አቶ ዛዲግ አብርሃ ከ UNIDO ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር ተወያዩ።
ርዕሰ አካዳሚው የተወያዩት ከአኡሬሊአ ፓትሪዚአ (Aurelia Patrizia Calabro, UNIDO Representative and Director of the Regional Office) እና አሰግድ አዳነ የ UNIDO ምክትል ተወካይ (Deputy UNIDO Representative) ጋር ነው ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከከፍተኛ የስረ ሃላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል።
ርዕሰ አካዳሚው አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተለይም ልዩ የኢንዱስትሪ አመራር ልማት ፕሮግራም መቀረጹን የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ከUNIDO ጋር በመሆን የኢንዱስትሪውን ዘርፍ አመራር ለማብቃት እንሰራለን ብለዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም UNIDO በአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቀረጻ፤ በአፍሌክስ አመራር ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ግንባታ ላይ ከአፍሌክስ ጋር አብሮ እንዲሰራ ግብዣ አቅርበዋል።
ርዕሰ አካዳሚው የተወያዩት ከአኡሬሊአ ፓትሪዚአ (Aurelia Patrizia Calabro, UNIDO Representative and Director of the Regional Office) እና አሰግድ አዳነ የ UNIDO ምክትል ተወካይ (Deputy UNIDO Representative) ጋር ነው ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከከፍተኛ የስረ ሃላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል።
ርዕሰ አካዳሚው አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተለይም ልዩ የኢንዱስትሪ አመራር ልማት ፕሮግራም መቀረጹን የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ከUNIDO ጋር በመሆን የኢንዱስትሪውን ዘርፍ አመራር ለማብቃት እንሰራለን ብለዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም UNIDO በአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቀረጻ፤ በአፍሌክስ አመራር ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ግንባታ ላይ ከአፍሌክስ ጋር አብሮ እንዲሰራ ግብዣ አቅርበዋል።
አኡሬሊአ ፓትሪዚአ (Aurelia Patrizia Calabro, UNIDO Representative and Director of the Regional Office) በበኩላቸው በኢንዱስትሪ አመራር ልማት ፕሮግራም፤ በአፍሌክስ ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ላይ የአፍሌክስ ፕሮጀክቶችን በቴክኒክ እና በባለሙያ መደገፍ እንደሚቻል ገልጸው፤ ለዚሁ የሚረዳ ዝርዝር ሀሳቦችን የሚያሳይ ፕሮፖዛል ለ UNIDO እንዲቀርብ ጠይቀዋል።
ዝርዝር የድጋፍ እና እገዛ ፍላጎቶችን የሚገልጽ ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ለ UNIDO እንዲቀርብ በመስማማትም ውይይቱ ተጠናቋል።
ዝርዝር የድጋፍ እና እገዛ ፍላጎቶችን የሚገልጽ ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ለ UNIDO እንዲቀርብ በመስማማትም ውይይቱ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን የሰባ አምስት ዓመታት ስኬታማ ጉዞ የሚያሳይ የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ምርምር ሪፖርት ቀረበ። ጥናቱን ያካሔደው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሲሆን የአየር መንገዱ ስራ አመራር አባላት ተገኝተው ሪፖርቱን ገምግመዋል።
የጥናቱ ዋና ዓላማም የአየር መንገዱን የስኬት ምስጢር በሳይንሳዊ ጥናት እና ምርምር ማረጋገጥና ለሌሎች ተቋማት እንደ ግብዓት የሚሆን የጥናት ሪፖርት ማቅረብ እንደሆነ በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ ተመላክቷል።
የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ሪፖርት ሲገመገም በመድረኩ የተገኙት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ታሪክ ለሀገራችን ስኬታማ ጉዞ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቀላል እንዳልሆነ ጠቅሰው፤ አካዳሚው እንደ ኬዝ ጥናት ወስዶ ማጥናቱ ለአመራር ልማት ፕሮግራሞቹ ግብዓት ከመሆኑም በላይ ለሌሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት የስኬት መንገድ ማሳያ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም የተገኘው የጥናት ውጤት እንዴት እንደሚሰፋ እና በስራ ላይ እንደሚውል ሀሳብ የሰጡ ሲሆን፤ ከመድረኩ የተገኘውን ግብዓት በማካተት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ባለድርሻ አካላት ሊጠቀሙበት የሚችል ውጤታማና ተግባራዊ የጥናት ውጤት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የጥናቱ ዋና ዓላማም የአየር መንገዱን የስኬት ምስጢር በሳይንሳዊ ጥናት እና ምርምር ማረጋገጥና ለሌሎች ተቋማት እንደ ግብዓት የሚሆን የጥናት ሪፖርት ማቅረብ እንደሆነ በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ ተመላክቷል።
የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ሪፖርት ሲገመገም በመድረኩ የተገኙት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ታሪክ ለሀገራችን ስኬታማ ጉዞ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቀላል እንዳልሆነ ጠቅሰው፤ አካዳሚው እንደ ኬዝ ጥናት ወስዶ ማጥናቱ ለአመራር ልማት ፕሮግራሞቹ ግብዓት ከመሆኑም በላይ ለሌሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት የስኬት መንገድ ማሳያ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም የተገኘው የጥናት ውጤት እንዴት እንደሚሰፋ እና በስራ ላይ እንደሚውል ሀሳብ የሰጡ ሲሆን፤ ከመድረኩ የተገኘውን ግብዓት በማካተት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ባለድርሻ አካላት ሊጠቀሙበት የሚችል ውጤታማና ተግባራዊ የጥናት ውጤት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ሪፖርት የተቀመጠለትን ግብ ማሳካቱን እና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መሰራቱን አረጋግጠው፤ ጥናቱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለባለድርሻ አካላት የሚኖረውን ጥቅም ከግምት በማስገባት የተሰጡትን ሀሳቦች እና አስተያየቶች አካቶ ስራ ላይ ቢውል ለተቋም ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
በመድረኩ የተሳተፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀድሞ ዋና ስራ አስፈጻሚዎች፤ የቀድሞ የቦርድ አመራሮች፤ የማኔጅመንት አባላት እና የአፍሌክስ አመራሮች በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ አስተያየት እና ሀሳብ የሰጡ ሲሆን የተሰጡትን ግብዓቶች በማካተት የመጨረሻ የጥናት ሪፖርት እንደሚቀርብም ለማወቅ ተችሏል።
በመድረኩ የተሳተፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀድሞ ዋና ስራ አስፈጻሚዎች፤ የቀድሞ የቦርድ አመራሮች፤ የማኔጅመንት አባላት እና የአፍሌክስ አመራሮች በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ አስተያየት እና ሀሳብ የሰጡ ሲሆን የተሰጡትን ግብዓቶች በማካተት የመጨረሻ የጥናት ሪፖርት እንደሚቀርብም ለማወቅ ተችሏል።
የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ መፅሐፍ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት በአብርሆት ቤተ መፅሐፍት እየተደረገ ይገኛል
**********
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ" የተሰኘ መፅሐፍ የምረቃ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተደረገ ይገኛል።
መፅሐፉ ለኢትዮጵያ ህልውና ከፍተኛ ሚና ባላቸው የዓባይ ወንዝ እና ቀይ ባሕር ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን፤ በስድስት ምዕራፎችም የተከፋፈለ ነው።
መፅሐፉ የዓባይ ተፋሰስ እና የባሕር በር ጉዳይ ዐቢይ ስትራቴጂ አዲስ ዕይታ፣ በዓባይ ተፋሰስ የውኃ ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና መጫወት፣ የሕግና የፖሊሲ ጉዳዮች እንዲሁም ስለ ባሕር በር የዓለም አቀፍ ሕግ፣ የሀገራት ተሞክሮ እና የባሕር በር ታሪካችን በስፋት ተዳሰውበታል።
የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ መፅሐፍ በሁለቱ የውኃ አካላት ላይ ጥቅሞቻችን፣ ልንከተላቸው የሚገቡ መርሆችና ስትራቴጂዎችም ተካተውበታል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በመፅሃፉ ላይ ዳሰሳ አቅርበዋል::
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይየመንግስት ኃላፊዎችና አመራሮች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ ጋዜጠኞች እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተዋል።
**********
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ" የተሰኘ መፅሐፍ የምረቃ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተደረገ ይገኛል።
መፅሐፉ ለኢትዮጵያ ህልውና ከፍተኛ ሚና ባላቸው የዓባይ ወንዝ እና ቀይ ባሕር ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን፤ በስድስት ምