"ተቀባይነት ማጣት ለሰነፍ ተስፋ መቁረጫ፡ ለብርቱ ደግሞ የቁጭት እና የብርታት ምንጭ ነው!" ዛዲግ አብርሃ፡ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
የአፍሌክስ ስልጠና 5ተኛ ቀን ውሎ
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - ዛሬ 5ተኛ ቀኑን ባሳቆጠረው ስልጠና አቶ ዛዲግ አብርሃ አትችልም ተብሎ ተቀባይነት ማጣትን ወደ ትልቅ እድል መቀየር ይቻላል ሲሉ ተናገሩ።
ተስፋ ያለመቁረጥን እና የሁለተኛ እድልን ላይ ትኩረት ሰጥተው በሰፊው የዳሰሱት አቶ ዛዲግ፡ በአለማችን በተደጋጋሚ ተቀባይነት አጥተው ተስፋ ባለመቁረጥ ታትረው ከስኬት የደረሱ ግለሰቦችን፤ ተቋማትን እና ሀገራትን እንደምሳሌ በማንሳት ተቀባይነት ማጣት ወድቆ መቅረት አለመሆኑን አስረድተዋል።
በንግግራቸው "ተቀባይነት ማጣት ለሰነፍ ተስፋ መቁረጫ፡ ለብርቱ ደግሞ የቁጭት እና የብርታት ምንጭ ነው!" ብለዋል።
"አፍሌክስ ሁለተኛ እድል ያገኘ ተቋም ነው!" ብለው፡ "ይህንን ሁለተኛ እድል ተጠቅሞ አካዳሚው ያነገበውን ታላቅ ራዕይ ከግብ በማድረስ ታላቅ አፍሪካዊ ተቋም ለማድረግ የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል" ሲሉ አሳስበዋል።
"ኢትዮጵያ የአፍሪካን መሪዎች የማሰልጠን አኩሪ ታሪኳን በአፍሌክስ አጠናክራ እንድታስቀጥል እኛ ሃላፊነት አለብን!" ብለዋል።
የአፍሌክስ ስልጠና 5ተኛ ቀን ውሎ
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - ዛሬ 5ተኛ ቀኑን ባሳቆጠረው ስልጠና አቶ ዛዲግ አብርሃ አትችልም ተብሎ ተቀባይነት ማጣትን ወደ ትልቅ እድል መቀየር ይቻላል ሲሉ ተናገሩ።
ተስፋ ያለመቁረጥን እና የሁለተኛ እድልን ላይ ትኩረት ሰጥተው በሰፊው የዳሰሱት አቶ ዛዲግ፡ በአለማችን በተደጋጋሚ ተቀባይነት አጥተው ተስፋ ባለመቁረጥ ታትረው ከስኬት የደረሱ ግለሰቦችን፤ ተቋማትን እና ሀገራትን እንደምሳሌ በማንሳት ተቀባይነት ማጣት ወድቆ መቅረት አለመሆኑን አስረድተዋል።
በንግግራቸው "ተቀባይነት ማጣት ለሰነፍ ተስፋ መቁረጫ፡ ለብርቱ ደግሞ የቁጭት እና የብርታት ምንጭ ነው!" ብለዋል።
"አፍሌክስ ሁለተኛ እድል ያገኘ ተቋም ነው!" ብለው፡ "ይህንን ሁለተኛ እድል ተጠቅሞ አካዳሚው ያነገበውን ታላቅ ራዕይ ከግብ በማድረስ ታላቅ አፍሪካዊ ተቋም ለማድረግ የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል" ሲሉ አሳስበዋል።
"ኢትዮጵያ የአፍሪካን መሪዎች የማሰልጠን አኩሪ ታሪኳን በአፍሌክስ አጠናክራ እንድታስቀጥል እኛ ሃላፊነት አለብን!" ብለዋል።
"የተቋማት ግንባታ ጊዜ የሚወስድ ተግባር በመሆኑ ስራውን ዛሬ መጀመር አለብን!" ዛዲግ አብርሃ፣ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
የአፍሌክስ መለወጥ የግድ ነው ተባለ
ሱሉልታ መጋቢት 14/2017 (አፍሌክስ) -ለአካዳሚው አመራር እና ሰራተኞች ስልጠና በመስጠት ላይ የሚገኙት የአካዳሚው ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለውጥ ለአፍሌክስ ምርጫ ሳይሆን ብልጫ ነው ብለዋል።
የሃገራዊ ሪፎርሙ አካል መሆን፣ የአሰራር ስርዐቱን ማሻሻል፣ ድርጅታዊ ቁመናውን ማሳደግ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም ማድረግ እና መሰረታዊ ከሆነው የአመራር ልማት ለውጥ ጋር መጓዝ የአካዳሚው የለውጥ ጉዞ ዋነኛ ኢላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል።
