African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.52K photos
96 videos
6 files
119 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
The morning session was nothing short of extraordinary! It kicked off with powerful speeches and heartfelt messages from our esteemed VIP guests, whose words of wisdom and encouragement resonated deeply with everyone in the room. Their insights on peacebuilding and climate justice sparked a wave of inspiration, setting the tone for a day filled with thoughtful dialogue and meaningful connections.

#NLC2024 | Lead with Purpose, Serve with Integrity.
#NLC2024 #LeadershipForChange #YouthEmpowerment #InspiredLeadership #EthiopiaRising #BuildingTomorrow #EmpoweredYouth #FutureLeaders #ConnectingMinds #CollaborationForChange #Networking #BeTheChange #InspiringGenerations #LeadersOfTomorrow #EthiopianLeadership #EthiopiaRising #BoldLeaders #VoicesForChange
👍8
"የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ በቅብብሎሽ የሚያሳኩ ተተኪ አመራሮችን መፍጠር ይገባል"-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፤ ህዳር 26/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ በቅብብሎሽ የሚያሳኩ ተተኪ አመራሮችን መፍጠር ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ነጸብራቅ የመሪነት ኮንፍረንስ"ን በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አስጀምረዋል።
👍8
በመክፈቻ ንግግራቸውም ኢትዮጵያ ታላላቅ ድሎችን ያስመዘገቡ፣ የስልጣኔ ከፍታን የተቀዳጁ መሪዎች ሀገር ብትሆንም ያንን ማስቀጠል ባለመቻሉ ወደኋላ መቅረቷን ገልጸዋል።
በረዥሙ የሀገራችን ታሪክ ታላላቅ መሪዎች እንደነበሩ በማውሳት በአንድ ወቅት በርተው የጠፉና ሊደገሙ የማይችሉ አመራሮች ሆነዋል ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ገናናነት የሚጠቀስባቸው ስኬቶች ከዘመን ዘመን መሸጋገርና መሳካት ያልቻሉት የአመራር ግንባታን እንደሀገር ባለማስቀጠላችን ነው ብለዋል።

አሁን ላይ ኢትዮጵያ የምትጠቀስባቸውን ጉድለቶች በመሙላት ወደ ከፍታ የማሻገር ጉዞ መጀመሩን ገልጸው የተተኪ አመራር ልማትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል።

ተተኪ ወጣት አመራሮችና ነባሩ አመራር የሚመክሩባቸውና ልምድ የሚለዋወጡባቸው መድረኮች ሲፈጠሩ በአመራር ትውልዶች መካከል መናበብ በመፍጠር ሀገራዊ ትልሞችን ለማሳካት ያስችላል ብለዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ አመራሮች የምትፈጥርበት እንዲሁም በአመራሮች መካከል የትውልዳዊ ቅብብሎሸ ሥርዓት የምትገነባበት አሠራርና ተቋም እንደሚያስፈልጋት ተናግረዋል።

ይህ የተተኪም ሆነ የነባሩ አመራር ቁልፍ ተልዕኮ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
የሀገር ቀጣይነት ያለው ዕድገትም ሆነ ውድቀት የሐሳብ ጥራት፣ የአመራር ብቃት እና ቁርጠኝነት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ጠቅሰው ችግሮችን ወደ ዕድል በመቀየር የሀገርን ዕድገት የሚያሳካ መሪ መሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ነፀብራቅ የመሪነት ኮንፍረንስ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የተሣለጠ የትውልዶች አመራር ቅብብሎሽ የሚቀጥልበትን መንገድ የሚያሳይ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የተጀመሩ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮችን በውጤታማነት በማስቀጠል የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ ለማሳካት በትጋትና በብቃት የሚሠራ ተከታታይ አመራር በየዘመኑ ሲኖር መሆኑንም አፅኖት ሰጥተዋል።
👍8
"የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ በቅብብሎሽ የሚያሳኩ ተተኪ አመራሮችን መፍጠር ይገባል"-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
👍8
"ተተኪ ወጣት አመራሮችና ነባሩ አመራር የሚመክሩባቸውና ልምድ የሚለዋወጡባቸው መድረኮች ሲፈጠሩ በአመራር ትውልዶች መካከል መናበብ በመፍጠር ሀገራዊ ትልሞችን ለማሳካት ያስችላል"ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
👍8
H.E. Dr. Ergoge Tesfaye (PhD), Minister of Women and Social Affairs, delivered a powerful message at the Netsebrak Leadership Conference, highlighting the vital leadership role young people play today. She emphasized that youth are not only the leaders of tomorrow, but also key change-makers in the present. By empowering them now, we’re building a more inclusive and prosperous future.

#NLC2024 | Lead with Purpose, Serve with Integrity.
#NLC2024 #LeadershipForChange #YouthEmpowerment #InspiredLeadership #EthiopiaRising #BuildingTomorrow #EmpoweredYouth #FutureLeaders #ConnectingMinds #CollaborationForChange #Networking #BeTheChange #InspiringGenerations #LeadersOfTomorrow #EthiopianLeadership #EthiopiaRising #BoldLeaders #VoicesForChange
👍9
በነጸብራቅ የመሪነት ኮንፈረንስ የመክፈቻ ስነ ስርዐት ላይ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ
የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የእለቱ የክብር እንግዳ
ክቡራን ሚኒስትሮች
ክቡራን ሚኒስትር ዴኤታዎች
ክቡራን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች
ክቡራን የሀይማኖት አባቶች
ክቡራን የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች
ክቡራትና ክቡራን

በቅድሚያ ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትራችን እንኳን ወደ አፍሌክስ ግቢ በደህና መጡ እያልኩኝ ጊዜዎ በእጅጉ የተጣበበ ቢሆንም ተቋሙ ያቀረበልዎትን የክብር እንግድነት ጥሪን ከተቀበሏቸው ሌሎች መሰል ጥሪዎች በላይ የቅድሚያ ቅድሚያ በመስጠት በመካከላችን በመገኘትዎ የተሰማኝን ልባዊ ደስታ እና ምስጋና በዚህ ኮንፈረንስ ታዳሚዎች፣ በተቋሙና በራሴ ስም እንዳቀርብ ይፈቀድልኝ፡፡ በተመሳሳይም ያቀረብንላችሁን የእንወያይ ጥሪን ተቀብላችሁ በመካከላችን ለተገኛችሁ የዚህ ኮንረንስ ተሳታፊዎች ሁሉ በተቋሙና በራሴ ስም ልባዊ ምስጋናዬን እያቀረብኩኝ በድጋሜ ወደ አፍሌክስ እንኳን በደህና መጣችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡
👍10