African Leadership Excellence Academy
2.12K subscribers
2.38K photos
89 videos
6 files
104 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ አውድን በመገንዘብ እየተገኙ ያሉ ስኬቶችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡

በአፍሌክስ የስትራቴጂ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ አቶ ሲሳይ ዘሪሁን የአካዳሚውን የ 2017 ዓ. ም የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል ።
መሰረታዊ አገልግሎትን ማቀላጠፍ እና ፋሲሊቲ ማዘመንና አገልግሎት አሰጣጥንና ቅልጥፍና በማሳደግ ረገድ በተሰራው የአገልግሎት እርካታ ዳሰሳ ጥናት የአገልግሎቶች እርካታ የ9ወሩ አማካይ ከ96% በላይ ለማድረስ መቻሉን ገልጸዋል።

የመሰረተ ልማት ፕሮጀክት ላይ ሱሉልታ የሚገኘውን የአስተዳደር ህንጻ የማገባደድ ስራ እየተከናወነ እንደሆነና የአካዳሚው ዋና የስራ ቦታ ወደ ሱሉልታ የሚዞር መሆኑን ተናግረዋል።

በአካዳሚው የሚሰጡ ስልጠናዎች የሥነ ምግባር ግንባታ እና የሞራል ግንባታን ያካተቱ እንዲሆኑ የመከታተል ስራም ተሰርቷል ብለዋል።
በሚዲያና ኮሚኒኬሽን የአካዳሚውን ገጽታ ለማሻሻልና ለመገንባት የተለያዩ የተግባቦት መሳሪያዎችን እና ስልቶችን በመጠቀም የተቋሙን ስራዎች ለማስተዋወቅ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውንም አብራርተዋል።

በቀረበው ገለጻ ላይ የአካዳሚው ሰራተኞች ሃሳባቸውን አንስተው የተወያዩ ሲሆን ለተነሱት ጥያቄዎችም ምላሽ ተሰጥቷቸዋል።
በአጠቃላይ እቅዱ አፈጻጸም ከተቀመጠው ግብ አንጻር 87.67 % ያሳካ እንደሆነ ተገልጿል።
አፍሌክስ ከሲዲ ሞሀመድ ቤን አብደላህ ዩኒቨርሲቲ ጋር አጋርነት መሰረተ

አዲስ አበባ/ ሚያዚያ 8/2017 (አፍሌክስ) -
አካዳሚው መገኛውን በፌዝ፣ ሞሮኮ ካደረገው የሲዲ ሞሀመድ ቤን አብደላህ ዩኒቨርሲቲ ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራርሟል።

ትብብሩ በአመራር ልማት እና ተያያዥ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው።

አፍሌክስን በመወከል የአካዳሚው ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ፣ የሞሮኮውን ዩኒቨርሲቲ ወክለው ደግሞ የዩኒቨርሲቲው የሳይንሳዊ ጥናትና ትብብር ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ኤል መስታፋ ኤል ሃድራሚ የመግባቢያ ሰነዱን ፈርመዋል። የፊርማ ስነ ስርዓቱ በአፍሌክስ ዋና መስሪያ ቤት በቨርቹዋል መንገድ ተከናውኗል።

አቶ ዛዲግ አብርሃ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር "ኢትዮጵያ እና ሞሮኮ ብዙ የሚያመሳስላቸው ሁለት በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት ናቸው። ከሞሮኮ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ስናስብ ቆይተናል እናም የዛሬው ፊርማ ይህን ሃሳብ ወደተግባር የምንቀይርበት ትልቅ ምዕራፍ ነው" ብለዋል። የሚቀጥለው እርምጃ በትብብር መስኮች ላይ የስራ ሂደቱን የሚመራ ኮሚቴ ማቋቋም መሆኑን በመግለጽ ስምምነቱን ለመፈጸም አፍሌክስ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

ፕሮፌሰር ኤል ሃድራሚ በበኩላቸው ስለ ትብብሩ ሲናገሩ "ይህ ስምምነት በሁለቱ ተቋማት አልፎም በኢትዮጵያና በሞሮኮ መካከል አካዳሚክ ትብብርን የሚያሳድግ እና ውጤታማ የአመራር ልማትን የሚያስፋፋ ነው“ ብለዋል።

የመግባቢያ ሰነዱ የሁለቱን ተቋማት ግንኙነት ለማጠናከር እና የአመራር ክህሎትን ለማሻሻል የሚረዱ የእውቀትና የልምድ ልውውጥን እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን ለመከወን መሰረት የሚጥል መሆኑ ተገልጿል።
እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!!