በተቋማት የለውጥ ሒደት ውስጥ ተግዳሮቶችን ተቋቁመውና አሸንፈው የአሻጋሪነት ሚና የሚወስዱ ተቋማት እንዳሉ ሁሉ፤ በገጠማቸው የህልውና አደጋ ተሸንፈው ህልውናቸውን ያጡ ተቋማት በታሪክ እንደተመዘገቡ ጠቁመው "የአፍሌክስ ስኬት የአመራርና የሰራተኛው ስኬት በመሆኑ፤ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ እንደ ዐይኑ ብሌን ሊጠብቀውና ሊያስቀጥለው ይገባል።" ሲሉ ተናግረዋል።
አያይዘውም "የመጪውን ትውልድ መሪዎች የሚቀርጽ ተቋም ገንብተን ለትውልድ አሻራችንን እናኑር" የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የተቋም ግንባታንና ስልጣኔን ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚሉት አቶ ዛዲግ፤ እውነታውን ከአፍሌክስ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አዛምደው አስቀምጠዋል። "የተቋም ግንባታ ጊዜ የሚወስድ ተግባር በመሆኑ፣ ስራውን ዛሬ መጀመር አለብን!" ብለዋል።
የአፍሌክስ መለወጥ የግድ ነው ተባለ
ሱሉልታ መጋቢት 14/2017 (አፍሌክስ) -ለአካዳሚው አመራር እና ሰራተኞች ስልጠና በመስጠት ላይ የሚገኙት የአካዳሚው ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለውጥ ለአፍሌክስ ምርጫ ሳይሆን ብልጫ ነው ብለዋል።
የሃገራዊ ሪፎርሙ አካል መሆን፣ የአሰራር ስርዐቱን ማሻሻል፣ ድርጅታዊ ቁመናውን ማሳደግ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም ማድረግ እና መሰረታዊ ከሆነው የአመራር ልማት ለውጥ ጋር መጓዝ የአካዳሚው የለውጥ ጉዞ ዋነኛ ኢላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል።
በተቋማት የለውጥ ሒደት ውስጥ ተግዳሮቶችን ተቋቁመውና አሸንፈው የአሻጋሪነት ሚና የሚወስዱ ተቋማት እንዳሉ ሁሉ፤ በገጠማቸው የህልውና አደጋ ተሸንፈው ህልውናቸውን ያጡ ተቋማት በታሪክ እንደተመዘገቡ ጠቁመው "የአፍሌክስ ስኬት የአመራርና የሰራተኛው ስኬት በመሆኑ፤ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ እንደ ዐይኑ ብሌን ሊጠብቀውና ሊያስቀጥለው ይገባል።" ሲሉ ተናግረዋል።
አያይዘውም "የመጪውን ትውልድ መሪዎች የሚቀርጽ ተቋም ገንብተን ለትውልድ አሻራችንን እናኑር" የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የተቋም ግንባታንና ስልጣኔን ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚሉት አቶ ዛዲግ፤ እውነታውን ከአፍሌክስ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አዛምደው አስቀምጠዋል። "የተቋም ግንባታ ጊዜ የሚወስድ ተግባር በመሆኑ፣ ስራውን ዛሬ መጀመር አለብን!" ብለዋል።
"ኮሚዩኒኬሽን ግጭትን ለማለዘብ ያገለግላል።"
አቶ ዛዲግ አብርሃ: የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
በኮሚዩኒኬሽን እና የአመራር ልማት ላይ ስልጠና ተሰጠ
ሱሉልታ መጋቢት 17/2027 (አፍሌክስ) - የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ የኮሚዩኒኬሽንን እና የአመራር ልማት ስርዐትን ዘርፈ ብዙ ሚና ለአፍሌክስ አመራር እና ሰራተኞች በጥልቀት አብራርተዋል።
ኮሚዩኒኬሽን በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ በሁሉም መስክ የሚጫወተውን ዘርፈ ብዙ ሚና ሲያብራሩ በግጭት ውስጥ የሚኖረውን አሉታዊ እና አዎንታዊ አስተዋጽዖ ላይ ትኩረት አድርገዋል።
"ኮሚዩኒኬሽን ዋነኛ የግጭት አባባሽ ሁነት እንደሆነው ሁሉ፣ ዋነኛ የግጭት መፍቻ መሳሪያም ነው!" ብለዋል።
"ከገጽ ለገጽ ኮሚዩኒኬሽን ይልቅ ዲጂታል ኮሚዩኒኬሽን ለተዛባ አረዳድ የተጋለጠ በመሆኑ ግጭት በመቀስቀስ እና በማባባስ ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል።"
"ኮሚዩኒኬሽን ግጭትን ለማለዘብ ያገለግላል።" ብለው፣ ግጭትን በኮሚዩኒኬሽን ለማብረድ የሚረዱ ቁልፍ መንገዶችን ዘርዝረዋል።
ስለአመራር ልማት ስርዐት ሲያስረዱ "በአመራር ልማት ላይ የሚሰራው እያንዳንዱ ተግባር ድምር ውጤቱ ትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋት ነው።" ሲሉ ተደምጠዋል።
የአመራር ልማት ስርዐት አስፈላጊነት፣ ትላንት የነበረበት፣ ዛሬ ያለበት እና የወደፊት ጉዞ በፕሬዝደንቱ ማብራርያ ተዳስሠዋል።
የስኬታማ አመራር ልማት ስርዐት መገለጫዎችና የውጤታማ አመራር ልማት ማነቆዎችን ዘርዝረው፣ አፍሌክስ እንደአመራር ልማት ማዕከልነቱ እነዚህን በመለየት በአፍሪካ ሁነኛ የአመራር ልማት ስርዐት የመዘርጋት ሃላፊነት እንዳለበት አሳስበዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ: የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
በኮሚዩኒኬሽን እና የአመራር ልማት ላይ ስልጠና ተሰጠ
ሱሉልታ መጋቢት 17/2027 (አፍሌክስ) - የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ የኮሚዩኒኬሽንን እና የአመራር ልማት ስርዐትን ዘርፈ ብዙ ሚና ለአፍሌክስ አመራር እና ሰራተኞች በጥልቀት አብራርተዋል።
ኮሚዩኒኬሽን በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ በሁሉም መስክ የሚጫወተውን ዘርፈ ብዙ ሚና ሲያብራሩ በግጭት ውስጥ የሚኖረውን አሉታዊ እና አዎንታዊ አስተዋጽዖ ላይ ትኩረት አድርገዋል።
"ኮሚዩኒኬሽን ዋነኛ የግጭት አባባሽ ሁነት እንደሆነው ሁሉ፣ ዋነኛ የግጭት መፍቻ መሳሪያም ነው!" ብለዋል።
"ከገጽ ለገጽ ኮሚዩኒኬሽን ይልቅ ዲጂታል ኮሚዩኒኬሽን ለተዛባ አረዳድ የተጋለጠ በመሆኑ ግጭት በመቀስቀስ እና በማባባስ ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል።"
"ኮሚዩኒኬሽን ግጭትን ለማለዘብ ያገለግላል።" ብለው፣ ግጭትን በኮሚዩኒኬሽን ለማብረድ የሚረዱ ቁልፍ መንገዶችን ዘርዝረዋል።
ስለአመራር ልማት ስርዐት ሲያስረዱ "በአመራር ልማት ላይ የሚሰራው እያንዳንዱ ተግባር ድምር ውጤቱ ትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋት ነው።" ሲሉ ተደምጠዋል።
የአመራር ልማት ስርዐት አስፈላጊነት፣ ትላንት የነበረበት፣ ዛሬ ያለበት እና የወደፊት ጉዞ በፕሬዝደንቱ ማብራርያ ተዳስሠዋል።
የስኬታማ አመራር ልማት ስርዐት መገለጫዎችና የውጤታማ አመራር ልማት ማነቆዎችን ዘርዝረው፣ አፍሌክስ እንደአመራር ልማት ማዕከልነቱ እነዚህን በመለየት በአፍሪካ ሁነኛ የአመራር ልማት ስርዐት የመዘርጋት ሃላፊነት እንዳለበት አሳስበዋል።