የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ስልጠና እየሰጠ ነው
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ኃላፊዎች ስልጠና እየሰጠ ሲሆን ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) አካዳሚው የተቋቋመው ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁሉም ደረጃ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እና የሀገሪቱን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም፣ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የአመራር አካላት አቅምን ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው አያይዘውም አካዳሚው በንድፈ ሀሳብ የተደገፈ ተግባር ተኮር የአመራር ስልጠና እንደሚሰጥ ገልፀው ስልጠናው The Art of finishing well በተለይም the proof of Integrity and The mark of Excellence በሚልና በሌሎች ርዕሶች ላይ በተለያዩ አሰልጣኞች እንደሚሰጥ አስታውቀዋል፡፡
የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋም የሚመሰረተው ጠንካራና ተባብረው በሚሰሩ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች መሆኑን አስታውቀው ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ኃላፊዎች ስልጠና እየሰጠ ሲሆን ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) አካዳሚው የተቋቋመው ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁሉም ደረጃ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እና የሀገሪቱን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም፣ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የአመራር አካላት አቅምን ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው አያይዘውም አካዳሚው በንድፈ ሀሳብ የተደገፈ ተግባር ተኮር የአመራር ስልጠና እንደሚሰጥ ገልፀው ስልጠናው The Art of finishing well በተለይም the proof of Integrity and The mark of Excellence በሚልና በሌሎች ርዕሶች ላይ በተለያዩ አሰልጣኞች እንደሚሰጥ አስታውቀዋል፡፡
የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋም የሚመሰረተው ጠንካራና ተባብረው በሚሰሩ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች መሆኑን አስታውቀው ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) በወሎ ዩኒቨርሲቲ ኮምበልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ግቢ በመምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና እና ውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ቁልፍ ንግግር አድርገዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በቁልፍ ንግግራቸውም እንደገለፁት በጦርነቱ የዩንቨርስቲው የማስተማርያ ግብዓቶችና መሰረተ ልማቶች በመዘረፋቸውና በመውደማቸው ከልብ ማዘናቸውን ተናግረው የሰው ልጅ ትልቁ ሀብት የሆነው ህሊና ባለመዘረፉ ዳግም ወደስራ ለመመለስ የሚገድብ ነገር እንደሌለ ግንዛቤ በመፍጠር የዩኒቨርስቲውን ማህበረሰብ የስራ መንፈስ አነሳስተዋል፡፡
ምህረት ደበበ (ዶ/ር) የህሊና መኖርንና አለመዘረፍ ጠቀሜታ ሲተነትኑ የሰው ልጅ ትልቁ ሀብትና የሁሉ ነገር ምንጭ ህሊና ነው፡፡ ገንዘብ ማስፈጸሚያ እንጂ ከህሊና በበለጠ መልኩ ዋጋ የለውም፡፡ ይህ ሀብት አልተዘረፈም፡፡ የዚህ ሀብት ዋና ሞተር የሆነው አእምሯችን አልተዘረፈም፡፡ ማሰብ እንችላለን ሊቆስል ይችል ይሆናል ሆኖም ግን ይታከማል፡፡ ገንዘብም ይተካል የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ለህሊናችን ዋጋ በመስጠትና በቀረው ሀብት ላይ በመመስረት ወደነበርንበት ብቻ ሳይሆን ወደተሻለ አሰራር ገብተን ዩኒቨርሲተያችንን መለወጥ እንችላለን የሚል እምነት ሊኖረን ይገባል በማለት የሰራተኛውን ሞራል ገንብተዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በዚህም ሂደት አራት