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እና ለአፍሌክስ ቤተሰቦች በሙሉ በአሉ የሰላም እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ::

መልካም በአል!

ዛዲግ አብርሃ
የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት
የአፍሌክስ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚሰጡትን የአመራር ልማት ስልጠና እንደቀጠሉ ነው::

በቀጣይ የሚሰጡ ስልጠናዎችን አሳውቁን ባላችሁት መሰረት በቀጣይ ሳምንታት ወደ እናንተ በአካዳሚው የዩቱዩብ ቻናል እና የፌስቡክ ገፃችን የምናደርሳቸውን የአመራር ልማት የስልጠና ቪዲዮዎች ስንጠቁማችሁ በክብር ነው::

1. The power and the art of execution and the fate of our generation from individual to national

2.The science and the art of finishing from individual to national endeavours

3. The key to the secret of leaders and leadership development from individual to national endeavours

4.Communication and its manifold benefits and practices, Communication as a tool of conflict resolution and peacebuilding

5. The power of ideas and our destiny from individual to national

በቅርቡ ይጠብቁን!! በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን ላይ ያገኙናል!!
የአፍሌክስ ፕሬዚደንት ዛዲግ አብርሃ በሚል ርዕስ #የማወቅ_የመፈጸምና_በማያቋርጥ_ሁኔታ_ውጤታማ_የመሆን_ምስጢርና_የጉጉት_ኃይልና_አስተዋጽኦ ለአመራሮች የሰጡትን የአመራር ልማት ስልጠና ከአካዳሚው ዩቱዩብ ቻናል እና የፌስቡክ ገጽ ይከታተሉ። በዩቱዩብ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://www.youtube.com/watch?v=TkDJRy1GNTI

👉 የአንድን ሰው፤ የአንድን ተቋም እና የአንድ ሀገር መነሻዎች የሚወስኑት አራት ነገሮች ምንድን ናቸው?

👉 የት መሔድ ነው የምንፈልገው? የት ነበርን? ዛሬስ የት ላይ ነን? ነገ የት መሔድ ነው የምንፈልገው ? እነዚህን ጥያቄዎች የመለሱ ግለሰቦች፤ ተቋማት እና ሀገራት ምን ያገኛሉ?

👉 ሰዎች የረጅም ጊዜ አሻጋሪ የስትራቴጂ ስራዎችን ትተው በዛሬ ስራ ላይ ለምን ይጠመዳሉ?

👉 አንድን ሀሳብ ማሰብ ብቻ የት ያደርሳል? መፈጸምስ?

👉 የተሟላ ስትራተጂ ምልከታ ያለው ግለሰብ፤ ተቋም እና መሪ ሀሳቡን ወደ ተጨባጭ ስትራቴጂ ለመቀየር ምን ያስፈልገዋል?

👉 የወደፊቱን የሚያስቡ ግለሰቦች፤ ቡድኖች፤ ካምፓኒዎች፤ መሪዎች እና ሀገራት መለያቸው ምንድን ነው?

