉና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ተግባራዊ ለውጥ ላይ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለፀ፡፡
ይኽ የተገለፀው ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀን በአካዳሚ ደረጃ ሲከበር ነው፡፡ አለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን "ሴትን አከብራለሁ፤ ጥቃቷንም እከላከላለሁ!" እንዲሁም አለም አቀፍ የኤድስ ቀን "ፍትሃዊና ተደራሽ የኤች አይ ቪ/ኤድስ አገልግሎት! በሚል መሪ ቃል በእግር ጉዞ እና በውይይት በተከበረበት ወቅት ነው፡፡
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት ፆታዊ ጥቃትንም ሆነ ኤድስን ለመከላከል ተግባራዊ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ሁሉም የአካዳሚው ማህበረሰብ ከመድረኩ የሚያገኘውን ግንዛቤ ወደ ተግባር በመለወጥ ለሴቶች ያለውን ድጋፍና አጋርነት በተግባር ማሳየት ይገባል ሲሉም አክለዋል፡፡
በአካዳሚው የሴቶች፣ ወጣቶች እና ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ በበኩላቸው ተቋሙ የፆታ ጥቃትን ለመከላከልና ወላጆቻቸውን በኤድስ ያጡ ህጻናትን ለመደገፍ ያለውን ጥረት አመላክተው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀንን በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብሮች ሱሉሉታ በሚገኘው የስልጠና ማዕከል ውስጥ አክብረዋል፡፡
ይኽ የተገለፀው ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀን በአካዳሚ ደረጃ ሲከበር ነው፡፡ አለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን "ሴትን አከብራለሁ፤ ጥቃቷንም እከላከላለሁ!" እንዲሁም አለም አቀፍ የኤድስ ቀን "ፍትሃዊና ተደራሽ የኤች አይ ቪ/ኤድስ አገልግሎት! በሚል መሪ ቃል በእግር ጉዞ እና በውይይት በተከበረበት ወቅት ነው፡፡
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት ፆታዊ ጥቃትንም ሆነ ኤድስን ለመከላከል ተግባራዊ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ሁሉም የአካዳሚው ማህበረሰብ ከመድረኩ የሚያገኘውን ግንዛቤ ወደ ተግባር በመለወጥ ለሴቶች ያለውን ድጋፍና አጋርነት በተግባር ማሳየት ይገባል ሲሉም አክለዋል፡፡
በአካዳሚው የሴቶች፣ ወጣቶች እና ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ በበኩላቸው ተቋሙ የፆታ ጥቃትን ለመከላከልና ወላጆቻቸውን በኤድስ ያጡ ህጻናትን ለመደገፍ ያለውን ጥረት አመላክተው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀንን በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብሮች ሱሉሉታ በሚገኘው የስልጠና ማዕከል ውስጥ አክብረዋል፡፡
Research Validation workshop at AFLEX
AFLEX holds a workshop on the Pan African Now: Pan Africanism for a changing world
Today, January 20, 2023, the African Leadership Excellence Academy, AFLEX, holds a discussion on Pan Africanism Now: Pan Africanism for a changing world here at Skylight Hotel Addis Ababa.
According to Dr.Shimles, the purpose of the workshop is research output validation.
Dr. Shimles Offered the Source, The argument, the background, significance, objectives, research questions, and what can be done as part of the broadsheet.
After the presentation, a discussion was apprehended on the topic. Participants outstretched their questions and perceptions and the questions were responded.
Finally, the head of the African Leadership Excellence Academy, Dr. Mehret Debebe, gave an explanation of the presentation given on the topic and told the inputs given by the participants are vital.
The presentation was moderated by professor Brook Hailu Senior Advisor of AFLEX.
AFLEX holds a workshop on the Pan African Now: Pan Africanism for a changing world
Today, January 20, 2023, the African Leadership Excellence Academy, AFLEX, holds a discussion on Pan Africanism Now: Pan Africanism for a changing world here at Skylight Hotel Addis Ababa.
According to Dr.Shimles, the purpose of the workshop is research output validation.
Dr. Shimles Offered the Source, The argument, the background, significance, objectives, research questions, and what can be done as part of the broadsheet.
After the presentation, a discussion was apprehended on the topic. Participants outstretched their questions and perceptions and the questions were responded.
Finally, the head of the African Leadership Excellence Academy, Dr. Mehret Debebe, gave an explanation of the presentation given on the topic and told the inputs given by the participants are vital.
The presentation was moderated by professor Brook Hailu Senior Advisor of AFLEX.
