የጋራ ትርክት ሀገራዊ ህልምን ዕውን ለማድረግ አጋዥ መሆኑን አቶ #ዛዲግ_አብርሐ ገለፁ
--------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 08 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የኢትዮጵያን ህልም ዕውን ለማድረግ የጋራ ትርክት መፍጠር አስፈላጊና አጋዥ ነው ሲሉ #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ገለፁ።
ክቡር አቶ ዛዲግ ይህን የገለፁት #"የትርክት_እመርታ_ከታሪካዊ_ስብራት_ወደ_ሀገራዊ_ምልአት" በሚል ርዕስ በሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በተሰጠው የሥልጠና ርዕስ ጉዳይ ላይ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች ማጠቃለያ በሰጡበት ወቅት ነው።
ክቡር አቶ ዛዲግ ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት #የኢትዮጵያ ታሪክ አጻጻፍ ላይ በሚነሱ አንዳንድ ክፍተቶች ምክንያት የጋራ ታሪክና የወል ትርክቶች መፍጠር አለመቻሉን ገልፀዋል ።
በመሆኑም እነዚህ አሉ የሚባሉ የታሪክ አተራረክ ክፍተቶችን በማረቅ ከነጠላ ትርክት ይልቅ አሰባሳቢና የጋራ የሆነ ትርክት መፍጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
--------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 08 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የኢትዮጵያን ህልም ዕውን ለማድረግ የጋራ ትርክት መፍጠር አስፈላጊና አጋዥ ነው ሲሉ #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ገለፁ።
ክቡር አቶ ዛዲግ ይህን የገለፁት #"የትርክት_እመርታ_ከታሪካዊ_ስብራት_ወደ_ሀገራዊ_ምልአት" በሚል ርዕስ በሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በተሰጠው የሥልጠና ርዕስ ጉዳይ ላይ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች ማጠቃለያ በሰጡበት ወቅት ነው።
ክቡር አቶ ዛዲግ ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት #የኢትዮጵያ ታሪክ አጻጻፍ ላይ በሚነሱ አንዳንድ ክፍተቶች ምክንያት የጋራ ታሪክና የወል ትርክቶች መፍጠር አለመቻሉን ገልፀዋል ።
በመሆኑም እነዚህ አሉ የሚባሉ የታሪክ አተራረክ ክፍተቶችን በማረቅ ከነጠላ ትርክት ይልቅ አሰባሳቢና የጋራ የሆነ ትርክት መፍጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።