African Leadership Excellence Academy pinned «የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ #የኮሙኒኬሽን_ኃይል_እና_የአመራር_ጥበብ በሚል ርዕስ ለከፍተኛ አመራሮች የሰጡትን #ክፍል_2 ስልጠና በአካዳሚው የዩቱዩብ ቻናል ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtu.be/hv3Q0klclPg»
"ለውጥን የምንመራበትን መንገድ መወሰን እንጂ ከለውጥ መሸሽ አንችልም" የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ
የአፍሌክስ አስተዳደር እና ሰራተኞች የአመራር ልማት ስልጠና መውሰድ ጀመሩ
ሱሉልታ፣ መጋቢት 9/2017 (አፍሌክስ) – የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ለተቋሙ አመራር እና ሰራተኞች 'ለውጥ እና የሀገራት ዕጣ ፈንታ' በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጥተዋል።
ዛሬ ጅማሮውን ያደረገው ለ6 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ስልጠና የመጀመሪያ ቀን ውሎ የአላማ ግልጽነት፣ የአመራር ልማት አስፈላጊነት፣ ለውጥ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በአካዳሚው ፕሬዝደንት ሰፊ ማብራርያ ተሰጥቷል።
አቶ ዛዲግ “የአላማ ግልጽነት በተቋም ውስጥ ከፉክክር ይልቅ ትብብር እንዲመጣ ያስችላል” ሲሉ ተናግረው ስለመሪነት እና የሃገራት እጣ ፈንታ ሲያስረዱ “የሃገራት ስኬትና ውድቀት ምክንያት ምንድነው ቢባል? ከምንም በላይ አመራር ነው” ብለዋል።
የትምህርት ስርዐታችን ሁሉንም ሰው ለመሪነት የሚያበቃ ሁሉን አቀፍ ባህርይ ስለሚጎድለው እንደአፍሌክስ ያሉ የአመራር ልማት ተቁማት አስፈላጊነት በእጅጉ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል።
በማብራርያቸው የለውጥን አይቀሬነት ሲናገሩ "ለውጥን የምንመራበትን መንገድ መወሰን እንጂ ከለውጥ መሸሽ አንችልም" በማለት ገልጸዋል።
ስልጠናው አካዳሚው እያካሄደ ያለውን የለውጥ ጉዞ በብቃት ለመምራት የሚያስችሉ ክህሎቶችን ለሰራተኞቹ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ቀጥሎ ሲካሄድ በነገው እለት አቶ ዛዲግ በለውጥ አመራር እና ተያያዥ ርዕሶች ላይ አሳታፊ ስልጠና ይሰጣሉ
የአፍሌክስ አስተዳደር እና ሰራተኞች የአመራር ልማት ስልጠና መውሰድ ጀመሩ
ሱሉልታ፣ መጋቢት 9/2017 (አፍሌክስ) – የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ለተቋሙ አመራር እና ሰራተኞች 'ለውጥ እና የሀገራት ዕጣ ፈንታ' በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጥተዋል።
ዛሬ ጅማሮውን ያደረገው ለ6 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ስልጠና የመጀመሪያ ቀን ውሎ የአላማ ግልጽነት፣ የአመራር ልማት አስፈላጊነት፣ ለውጥ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በአካዳሚው ፕሬዝደንት ሰፊ ማብራርያ ተሰጥቷል።
አቶ ዛዲግ “የአላማ ግልጽነት በተቋም ውስጥ ከፉክክር ይልቅ ትብብር እንዲመጣ ያስችላል” ሲሉ ተናግረው ስለመሪነት እና የሃገራት እጣ ፈንታ ሲያስረዱ “የሃገራት ስኬትና ውድቀት ምክንያት ምንድነው ቢባል? ከምንም በላይ አመራር ነው” ብለዋል።