በትውውቅ መርሀ ግብሩ ላይ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክ፤ ከመከላከያ፤ ከትምህርት፤ ከኢንዱስትሪ፤ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ፤ ከግብርና ሚ/ር መስሪያ ቤቶች፤ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል፤ ከኢትዮ ኢንጂነሪንግ፤ ከስፔስ ሳይንስ፤ ከምድር ባቡር፤ ከፌዴራል ፖሊስ እና ሌሎችም ተቋማት የመጡ ተሳታፊዎች የተካፈሉ ሲሆን ሱሉሉታ የሚገኘውን የአካዳሚውን የስልጠና ማዕከልም ጎብኝተዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከሜሊንዳ እና ቢልጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን ለሚሰጠው የሴቶች አመራር ልማት ስልጠና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብር ተከናወነ፡፡ ሰልጣኞችም የእርስ በእርስ ትውውቅ አድርገዋል፡፡
የትውውቅ መርሀ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የአካዳሚው የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ እንደተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እንደ አዲስ በህግ ከተቋቋመ ጀምሮ በስልጠና እና በምርምር የሰራቸውን ስራዎች የገለፁ ሲሆን የከፍተኛ አመራር ስልጠናን በመስጠት ላይ እንደሆነና ለፖሊሲ አውጭውና ለስልጠና ፕሮግራሙ ግብዓት የሚውሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የስልጠናውን መስፈርት አሟልተው ከተለያዩ ተቋማት የመጡ ሴት የስልጠና ተሳታፊዎችን አቅም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አካዳሚው የራሱን ሚና እንደሚጫወትና ስልጠናውን ተከታትለው በቁርጠኝነት የሚያጠናቅቁ ተሳታፊዎችም በሀገር ግንባታ ውስጥ የራሳቸውን የአመራር ድርሻ እንዲያበረክቱ ድጋፍና እገዛ እንደሚደረግና ሰልጣኞችም ስልጠናውን በተገቢው መንገድ እንዲከታተሉና ለውጤት እንዲበቁ ም/ል ርዕሰ አካዳሚዋ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡
የሴቶች አመራር ልማት ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ መስፍን በሀይሉ የፕሮጀክቱን ዓላማ በስፋት የገለፁ ሲሆን ሰልጣኞች ወደ ፊት ስለሚሰለጥኑባቸው ርዕሰ ጉዳዮችና ከስልጠናው የሚጠበቀውን ውጤትም አብራርተዋል፡ ስልታዊ አስተሳሰብን ማበልፀግ፤ ችግርን ተረድቶ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መፍታት፤ ውጤታማ የተግባቦት ክህሎትን ማሳደግ፤ የቡድን ስራ ግንባታና የባለድርሻ አካላት ስራ አመራር ከስልጠናው የሚጠበቁ ውጤቶች መሆናቸውንም አቶ መስፍን ጠቅሰዋል፡፡
የትውውቅ መርሀ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የአካዳሚው የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ እንደተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እንደ አዲስ በህግ ከተቋቋመ ጀምሮ በስልጠና እና በምርምር የሰራቸውን ስራዎች የገለፁ ሲሆን የከፍተኛ አመራር ስልጠናን በመስጠት ላይ እንደሆነና ለፖሊሲ አውጭውና ለስልጠና ፕሮግራሙ ግብዓት የሚውሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የስልጠናውን መስፈርት አሟልተው ከተለያዩ ተቋማት የመጡ ሴት የስልጠና ተሳታፊዎችን አቅም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አካዳሚው የራሱን ሚና እንደሚጫወትና ስልጠናውን ተከታትለው በቁርጠኝነት የሚያጠናቅቁ ተሳታፊዎችም በሀገር ግንባታ ውስጥ የራሳቸውን የአመራር ድርሻ እንዲያበረክቱ ድጋፍና እገዛ እንደሚደረግና ሰልጣኞችም ስልጠናውን በተገቢው መንገድ እንዲከታተሉና ለውጤት እንዲበቁ ም/ል ርዕሰ አካዳሚዋ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡
የሴቶች አመራር ልማት ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ መስፍን በሀይሉ የፕሮጀክቱን ዓላማ በስፋት የገለፁ ሲሆን ሰልጣኞች ወደ ፊት ስለሚሰለጥኑባቸው ርዕሰ ጉዳዮችና ከስልጠናው የሚጠበቀውን ውጤትም አብራርተዋል፡ ስልታዊ አስተሳሰብን ማበልፀግ፤ ችግርን ተረድቶ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መፍታት፤ ውጤታማ የተግባቦት ክህሎትን ማሳደግ፤ የቡድን ስራ ግንባታና የባለድርሻ አካላት ስራ አመራር ከስልጠናው የሚጠበቁ ውጤቶች መሆናቸውንም አቶ መስፍን ጠቅሰዋል፡፡
በኢትዮጵያ የሚገኙ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎበኙ፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