የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የ 2013/14 ዓ.ም የሁለተኛ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎችን የመመረቂያ ጽሁፎች ግምገማ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንትና ፈታኞች በተገኙበት መጀመሩን ከአካዳሚክ ጉዳዮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
በአዲሱ መንግስት ለተሾሙ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ነው
በአዲሱ መንግስት ለተሾሙ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ አመራሮች በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በዚህ ስልጠና መክፈቻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባደረጉት ገለጻ÷ አመራሩ በንፁህ እጅና በቅንነት ሀገሩን ማገልገል አለበት ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚረጋገጠው ኢትዮጵያ ያሏትን ሃብቶች በአግባቡ በማልማት፣ በትጋት በመስራትና በንፁህ እጅና በቅንነት መሆኑን ተናግረዋል።
አመራሮች ከስለጠናው በኋላም የዓላማ ጽናት በቡድን የመስራት መንፈስና በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር መለወጥ ይኖርባቸዋል ማለታቸውን ኢፕድ ዘግቧል።
በአዲሱ መንግስት ለተሾሙ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ አመራሮች በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በዚህ ስልጠና መክፈቻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባደረጉት ገለጻ÷ አመራሩ በንፁህ እጅና በቅንነት ሀገሩን ማገልገል አለበት ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚረጋገጠው ኢትዮጵያ ያሏትን ሃብቶች በአግባቡ በማልማት፣ በትጋት በመስራትና በንፁህ እጅና በቅንነት መሆኑን ተናግረዋል።
አመራሮች ከስለጠናው በኋላም የዓላማ ጽናት በቡድን የመስራት መንፈስና በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር መለወጥ ይኖርባቸዋል ማለታቸውን ኢፕድ ዘግቧል።
በአዲሱ መንግሥት የተካተቱ ሚኒስትሮች እና ሚኒስትር ዴኤታዎች በዚህ ሳምንት በሚኖራቸው የሥራ ማስጀመሪያ በሚሳተፉበት ወቅት፣ በአገልጋይ መሪነት ልብ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ። የዚህች ታላቅ ሀገር ዜጎች ከዚህ ያነሰ አገልግሎት አይገባቸውም።
በየአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የተናገሩት
ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር
በየአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የተናገሩት
ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር
በየአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ስልጠና እየወሰዱ ካሉ ሚኒስትሮችና ሚኒስትር ዲኤታዎች መካከል ስለ አካዳሚው አገልግሎት አስተያየት ከሰጡን መካከል የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትሩ አብርሐም በላይ (ዶ/ር) አንዱ ናቸው ፡፡
ይህን ብለውናል፡- በሌሎች አገራት ያለውን የአመራር አቅም መገንቢያ የሚስተካከል ተቋም በዚህ ግቢ ውስጥ አይቻለሁ፡፡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ ቢሰራ ጥሩ ነው የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡ በተረፈ ጥራት ያለው አካዳሚ መኖሩን አይቻለሁ፡፡
አብርሐም በላይ (ዶ/ር)
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር
ይህን ብለውናል፡- በሌሎች አገራት ያለውን የአመራር አቅም መገንቢያ የሚስተካከል ተቋም በዚህ ግቢ ውስጥ አይቻለሁ፡፡ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ ቢሰራ ጥሩ ነው የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡ በተረፈ ጥራት ያለው አካዳሚ መኖሩን አይቻለሁ፡፡
አብርሐም በላይ (ዶ/ር)
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር
በየአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ስልጠና እየወሰዱ ካሉ በአዲሱ መንግሥት የተካተቱ ሚኒስትሮች፤ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የመንግስት ተሹዋሚዎች ውስጥ ስለ አካዳሚው አገልግሎት አስተያየት ከሰጡን መካከል የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍስሃ ይታገሱ ይገኙበታል፡፡
ዋና ስራ አስፈፃሚው ይህን ብለውናል፡- የአካዳሚው አገልግሎት አሰጣጥ በጣም ጥሩ ነው፡፡ የህንፃው ጥራት፤ የመኝታ ክፍሎቹ፤ መወያያ ክፍሎቹና አዳራሹ በጣም ጥሩዎች ናቸው፡፡ አካዳሚው ዓለም አቀፍ ደረጃን ባሟላ መልኩ የተገነባ ነው፡፡ በሀገራችን ታሪክም የመጀመሪያው የማሰልጠኛ ማዕከል ሳይሆን አይቀርም፡፡ ሀገራችን ውስጥ ባልተለመደ መልኩ ስልጠናውን እዚሁ ወስዶ እዚሁ የመኝታ አገልግሎት አግኝቶ አቅምን መገንባት ጥሩ ነው፡፡ በተሟላ የስልጠና አገልግሎት ውስጥ ጥሩ የሚባል የቡድን መንፈስ ይፈጠራል፡፡ መቀራረብ እንዲኖር ያስችላል፡፡
