African Leadership Excellence Academy
2.3K subscribers
2.49K photos
96 videos
6 files
116 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
የአካዳሚው ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ ከሚዲያ ተቋማት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ከሰጡት ምላሽና አስተያየት የተወሰደ

የአገራችን ከፍታ ማለት የአመራር ከፍታ ነው፡፡ የአመራር ከፍታ ማለት ደግሞ የአመራር የአመለካከት፣ የክህሎት እና የብቃት ከፍታ ነው ተብሎ የሚታሰበው፡፡ ምክንያቱም ብዙ ሀገሮች የተለወጡት ጠንካራ አመራር ስላላቸው ነው ለሀገር የሚያስቡ፣ የማይሰርቁ፣ Committed የሆኑና ለሀገር የሚቆርቆሩ አመራሮች ስላላቸው ከድህነት ተነስተው ተለውጠዋል፡፡ ለምሳሌ ቻይና የዛሬ 30 እና 40 አመት ከኢትዮጵያ ጋር እኩል ድህነት ተርታ ላይ የነበረች አገር ናት፤ ኮሪያ የዛሬ 50 አመት እኛ ስንደግፋት የነበረች አገር ናት ነገር ግን ዛሬ ከአለማችን ALMOST 1ኛ እና 2ኛ ከሚባሉ ደረጃ ደርሰዋል ማለት ይቻላል፡፡ የዚህ ሁሉ ሚስጥር ደግሞ አመራር ነው፤ ስለዚህ አመራርን ማብቃት፣ ማሰልጠን፣ አመራር የሚሰለጥንበት ቦታ ማደራጀት ለቀጣይ የብልፅግና ጉዛችን ትልቁ መሰረት ነው ብለን ነው የምናምነው፡፡ አካዳሚያችንም ከተሰጠው ተልዕኮ አንፃር እነዚህን ነገሮች በአግባቡ ማበልፀግ፣ ማደራጀትና ለስልጠና ምቹ እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡
ለአካደሚው አመራሮች ባለሙያዎች የማናቃቂየ ስልጠና ተሰጠ ፡፡

ስልጠናውን የሰጡት ከኮርያ የመጡ የአይ ዋይ ኤፍ (IYF) ባለሙያዎች ናቸው፡፡
የመናቃቂያ ስልጠናው የኮሪያን የእድገት መንገድ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም የአካዳሚው አመራሮችና ባለሙያዎች ምን ሊማሩበት እንደሚችሉና እንዴት ከአስተሳሰብና ከአመለካከት ለውጥ ጋር ማስተሳሰር እንደሚገባቸው ለማስቻል የሚረዳ መሆኑን የገለፅት የስልጠና ቡድን አባላት፤ ኢትዮጵያ ምቹ የተፈጥሮ ሃብት ያላትና ለቅኝ ገዢዎች እጀቸውን ያልሰጡ የትልቅ ህዝቦች ሃገር ሆና ሳለ ድሃ መባሏ የሚያቆጭ ነው ብለዋል፡፡ ይህን የተፈጥሮ ሃብትና ትልቅ ህዝብ ይዞ ካደጉት ሃገሮች ተርታ ለመሰለፍ የአስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ያስረዱት አባላቱ ለዚህ ደግሞ የአመራር ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አካዳሚው እያስገነባ ያለው ዘመናዊ የትምህርትና ስልጠና ማዕከል ተጎበኘ

በቻይና መንግስት ዕርዳታ እየተገነባ የሚገኘው ዘመናዊ የትምህርትና ስልጠና ማዕከል የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ በዛብህ ገብረየስ፣ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ብርሃኑ ፈይሳ እና በአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች ተጎብኝቷል፡፡
የግንባታ ሂደቱ ዘጠና አምስት ፐርሰንት (95%) መጠናቀቁን የገለፁት የአካዳሚው ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ በአፍሪካ ደረጃ እጅግ ዘመናዊ የሆነ የአመራር ማብቂያ ህንፃ ኮምፕሌክስ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ በዛብህ ገብረየሱስ በበኩላቸው አካዳሚው በአሁኑ ወቅት ራሱን ከሃገሪቱ ለውጥ ጋር ለማራመድ እያከሄደው ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን ገልፀው እየተገነባ ያለው ዘመናዊ የአመራር ህንፃ የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡
አካዳሚው ከኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

የኢፌዴሪ መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ከኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ጋር የተጀመረውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግና በጋራ በጥናትና ምርምር፤ በስልጠናና በድጋፍ፣ በአመራር አቅም ግንባታ እና በካይዘን ትግበራ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ (MoU) ተፈራርመዋል፡፡
በአካዳሚው በኩል የፊርማ ስነ ስርዓቱን ያከናወኑት የአካዳሚው ፕሬዝዳንት አቶ አወሉ አብዲ አገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ ከግብ ለማድረስ በዘመናዊ የካይዘን አሰራር የተካነ አመራር ትልቅ ድርሻ እንዳለው በማንሳት የተጀመረውን የጋራ ስራ ወደ ተግባር በመለውጥ ውጤታማ ስራ ማከናወን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት በኩል ፊርማቸውን ያኖሩት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን ያኢ በበኩላቸው ካይዘን ሂደትንና የአመለካከት ግንባታን ቀጣይነት ባለው ሁኔታ በማሻሻል የማያቋርጥ ለውጥ እውን እንዲሆን እንደሚያግዝ በተግባራዊ ልምምድ የተፈተሸና የተረጋገጠ አማራጭ የአመራር ፍልስፍና ነው ያሉት ዳይሬክተሩ ለአገራችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ግቦች መሳካት የሚረባረብ የጋራ አመራር ዘይቤ ለመፍጠር ከምንጊዜውም በላይ ያለንን እምቅ አቅም አሰባስበንና አቀናጅተን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
የአካዳሚው የትምህርትና ስልጠና ፍላጎትና ውጤታማነት ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ሞገስ ሎጋው ስለመግባቢያ ሰነዱ ሲናገሩ ችግር ፈቺ የሆነ ጠናትና ምርምር ፤ ጥራቱን የጠበቀ፣ ዘመናዊና ወጪ ቆጣቢ የሆነ የካይዘን አሰራር እና በዘመናዊ የካይዘን አሰራር የተካነ አመራር ለማፍራት እንዲሁም በሌሎች ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች በጋራ ለመስራትና ወደ ተግባር ለመግባት የመግባቢያ