መሰረታዊ መዋቅሮች አንዳሉ በማሰገንዘብ አነሱም የመሰረተ ልማት መዋቅር፣ የህግ መዋቅር፣ የልቦና መዋቅርና የህሊና መዋቅር ሲሆኑ የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ መዋቅሮች ከሰው ውጭ ያሉ ሊወድሙ ወይም ሊዘረፉ የሚችሉ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሁለቱ ግን በሰው ውስጥ ያሉ የማይዘረፉ ለሰው ልጅ ትልቁ ሀብት እንደሆኑ አጽንኦት በመስጠት በዩኒቨርስቲው ውስጥ ታላቅ የስራ መነሳሳት ፈጥረዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በቁልፍ ንግግራቸውም እንደገለፁት በጦርነቱ የዩንቨርስቲው የማስተማርያ ግብዓቶችና መሰረተ ልማቶች በመዘረፋቸውና በመውደማቸው ከልብ ማዘናቸውን ተናግረው የሰው ልጅ ትልቁ ሀብት የሆነው ህሊና ባለመዘረፉ ዳግም ወደስራ ለመመለስ የሚገድብ ነገር እንደሌለ ግንዛቤ በመፍጠር የዩኒቨርስቲውን ማህበረሰብ የስራ መንፈስ አነሳስተዋል፡፡
ምህረት ደበበ (ዶ/ር) የህሊና መኖርንና አለመዘረፍ ጠቀሜታ ሲተነትኑ የሰው ልጅ ትልቁ ሀብትና የሁሉ ነገር ምንጭ ህሊና ነው፡፡ ገንዘብ ማስፈጸሚያ እንጂ ከህሊና በበለጠ መልኩ ዋጋ የለውም፡፡ ይህ ሀብት አልተዘረፈም፡፡ የዚህ ሀብት ዋና ሞተር የሆነው አእምሯችን አልተዘረፈም፡፡ ማሰብ እንችላለን ሊቆስል ይችል ይሆናል ሆኖም ግን ይታከማል፡፡ ገንዘብም ይተካል የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ለህሊናችን ዋጋ በመስጠትና በቀረው ሀብት ላይ በመመስረት ወደነበርንበት ብቻ ሳይሆን ወደተሻለ አሰራር ገብተን ዩኒቨርሲተያችንን መለወጥ እንችላለን የሚል እምነት ሊኖረን ይገባል በማለት የሰራተኛውን ሞራል ገንብተዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በዚህም ሂደት አራት መሰረታዊ መዋቅሮች አንዳሉ በማሰገንዘብ አነሱም የመሰረተ ልማት መዋቅር፣ የህግ መዋቅር፣ የልቦና መዋቅርና የህሊና መዋቅር ሲሆኑ የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ መዋቅሮች ከሰው ውጭ ያሉ ሊወድሙ ወይም ሊዘረፉ የሚችሉ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሁለቱ ግን በሰው ውስጥ ያሉ የማይዘረፉ ለሰው ልጅ ትልቁ ሀብት እንደሆኑ አጽንኦት በመስጠት በዩኒቨርስቲው ውስጥ ታላቅ የስራ መነሳሳት ፈጥረዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ወላጆቻቸውን በተለያዩ ምክንያቶች ላጡ ህጻናት ድጋር አደረገ
ድጋፉን ለህጻናቱ አሳዳጊዎች ያስረከቡት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ ልጆች ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ብሎም ሀገርን የሚጠቅሙ ትልቅ ደረጃ ላይ እንዲደርሱና ታላላቅ መሪዎች እንዲሆኑ አካዳሚው የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
የአካዳሚው የስርዓተ ጾታና ባለብዙ ዘርፍ ማስተባበር ክፍል ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ በበኩላቸው የአካዳሚው ሰራተኞች ከደመወዛቸው ላይ ተቆራጭ በማድረግ ስምንት(8) ህጻናትን በየወሩ እንደሚደግፉ በማስታወስ በቀጣይም ድጋፉን በተሸለ ሁኔታ ለማስቀጠል መታቀዱን አስታውቀዋል፡፡
ድጋፉን ለህጻናቱ አሳዳጊዎች ያስረከቡት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ ልጆች ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ብሎም ሀገርን የሚጠቅሙ ትልቅ ደረጃ ላይ እንዲደርሱና ታላላቅ መሪዎች እንዲሆኑ አካዳሚው የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
የአካዳሚው የስርዓተ ጾታና ባለብዙ ዘርፍ ማስተባበር ክፍል ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ በበኩላቸው የአካዳሚው ሰራተኞች ከደመወዛቸው ላይ ተቆራጭ በማድረግ ስምንት(8) ህጻናትን በየወሩ እንደሚደግፉ በማስታወስ በቀጣይም ድጋፉን በተሸለ ሁኔታ ለማስቀጠል መታቀዱን አስታውቀዋል፡፡
ዜና ሹመት
############
ወ/ሮ ህይወት አለማየሁ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ እንዲሁም አቶ ወንድዬ ለገሰ በስራ አመራር ኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ተሹመዋል፡፡
የአካዳሚው ማህበረሰብም መልካም የስራ ዘመን ተመኝተውላቸዋል፡፡
############