አቶ ፍስሃ ይታገሱ
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ
ዋና ስራ አስፈፃሚው ይህን ብለውናል፡- የአካዳሚው አገልግሎት አሰጣጥ በጣም ጥሩ ነው፡፡ የህንፃው ጥራት፤ የመኝታ ክፍሎቹ፤ መወያያ ክፍሎቹና አዳራሹ በጣም ጥሩዎች ናቸው፡፡ አካዳሚው ዓለም አቀፍ ደረጃን ባሟላ መልኩ የተገነባ ነው፡፡ በሀገራችን ታሪክም የመጀመሪያው የማሰልጠኛ ማዕከል ሳይሆን አይቀርም፡፡ ሀገራችን ውስጥ ባልተለመደ መልኩ ስልጠናውን እዚሁ ወስዶ እዚሁ የመኝታ አገልግሎት አግኝቶ አቅምን መገንባት ጥሩ ነው፡፡ በተሟላ የስልጠና አገልግሎት ውስጥ ጥሩ የሚባል የቡድን መንፈስ ይፈጠራል፡፡ መቀራረብ እንዲኖር ያስችላል፡፡
አቶ ፍስሃ ይታገሱ
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ
በየአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ስልጠና እየወሰዱ ካሉ በአዲሱ መንግሥት የተካተቱ ሚኒስትሮች፤ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የመንግስት ተሹዋሚዎች ውስጥ ስለ አካዳሚው አገልግሎት አስተያየት ከሰጡን መካከል በሚኒስትር ማዕረግ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችና የህዳሴ ግድብ ዋና ተደራዳሪና አማካሪ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) ኢንጂነር ይገኙበታል፡፡
ዶክተሩ ይህን ብለውናል፡- በአካዳሚው እያገኘነው ያለው አገልግሎት እጅግ በጣም ዘመናዊና ባደጉ አገራት ውስጥ ያሉትን አይነት ነው፡፡ የአየር ሁኔታውም ለስልጠና ምቹ የሆነ ነው፡፡ በተለይም የስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ተግባራት ቢከናወኑ የተሟላ ይሆናል፡፡ የግቢውን ይዘትም በተወሰነ መልኩ በማሻሻል እጅግ ውብ ማድረግ ይቻላል፡፡ ከግቢው ውጭ ባሉ ቦታዎች ላይም ትኩረት ተደርጎ በደንብ የማስዋብ ስራ ቢሰራ አገልግሎቱን ውብ ያደርገዋል፡፡
ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) ኢንጂነር
በሚኒስትር ማዕረግ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችና የህዳሴ ግድብ ዋና ተደራዳሪና አማካሪ
ዶክተሩ ይህን ብለውናል፡- በአካዳሚው እያገኘነው ያለው አገልግሎት እጅግ በጣም ዘመናዊና ባደጉ አገራት ውስጥ ያሉትን አይነት ነው፡፡ የአየር ሁኔታውም ለስልጠና ምቹ የሆነ ነው፡፡ በተለይም የስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ተግባራት ቢከናወኑ የተሟላ ይሆናል፡፡ የግቢውን ይዘትም በተወሰነ መልኩ በማሻሻል እጅግ ውብ ማድረግ ይቻላል፡፡ ከግቢው ውጭ ባሉ ቦታዎች ላይም ትኩረት ተደርጎ በደንብ የማስዋብ ስራ ቢሰራ አገልግሎቱን ውብ ያደርገዋል፡፡
ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) ኢንጂነር
በሚኒስትር ማዕረግ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችና የህዳሴ ግድብ ዋና ተደራዳሪና አማካሪ
በየአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ስልጠና እየወሰዱ ካሉ በአዲሱ መንግሥት የተካተቱ ሚኒስትሮች፤ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የመንግስት ተሹዋሚዎች ውስጥ ስለ አካዳሚው አገልግሎት አስተያየት ከሰጡን መካከል ሰላማዊት ካሳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ይገኙበታል፡፡
ሚኒስትር ዲኤታዋ ይህን ብለውናል፡- በዚህ አካዳሚ አገልግሎት ሳገኝ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ በዚህ ተቋም ውስጥ ገብቼ በመሰልጠኔም እድለኛ እንደሆንኩ ነው የሚሰማኝ፡፡ የተቋሙ አገልግሎት ለማስተዋል ለማሰላሰል ሰፊ ዕድል ይሰጣል፡፡ ስልጠናውን ወደ ተግባር ለመመንዘርም የሚያስችል አገልግሎት ነው ያለው፡፡ የግቢው ስፋትም እየተንቀሳቀሱ ሀሳብን ለማንሸራሸር ትልቅ ጥቅም አለው፡፡ ካፍቴሪያው፤ አዳራሹ፤ የመወያያ ክፍሎቹ እና ጂሙን የማየት አጋጣሚ አግኝቻለሁ እጅግ ምቹዎች ናቸው፡፡ አፍሪካዊ መሪዎችን ለማፍራት የሚያስችል ደረጃ ላይ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡
ሰላማዊት ካሳ
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ
ሚኒስትር ዲኤታዋ ይህን ብለውናል፡- በዚህ አካዳሚ አገልግሎት ሳገኝ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ በዚህ ተቋም ውስጥ ገብቼ በመሰልጠኔም እድለኛ እንደሆንኩ ነው የሚሰማኝ፡፡ የተቋሙ አገልግሎት ለማስተዋል ለማሰላሰል ሰፊ ዕድል ይሰጣል፡፡ ስልጠናውን ወደ ተግባር ለመመንዘርም የሚያስችል አገልግሎት ነው ያለው፡፡ የግቢው ስፋትም እየተንቀሳቀሱ ሀሳብን ለማንሸራሸር ትልቅ ጥቅም አለው፡፡ ካፍቴሪያው፤ አዳራሹ፤ የመወያያ ክፍሎቹ እና ጂሙን የማየት አጋጣሚ አግኝቻለሁ እጅግ ምቹዎች ናቸው፡፡ አፍሪካዊ መሪዎችን ለማፍራት የሚያስችል ደረጃ ላይ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡
ሰላማዊት ካሳ
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