African Leadership Excellence Academy
2.3K subscribers
2.48K photos
96 videos
6 files
116 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
በከፍተኛ ሹመት ወደ ሌላ የስራ ኃላፊነት ለተዘዋወሩ የቀድሞ የአካዳሚው ፕሬዝዳንትና ም/ፕሬዝዳንት የሽኝትና የምስጋና መርሃ ግብር ተካዷል፡፡
በሽኝትና በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ የቀድሞ የአካዳሚው አመራሮች ለሰሩት ስራ ምስጋና እንደሚገባቸው በመግለጽ በሄዱበት መልካም የስራ ጊዜ አንዲሁንላቸው ተመኝተዋል፡፡
የሽኝትና የምስጋና መርሃ ግብሩ የአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በአካዳሚው የሱሉልታ ማሰልጠኛ ማዕከል ተደርጓል፡፡
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በረዳት ፕሮፌሰር ማዕረግ ተመራማሪ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ደሳለኝ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል፡፡
እንኳን ደስ አለዎ!! መልካም የስራ ዘመን እንመኛለን!!
በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት ተደረገ

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ ከመላው የአካዳሚው ሰራተኞች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ እንደተናገሩት የውይይቱ አላማ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የጋራ ግንዛቤ ለመያዝና ሰራተኛው የሚጠበቅበትን ማድረግ እንዲችል ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ምህረት የሀገራችን ሁኔታ ከህልውና ጋርና ኢትዮጵያ ትቀጥላለች ወይም አትቀጥልም የሚል ሁኔታ ላይ የደረሰና ሀገሪቱ በምዕራባውያን ከባድ ጫና እየደረሰባት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ርዕሰ አካዳሚው የሰብአዊ መብት ጉዳይ ሳይሆን ሀገሪቱን እንደ ሶሪያ፣አፍጋኒስታንና ሊቢያ ለማፈራረስ የታሰበ አጀንዳ በመሆኑ ህዝባዊ ድጋፍ ማድረግ አማራጭ የሌለው መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

የጥናትና ምርምር ምክትል ርዕሰ አካዳሚ የሆኑት አቶ ደምሴ ሽቶ በበኩላቸው የሀገሪቱን አንድነት የሚፈታተንና ህዝባችንን በተለያየ መንገድ የሚረብሸ ነገር ሲከናወን ወቅታዊ ወይይቶች ማድረግና ግንዛቤ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አቶ ደምሴ ሀገር የማፍረስ እንቅስቃሴንና ውዥንብሮችን መከላከል፣ የሚኖርበትን አካባቢ መጠበቅና ሰላምን ማስከበር እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊቱን በተለያየ መንገድ በመደገፍ የሚጠበቅበትን ሃላፊነት መወጣት የሰራተኛው ድርሻ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

የአካዳሚው ሰራተኞችና አመራሮችም በበኩላቸው ወቅታዊ ውይይቱ አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት የአንድ ወር ደመወዛቸውን በአንድ አመት ለመክፈል ተስማምተው በተጨማሪም ባላቸው አቅም በዕውቀት፣ በቁሳቁስ እንዲሁም በደም ልገሳ እንደሚሳተፉም ቃል ገብተዋል፡