👉 የጉጉታችን መነሻ ምንድን ነው? ጉጉት የምንለውስ የትኛውን ነው? ትክክለኛ ጉጉታችንን በምን እንለየዋለን?
የልህቀት አካዳሚና የጋራ ምክር ቤቱ በአቅም ግንባታና ምርምሮች በጋራ ለመሥራት የደረሱበትን ስምምነት ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በአቅም ግንባታ፣ ጥናትና ምርምሮች ላይ በጋራ ለመሥራት የደረሱበትን ስምምነት ተግባራዊ ማድረግ ጀምረዋል።

ተቋማቱ ህዳር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

የመግባቢያ ሰነዱን ወደ መሬት ለማውረድ ከሁለቱ ተቋማት የተውጣጣ የቴክኒክ ቡድን በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት ላይ የጋራ ዕቅድ አዘጋጅቷል።

በዛሬው ዕለትም በተዘጋጀው ዕቅድ ዙሪያ የአካዳሚው እና የጋራ ምክር ቤቱ አመራር አባላት የተወያዩ ሲሆን፤ በአቅም ግንባታ፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች በጋራ የመስራት እንቅስቃሴ ጀምረዋል።

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት መሰረት ደስታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በስምምነቱ መሰረት አካዳሚው ለፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባlaት የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን ይሰጣል።

በዚህም ያሉ ክፍተቶችን በጥናት በመለየት እንደሚሰራ ጠቁመው፤ የፖሊሲ ማማከር ሥራዎችንም አካዳሚው እንደሚያከናውን አብራርተዋል።

በዚህ ዓመት ለ120 የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት የአቅም ግንባታ ሥልጠና እንደሚሰጥ ገልጸው፤ ሥልጠናው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስረድተዋል።

በኢትዮጵያም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ ሁኔታዎችን በላቀ ደረጃ የሚረዳና በቂ ግንዛቤ የጨበጠ አመራር ወሳኝ ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቷ፤ በተቋማቱ መካከል የተደረገው ትብብር ይሄን ግብ ለማሳካት ያለመ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ በበኩላቸው፤ ያለን አንድ ሀገር ነው፤ ኢትዮጵያን በጋራ ለመገንባት መረባረብ አለብን ነው ያሉት።

በስምምነቱ መሰረት ኢትዮጵያን በጋራ መገንባት የሚያስችሉ ሀሳቦች የሚንሸራሸርባቸው የውይይት መድረኮች እንደሚካሄዱም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ሰፍኖ የቆየውን የፖለቲካ ስብራት ለመጠገን መሰል ትብብሮች ቁልፍ ሚና እንዳላቸውም ነው ያስረዱት።

ምክር ቤቱ ከአካዳሚው ጋር በፈጠረው ግንኙነት ሀገራዊ አስተዋጽኦን የሚያሳድግበት ልምድ የቀሰመ ሲሆን፤ ግንኙነቱ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሥራ አስፈጻሚ አቶ መለሰ ዓለሙ በበኩላቸው፤ ተቋማቱ በጋራ ለመስራት መወሰናቸው ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አዎንታዊ ሚና ይጫወታል።

ተቋማቱ በጋራ ለመተግበር የያዟቸው ግቦች እንዲሳኩ ሁሉን አቀፍ ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።
የመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን ሴት አመራሮች በአፍሌክስ የአመራር ልማት ስልጠና ወሰዱ

ሱሉልታ ሚያዚያ 17/2017 (አፍሌክስ) - የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ሴት አመራሮች ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሌክስ የአመራር ልማት ማዕከል የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል።

መርሃ ግብሩ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን ሴት የቡድን መሪዎችን እና ስራ አስፈፃሚዎች ጨምሮ 44 ተሳታፊዎችን ይዟል።

ስልጠናው የአመራር ልማት እና የልቦና ውቅር ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ለተቋም አመራር ወሳኝ የሆኑ ርዕሶችንም አካቷል።

ስልጠናው መሪዎቹ በስራ ላይ የሚገጥሙ ውስብስብ ፈተናዎችን በመፈተሽ እና አወንታዊ የስራ አካባቢን በመፍጠር ውጤታማ የለውጥ አመራርን መተግበር እንዲችሉ ማገዝን አላማው አድርጓል።

የአመራር መርሆዎችን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያስችሉ ገለጻዎች እና ውይይቶች የስልጠናው አካላት ናቸው።