የሱማሌ ክልላዊ መንግሰት የማኔጅመንት እና ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሌጅ በ አራት የስልጠናና የትምህርት መስክ ማለትም በ አመራር (Leadership) ፤ ደቨሎፕመንት ኮሚኒኬሽን (Development Communication)፤ በሰላምና ግጭት ማኔጅመንት (Peace and Conflict Management) ፤ እና በፕሮጀክት ማኔጅመንት (Project Management) ለክልሉ አመራሮች በማስተርስ ዲግሪ ደረጃ ትምህርት እና የአጫጭር ጊዜ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ኮሌጁን ወደ ዩንቨርሲቲ ደረጃ ለማሳደግ ከከፍተኛ ትምህርት አግባብነት እና ጥራት ኤጀንሲ(HERQA) ጋር አብሮ እየሰራ እንደሆነ ታውቋል፡፡
የማኔጅመንት እና ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሌጁ ዲን አመራር አካላት ለጉዳዩ መሳካት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ቀን ከሌት እየተጉ ይገኛሉ፡፡
ለዚህ ውጥን ስኬት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እያደረገ ያለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ የክልሉ መንግሰት የማኔጅመንት እና ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሌጅ ትልቅ አክብሮት አለው፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ኮሌጁን ወደ ዩንቨርሲቲ ደረጃ ለማሳደግ ከከፍተኛ ትምህርት አግባብነት እና ጥራት ኤጀንሲ(HERQA) ጋር አብሮ እየሰራ እንደሆነ ታውቋል፡፡
የማኔጅመንት እና ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሌጁ ዲን አመራር አካላት ለጉዳዩ መሳካት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ቀን ከሌት እየተጉ ይገኛሉ፡፡
ለዚህ ውጥን ስኬት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እያደረገ ያለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ የክልሉ መንግሰት የማኔጅመንት እና ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሌጅ ትልቅ አክብሮት አለው፡፡
The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 5 months. If it remains inactive in the next 9 days, that account will self-destruct and this channel may no longer have an owner.
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በአመራርነት ሲያገለግሉ የነበሩት የአካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ም/ፕሬዝዳንት አቶ ፀጋዬ ማሞ እና የጥናትና ምርምር ዘርፍ ም/ፕሬዝዳንት አቶ ደምሴ ሽቶ እንዲሁም በአካዳሚው በመምህርነት ሲያገለግሉ ለነበሩት መምህራን የሽኝትና የምስጋና መርሃ ግብር እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የስነልቦና ፣ የማህበራዊና የአዕምሮ ጤና ድጋፍ አገልግሎቶችን ውጤታማነት ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና መሰጠት ተጀመረ
***********************
የካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ፡ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የስነልቦና ፣ የማህበራዊና የአዕምሮ ጤና ድጋፍ አገልግሎቶችን ውጤታማነት ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ መሰጠት ተጀመረ፡፡
ስልጠናውን በይፋ የከፈቱት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርእሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደገለጹት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች ተደራሽ የሚያደረግ የማህበራዊ፣የስነልበናና የአእምሮ ጤና ስልጠና ዘረፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው ገልጸው የአመራር ልህቀት አካዳሚውም ሰልጠናው በተገቢው መንገድ እንዲከናወን ድጋፍን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው እንደገለጹት በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ምክንያት የተከሰቱት ችግሮች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ካሰድሩት ተጽእኖ በተጨማሪ በዜጎች ላይ እጅግ የከፋ ማህበራዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት እንዳደረሰ በተለይም በአሸበሪው ህውሃት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉና ጾታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴት የህብረተሰብ ክፍሎች ከደረሰባቸው አሰቃቂ ጉዳት ተላቀው ወደ ቀደመ ህይወታቸው ለመመለስ የሁሉንም አካላት ርብርቦሽ እየጠበቁ አንደሆ ገልጸው ዛሬ በይፋ የተጀመረው በስነልቦና፣ በማህበራዊና በአዕምሮ ጤና፣ ድጋፍ ላይ ያተኮረ የአሰልጣኞች ስልጠና ይህንን ግዙፍ ሀገራዊ ችግር ለመቅረፍ የራሱን አበርክቶ ይወጣል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