በመጨረሻም በውይይት መድረኩ የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ የመስሪያ ቤቱ መዋቅር በባለሙያዎች ከ6-8 ሳምንታት ውስጥ ተሰርቶ ለሰራተኛው እንደሚቀርብም አስታውቀዋል፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጫናውን አሸንፎ መውጣት ለአፍሪካም ማሸነፍ ነው - ዶ/ር ምህረት ደበበ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ አሁን የተከፈተባትን የውጭ ጫና አሸንፎ መውጣት ለአፍሪካም ጭምር ማሸነፍ እንደሆነ መገንዘብ እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ ገለጹ፡፡
ዶክተር ምህረት እንደገለጹት ÷ ኢትዮጵያ አሁን የተከፈተባትን የውጭ ጫና አሸንፎ መውጣት ለአፍሪካም ጭምር ማሸነፍ እንደሆነ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡
በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያውያን ትልቅ እና ታሪካዊ ጊዜ ላይ ነን ፤ አፍሪካውያን ከጎናችን እንደሚቆሙ እያሳዩን ነው ፤ ስለሆነም ጦርነቱን ከማሸነፍ ውጪ ሌላ ምርጫ የለንም ብለዋል፡፡
በታሪካችን ኢትዮጵያ ብቻዋን ነፃነቷን አስከብራ ሌሎችንም ወደ ነፃነት ስትመራ ይሄ ሁለተኛው የነፃነት ጥሪ መሆኑን ጠቁመው ÷ ይሄንን ጦርነት በማሸነፍ የአሁኑ ትውልድ ታሪክ መጻፍ እንዳለበትም ነው የገለጹት፡፡
ምዕራባውያን የአፍሪካን አገራት እንደ አገር ማየት እና ማክበር አይፈልጉም ያሉት ፕሬዚዳንቱ ÷ ኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ውስጥ ያልገባች በአጭር ጊዜ ውስጥም ቢሆን በጣልያን ወረራ አባቶቻችን እጅ ሳይሰጡ የኢትዮጵያን ነፃነት እንዳስጠበቁ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያን ትልቅ እናደርጋታለን ብለው ዜጎቿ ሲነሱ ምዕራባውያን ደግሞ እንዳንሆን በአሁኑ ወቅት ተነስተውብናል ብለዋል፡፡
ይህንን እንዳይሳካ ለማድረግ እንደ ሁነኛ መሣሪያ ሆኖ ያገኙት በአሁኑ ጊዜ በአገሪቱ እየተካሄደ ያለውን ጦርነት እንደሆነ ጠቅሰው ÷ የአሸባሪውን ህወሓት ኃይል ለዚህ መጠቀሚያ ስለማድረጋቸውም ነው ያነሱት፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ - https://www.fanabc.com/የኢትዮጵያ-የውጭ-ጫናውን-አሸንፎ-መውጣት/
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረገ፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለሃገር መከላከያ ሰራዊት እና በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብታቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ድጋፉን ለብሔራዊ አደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን ያስረከቡት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ ይህን አስቸጋሪ ወቅት ማለፍ የሚቻለው በመደጋገፍ እንደሆነ ገልፀው ሁሉም ነገር የሚኖረው ሃገርና ህዝብ ሲኖር ነው ብለዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የብሔራዊ አደጋ ስጋትና አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ አካዳሚው ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
"ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ስትካድ የመጀመሪያዋ አይደለም፡፡" ክህደትን ማሸነፊያው ብቸኛ መንገድ ደግሞ አንድነትንና ህብረትን ማጠናከሩ ነው ብለዋል ምህረት ደበበ (ዶ/ር) የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ፡፡
በምዕራባውያንና በአሜሪካ የሚደረግብንን ጫና ልንሻገረው የምንችለው ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጉላት በመሆኑ ሁላችንም ከመቼውም በበለጠ መንገድ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንዳለብን አስታውሰው የአገር መሪ እስከ ጦር ግንባር ድረስ እንዲዘምትና እንዲመራ የሚያስገድድ ሁኔታ ውስጥ መገኘታችንን ሁሉም ሰው ተገንዝቦ ለመከላከያ ሰራዊቱና ለተፈናቀሉ ዜጎች በአቅሙ ድጋፍና እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባ ርዕሰ አካዳሚው ተናግረዋል፡፡
የጦርነቱ ድል በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በዲፕሎማሲ ድል መታገዝ እንደሚገባው ተገለፀ
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጦር ግንባር መገኘታቸው ከፍተኛ የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም የፈጠረ መሆኑን ያነሱት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ መምህር ያሬድ አስራት (ዶ/ር) እየተገኘ ያለው ድል በፖለቲካና በዲፕሎማሲው እንዲሁም በሁሉም መስክ መታገዝ እንደሚገባው ገልፀዋል፡፡
እየተገኘ ያለው ድል የሚደነቅና የሚያኮራ እንደሆነ ያነሱት ያሬድ አስራት (ዶ/ር) “አንዳንዴ ጦርነትን ማሸነፍ በራሱ በቂ አይደለም ከዚህ በፊት መቀሌ በ3 ሳምንት ውስጥ መግባት ችለናል ነገር ግን መቀሌ መግባት ግብ አይደለም፤ ስለዚህ ከጦርነቱ ማሸነፍ ባሻገር በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚውና በዲፕሎማሲው መስክ ማሸነፍ ይገባል” ብለዋል፡፡
የተፈጠረው ሃገራዊ አንድነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከዚህ በፊት የነበሩ መከፋፈሎች ተመልሰው እንዳይመጡ ሁሉንም በእኩልነት ሊያሰባሰቡ የሚችሉ የጋራ ራዕዮችን እና የጋራ ትርክቶችን መፍጠር እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
ጦርነቱን እንደምናሸንፍ እርግጠኛ ነኝ ያሉት ያሬድ አስራት (ዶ/ር) አላማችን ሰፊ መሆን እንዳለበት እና የውጭውን ጫና ለመቀነስ ጦርነቱን በአጭር ጊዜ መቋጨት እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በፀረ ፆታዊ ጥቃት፣ በኤች አይቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር እና በስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ርዕሶች ላይ ያተኮረ ስልጠና ለአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