African Leadership Excellence Academy pinned «የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ #የኮሙኒኬሽን_ኃይል_እና_የአመራር_ጥበብ በሚል ርዕስ ለከፍተኛ አመራሮች የሰጡትን #ክፍል_2 ስልጠና በአካዳሚው የዩቱዩብ ቻናል ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtu.be/hv3Q0klclPg»
"ለውጥን የምንመራበትን መንገድ መወሰን እንጂ ከለውጥ መሸሽ አንችልም" የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ
የአፍሌክስ አስተዳደር እና ሰራተኞች የአመራር ልማት ስልጠና መውሰድ ጀመሩ
ሱሉልታ፣ መጋቢት 9/2017 (አፍሌክስ) – የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ለተቋሙ አመራር እና ሰራተኞች 'ለውጥ እና የሀገራት ዕጣ ፈንታ' በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጥተዋል።
ዛሬ ጅማሮውን ያደረገው ለ6 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ስልጠና የመጀመሪያ ቀን ውሎ የአላማ ግልጽነት፣ የአመራር ልማት አስፈላጊነት፣ ለውጥ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በአካዳሚው ፕሬዝደንት ሰፊ ማብራርያ ተሰጥቷል።
አቶ ዛዲግ “የአላማ ግልጽነት በተቋም ውስጥ ከፉክክር ይልቅ ትብብር እንዲመጣ ያስችላል” ሲሉ ተናግረው ስለመሪነት እና የሃገራት እጣ ፈንታ ሲያስረዱ “የሃገራት ስኬትና ውድቀት ምክንያት ምንድነው ቢባል? ከምንም በላይ አመራር ነው” ብለዋል።
የትምህርት ስርዐታችን ሁሉንም ሰው ለመሪነት የሚያበቃ ሁሉን አቀፍ ባህርይ ስለሚጎድለው እንደአፍሌክስ ያሉ የአመራር ልማት ተቁማት አስፈላጊነት በእጅጉ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል።
በማብራርያቸው የለውጥን አይቀሬነት ሲናገሩ "ለውጥን የምንመራበትን መንገድ መወሰን እንጂ ከለውጥ መሸሽ አንችልም" በማለት ገልጸዋል።
ስልጠናው አካዳሚው እያካሄደ ያለውን የለውጥ ጉዞ በብቃት ለመምራት የሚያስችሉ ክህሎቶችን ለሰራተኞቹ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ቀጥሎ ሲካሄድ በነገው እለት አቶ ዛዲግ በለውጥ አመራር እና ተያያዥ ርዕሶች ላይ አሳታፊ ስልጠና ይሰጣሉ
የአፍሌክስ አስተዳደር እና ሰራተኞች የአመራር ልማት ስልጠና መውሰድ ጀመሩ
ሱሉልታ፣ መጋቢት 9/2017 (አፍሌክስ) – የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ለተቋሙ አመራር እና ሰራተኞች 'ለውጥ እና የሀገራት ዕጣ ፈንታ' በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጥተዋል።
ዛሬ ጅማሮውን ያደረገው ለ6 ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ስልጠና የመጀመሪያ ቀን ውሎ የአላማ ግልጽነት፣ የአመራር ልማት አስፈላጊነት፣ ለውጥ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በአካዳሚው ፕሬዝደንት ሰፊ ማብራርያ ተሰጥቷል።
አቶ ዛዲግ “የአላማ ግልጽነት በተቋም ውስጥ ከፉክክር ይልቅ ትብብር እንዲመጣ ያስችላል” ሲሉ ተናግረው ስለመሪነት እና የሃገራት እጣ ፈንታ ሲያስረዱ “የሃገራት ስኬትና ውድቀት ምክንያት ምንድነው ቢባል? ከምንም በላይ አመራር ነው” ብለዋል።
የትምህርት ስርዐታችን ሁሉንም ሰው ለመሪነት የሚያበቃ ሁሉን አቀፍ ባህርይ ስለሚጎድለው እንደአፍሌክስ ያሉ የአመራር ልማት ተቁማት አስፈላጊነት በእጅጉ የላቀ መሆኑንም አንስተዋል።
በማብራርያቸው የለውጥን አይቀሬነት ሲናገሩ "ለውጥን የምንመራበትን መንገድ መወሰን እንጂ ከለውጥ መሸሽ አንችልም" በማለት ገልጸዋል።
ስልጠናው አካዳሚው እያካሄደ ያለውን የለውጥ ጉዞ በብቃት ለመምራት የሚያስችሉ ክህሎቶችን ለሰራተኞቹ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ቀጥሎ ሲካሄድ በነገው እለት አቶ ዛዲግ በለውጥ አመራር እና ተያያዥ ርዕሶች ላይ አሳታፊ ስልጠና ይሰጣሉ