ወ/ሮ ህይወት አለማየሁ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ እንዲሁም አቶ ወንድዬ ለገሰ በስራ አመራር ኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ተሹመዋል፡፡
የአካዳሚው ማህበረሰብም መልካም የስራ ዘመን ተመኝተውላቸዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሱሉልታ ከተማ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶችና የወጣቶች ማዕከል የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡
የድጋፍ ርክክቡ የተደረገው የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አቡ ብርኪ እና ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ሲሆን ምክትል ከንቲባው አካዳሚው የትምህርት ተቋማትንና የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያን ለመደገፍ የወሰነውን ውሳኔ አድንቀው የተደረገው ድጋፍ ለትምህርት ጥራትና ለመማር ማስተማሩ ተግባር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡
ምክትል ከንቲባው አያይዘው ተቋሙ በሱሉልታ ከተማ እንደመገኘቱ ለከተማዋ ዕድገትና ልማት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው አስታውሰው በቀጣይም ከተቋሙ ጋር ለመስራትና አካዳሚውን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
የአካዳሚው የሰልጣኞችና ተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ሔኖክ አስፋው በበኩላቸው ተቋሙ ለከተማ አስተዳደሩ ያደረገው ድጋፍ የመጀመሪያው እንዳልሆነና ከዚህ ቀደም ለከተማው ስድስት አመራሮች የሁለተኛ ዲግሪ እና አንድ የሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት ዕድል መስጠቱን አስታውሰው አካዳሚው ከአመራሩ ልማት ባሻገር በማህበረሰባዊ አገልግሎት ላይ እየተሳተፈ እንደሆነና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
ለሁለት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ለአንድ የወጣቶች ማዕከል ከተደረገው ድጋፍ ውስጥ ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ ፕሮጀክተር፣ ፎቶ ኮፒየር፣ ቴሌቪዥን ተጠቃሾች ሲሆኑ የንብረቶቹ አጠቃላይ ግምትም 800,000.00 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡
የድጋፍ ርክክቡ የተደረገው የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አቡ ብርኪ እና ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ሲሆን ምክትል ከንቲባው አካዳሚው የትምህርት ተቋማትንና የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያን ለመደገፍ የወሰነውን ውሳኔ አድንቀው የተደረገው ድጋፍ ለትምህርት ጥራትና ለመማር ማስተማሩ ተግባር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡
ምክትል ከንቲባው አያይዘው ተቋሙ በሱሉልታ ከተማ እንደመገኘቱ ለከተማዋ ዕድገትና ልማት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው አስታውሰው በቀጣይም ከተቋሙ ጋር ለመስራትና አካዳሚውን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
የአካዳሚው የሰልጣኞችና ተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ሔኖክ አስፋው በበኩላቸው ተቋሙ ለከተማ አስተዳደሩ ያደረገው ድጋፍ የመጀመሪያው እንዳልሆነና ከዚህ ቀደም ለከተማው ስድስት አመራሮች የሁለተኛ ዲግሪ እና አንድ የሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት ዕድል መስጠቱን አስታውሰው አካዳሚው ከአመራሩ ልማት ባሻገር በማህበረሰባዊ አገልግሎት ላይ እየተሳተፈ እንደሆነና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
ለሁለት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ለአንድ የወጣቶች ማዕከል ከተደረገው ድጋፍ ውስጥ ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ ፕሮጀክተር፣ ፎቶ ኮፒየር፣ ቴሌቪዥን ተጠቃሾች ሲሆኑ የንብረቶቹ አጠቃላይ ግምትም 800,000.00 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