***********************
የካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ፡ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የስነልቦና ፣ የማህበራዊና የአዕምሮ ጤና ድጋፍ አገልግሎቶችን ውጤታማነት ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ መሰጠት ተጀመረ፡፡
ስልጠናውን በይፋ የከፈቱት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርእሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደገለጹት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች ተደራሽ የሚያደረግ የማህበራዊ፣የስነልበናና የአእምሮ ጤና ስልጠና ዘረፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው ገልጸው የአመራር ልህቀት አካዳሚውም ሰልጠናው በተገቢው መንገድ እንዲከናወን ድጋፍን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው እንደገለጹት በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ምክንያት የተከሰቱት ችግሮች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ካሰድሩት ተጽእኖ በተጨማሪ በዜጎች ላይ እጅግ የከፋ ማህበራዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት እንዳደረሰ በተለይም በአሸበሪው ህውሃት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉና ጾታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴት የህብረተሰብ ክፍሎች ከደረሰባቸው አሰቃቂ ጉዳት ተላቀው ወደ ቀደመ ህይወታቸው ለመመለስ የሁሉንም አካላት ርብርቦሽ እየጠበቁ አንደሆ ገልጸው ዛሬ በይፋ የተጀመረው በስነልቦና፣ በማህበራዊና በአዕምሮ ጤና፣ ድጋፍ ላይ ያተኮረ የአሰልጣኞች ስልጠና ይህንን ግዙፍ ሀገራዊ ችግር ለመቅረፍ የራሱን አበርክቶ ይወጣል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የማስተርስ ዲግሪ ለመማር የመግቢያ ፈተና ተፈትናችሁ በ2014 ዓ.ም ትምህርት ለመጀመር በዝግጅት ላይ የነበራችሁ ተማሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ተዛውራችሁ በመደበኛ የትምህርት መርሀ ግብር እንድትቀጥሉ በተወሰነው መሰረት ዩኒቨርስቲው የምዝገባውን ቀን እና ተመዝጋቢዎች ማሟላት ያለባቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ ለአካዳሚው በግልባጭ አሳውቋል፡፡
በመሆኑም በተጠቀሰው ቀን በዩኒቨርስቲው በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳወቅን ከዩኒቨርስቲው የተላከውን ደብዳቤ ከዚህ መልዕክት ጋር አያይዘንላችኋል፡፡
በመሆኑም በተጠቀሰው ቀን በዩኒቨርስቲው በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳወቅን ከዩኒቨርስቲው የተላከውን ደብዳቤ ከዚህ መልዕክት ጋር አያይዘንላችኋል፡፡
አካዳሚያችንን በሚመለከት በሚከተሉት አድራሻዎቻችን ልታገኙን ትችላላችሁ
Mail:-info@aflexacademy.gov.et
Web:-www.aflexacademy.gov.et
Facebook:-African Leadership Excellence Academy
Telegram:- https://t.me/afleexac
Phone:-+2516674837/+2518932655
Po.Box:-7254
Mail:-info@aflexacademy.gov.et
Web:-www.aflexacademy.gov.et
Facebook:-African Leadership Excellence Academy
Telegram:- https://t.me/afleexac
Phone:-+2516674837/+2518932655
Po.Box:-7254
Telegram
African Leadership Excellence Academy
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
በንድፈ-ኃ
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ስልጠና እየሰጠ ነው
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ኃላፊዎች ስልጠና እየሰጠ ሲሆን ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) አካዳሚው የተቋቋመው ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁሉም ደረጃ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እና የሀገሪቱን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም፣ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የአመራር አካላት አቅምን ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው አያይዘውም አካዳሚው በንድፈ ሀሳብ የተደገፈ ተግባር ተኮር የአመራር ስልጠና እንደሚሰጥ ገልፀው ስልጠናው The Art of finishing well በተለይም the proof of Integrity and The mark of Excellence በሚልና በሌሎች ርዕሶች ላይ በተለያዩ አሰልጣኞች እንደሚሰጥ አስታውቀዋል፡፡
የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋም የሚመሰረተው ጠንካራና ተባብረው በሚሰሩ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች መሆኑን አስታውቀው ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ኃላፊዎች ስልጠና እየሰጠ ሲሆን ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) አካዳሚው የተቋቋመው ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁሉም ደረጃ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እና የሀገሪቱን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም፣ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የአመራር አካላት አቅምን ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው አያይዘውም አካዳሚው በንድፈ ሀሳብ የተደገፈ ተግባር ተኮር የአመራር ስልጠና እንደሚሰጥ ገልፀው ስልጠናው The Art of finishing well በተለይም the proof of Integrity and The mark of Excellence በሚልና በሌሎች ርዕሶች ላይ በተለያዩ አሰልጣኞች እንደሚሰጥ አስታውቀዋል፡፡
የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋም የሚመሰረተው ጠንካራና ተባብረው በሚሰሩ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች መሆኑን አስታውቀው ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) በወሎ ዩኒቨርሲቲ ኮምበልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ግቢ በመምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና እና ውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ቁልፍ ንግግር አድርገዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በቁልፍ ንግግራቸውም እንደገለፁት በጦርነቱ የዩንቨርስቲው የማስተማርያ ግብዓቶችና መሰረተ ልማቶች በመዘረፋቸውና በመውደማቸው ከልብ ማዘናቸውን ተናግረው የሰው ልጅ ትልቁ ሀብት የሆነው ህሊና ባለመዘረፉ ዳግም ወደስራ ለመመለስ የሚገድብ ነገር እንደሌለ ግንዛቤ በመፍጠር የዩኒቨርስቲውን ማህበረሰብ የስራ መንፈስ አነሳስተዋል፡፡
ምህረት ደበበ (ዶ/ር) የህሊና መኖርንና አለመዘረፍ ጠቀሜታ ሲተነትኑ የሰው ልጅ ትልቁ ሀብትና የሁሉ ነገር ምንጭ ህሊና ነው፡፡ ገንዘብ ማስፈጸሚያ እንጂ ከህሊና በበለጠ መልኩ ዋጋ የለውም፡፡ ይህ ሀብት አልተዘረፈም፡፡ የዚህ ሀብት ዋና ሞተር የሆነው አእምሯችን አልተዘረፈም፡፡ ማሰብ እንችላለን ሊቆስል ይችል ይሆናል ሆኖም ግን ይታከማል፡፡ ገንዘብም ይተካል የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ለህሊናችን ዋጋ በመስጠትና በቀረው ሀብት ላይ በመመስረት ወደነበርንበት ብቻ ሳይሆን ወደተሻለ አሰራር ገብተን ዩኒቨርሲተያችንን መለወጥ እንችላለን የሚል እምነት ሊኖረን ይገባል በማለት የሰራተኛውን ሞራል ገንብተዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በዚህም ሂደት አራት መሰረታዊ መዋቅሮች አንዳሉ በማሰገንዘብ አነሱም የመሰረተ ልማት መዋቅር፣ የህግ መዋቅር፣ የልቦና መዋቅርና የህሊና መዋቅር ሲሆኑ የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ መዋቅሮች ከሰው ውጭ ያሉ ሊወድሙ ወይም ሊዘረፉ የሚችሉ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሁለቱ ግን በሰው ውስጥ ያሉ የማይዘረፉ ለሰው ልጅ ትልቁ ሀብት እንደሆኑ አጽንኦት በመስጠት በዩኒቨርስቲው ውስጥ ታላቅ የስራ መነሳሳት ፈጥረዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በቁልፍ ንግግራቸውም እንደገለፁት በጦርነቱ የዩንቨርስቲው የማስተማርያ ግብዓቶችና መሰረተ ልማቶች በመዘረፋቸውና በመውደማቸው ከልብ ማዘናቸውን ተናግረው የሰው ልጅ ትልቁ ሀብት የሆነው ህሊና ባለመዘረፉ ዳግም ወደስራ ለመመለስ የሚገድብ ነገር እንደሌለ ግንዛቤ በመፍጠር የዩኒቨርስቲውን ማህበረሰብ የስራ መንፈስ አነሳስተዋል፡፡
ምህረት ደበበ (ዶ/ር) የህሊና መኖርንና አለመዘረፍ ጠቀሜታ ሲተነትኑ የሰው ልጅ ትልቁ ሀብትና የሁሉ ነገር ምንጭ ህሊና ነው፡፡ ገንዘብ ማስፈጸሚያ እንጂ ከህሊና በበለጠ መልኩ ዋጋ የለውም፡፡ ይህ ሀብት አልተዘረፈም፡፡ የዚህ ሀብት ዋና ሞተር የሆነው አእምሯችን አልተዘረፈም፡፡ ማሰብ እንችላለን ሊቆስል ይችል ይሆናል ሆኖም ግን ይታከማል፡፡ ገንዘብም ይተካል የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ለህሊናችን ዋጋ በመስጠትና በቀረው ሀብት ላይ በመመስረት ወደነበርንበት ብቻ ሳይሆን ወደተሻለ አሰራር ገብተን ዩኒቨርሲተያችንን መለወጥ እንችላለን የሚል እምነት ሊኖረን ይገባል በማለት የሰራተኛውን ሞራል ገንብተዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው በዚህም ሂደት አራት መሰረታዊ መዋቅሮች አንዳሉ በማሰገንዘብ አነሱም የመሰረተ ልማት መዋቅር፣ የህግ መዋቅር፣ የልቦና መዋቅርና የህሊና መዋቅር ሲሆኑ የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ መዋቅሮች ከሰው ውጭ ያሉ ሊወድሙ ወይም ሊዘረፉ የሚችሉ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሁለቱ ግን በሰው ውስጥ ያሉ የማይዘረፉ ለሰው ልጅ ትልቁ ሀብት እንደሆኑ አጽንኦት በመስጠት በዩኒቨርስቲው ውስጥ ታላቅ የስራ መነሳሳት ፈጥረዋል፡፡