የትምህርት ስርዐታችን ሁሉንም ሰው ለመሪነት የሚያበቃ ሁሉን አቀፍ ባህርይ ስለሚጎድለው እንደአፍሌክስ ያሉ የአመራር ልማት ተቁማት አስፈላጊነት በእጅጉ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል።
በማብራርያቸው የለውጥን አይቀሬነት ሲናገሩ "ለውጥን የምንመራበትን መንገድ መወሰን እንጂ ከለውጥ መሸሽ አንችልም" በማለት ገልጸዋል።
ስልጠናው አካዳሚው እያካሄደ ያለውን የለውጥ ጉዞ በብቃት ለመምራት የሚያስችሉ ክህሎቶችን ለሰራተኞቹ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ቀጥሎ ሲካሄድ በነገው እለት አቶ ዛዲግ በለውጥ አመራር እና ተያያዥ ርዕሶች ላይ አሳታፊ ስልጠና ይሰጣሉ
"መሪዎች ምሳሌ ሆነው መምራት ካልቻሉ ተቀባይነት አይኖራቸውም።" - ዛዲግ አብርሃ፣ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
የአፍሌክስ አመራር እና ሰራተኞች የሚወስዱት ስልጠና ቀጥሏል።
ሱሉልታ - መጋቢት 10/2017 (አፍሌክስ) - ሁለተኛ ቀኑን ባስቆጠረው ስልጠና ‘በምሳሌነት መምራት’፣ ‘ቃልን መጠበቅ’፣ ‘ታማኝነት’ እና ‘የሃሳብ ሃያልነት’ በሚሉ እሳቤዎች ዙሪያ በአካዳሚው ፕሬዝደን አቶ ዛዲግ አብርሃ ሰፊ ገለጻ ሲደረግ ውሏል።
“አፍሌክስ እንደ አመራር ልህቀት አካዳሚነቱ፣ ራሱን የብቁ አመራር ምሳሌ አድርጎ ለሌሎች ማሳየት አለበት።” ብለዋል አቶ ዛዲግ።
በመሪነት ውስጥ የገቡትን ቃል መፈጸም እና ታማኝነት ስለሚጫወቱት ወሳኝ ሚና ያብራሩት ፕሬዝደንቱ "መሪዎች ምሳሌ ሆነው መምራት ካልቻሉ ተቀባይነት አይኖራቸውም።" ሲሉ አሳስበዋል።
ታላላቅ ሃሳቦች አለማችንን እንዴት እንደቀየሩ ተግባራዊ ምሳሌዎችን በማንሳት የሃሳብን ሃያልነት በሰፊው አስረድተዋል።
በርካታ በጎ እንዲሁም መጥፎ ክስተቶችን ያስከተሉ ታላላቅ እሳቤዎችን አንስተዋል። በንግግራቸውም “ሃሳብ የማይሻገረው ወሰን እና ድንበር የለም!” ሲሉ ተደምጠዋል።
“ሃሳብ የግለሰቦችን ህይወት ከመቀየር ህብረተሰብን እስከማሻገር የሚደርስ ሃይል አለው።” ብለዋል።
ስልጠናው የአመራር ልማት እና የአመራር ልማት የሚሰጡ ተቋማት ላይ ትኩረት ባደረጉ ርዕሶች ነገም ቀጥሎ የሚካሄድ ይሆናል።
የአፍሌክስ አመራር እና ሰራተኞች የሚወስዱት ስልጠና ቀጥሏል።
ሱሉልታ - መጋቢት 10/2017 (አፍሌክስ) - ሁለተኛ ቀኑን ባስቆጠረው ስልጠና ‘በምሳሌነት መምራት’፣ ‘ቃልን መጠበቅ’፣ ‘ታማኝነት’ እና ‘የሃሳብ ሃያልነት’ በሚሉ እሳቤዎች ዙሪያ በአካዳሚው ፕሬዝደን አቶ ዛዲግ አብርሃ ሰፊ ገለጻ ሲደረግ ውሏል።
“አፍሌክስ እንደ አመራር ልህቀት አካዳሚነቱ፣ ራሱን የብቁ አመራር ምሳሌ አድርጎ ለሌሎች ማሳየት አለበት።” ብለዋል አቶ ዛዲግ።
በመሪነት ውስጥ የገቡትን ቃል መፈጸም እና ታማኝነት ስለሚጫወቱት ወሳኝ ሚና ያብራሩት ፕሬዝደንቱ "መሪዎች ምሳሌ ሆነው መምራት ካልቻሉ ተቀባይነት አይኖራቸውም።" ሲሉ አሳስበዋል።
ታላላቅ ሃሳቦች አለማችንን እንዴት እንደቀየሩ ተግባራዊ ምሳሌዎችን በማንሳት የሃሳብን ሃያልነት በሰፊው አስረድተዋል።
በርካታ በጎ እንዲሁም መጥፎ ክስተቶችን ያስከተሉ ታላላቅ እሳቤዎችን አንስተዋል። በንግግራቸውም “ሃሳብ የማይሻገረው ወሰን እና ድንበር የለም!” ሲሉ ተደምጠዋል።
“ሃሳብ የግለሰቦችን ህይወት ከመቀየር ህብረተሰብን እስከማሻገር የሚደርስ ሃይል አለው።” ብለዋል።
ስልጠናው የአመራር ልማት እና የአመራር ልማት የሚሰጡ ተቋማት ላይ ትኩረት ባደረጉ ርዕሶች ነገም ቀጥሎ የሚካሄድ ይሆናል።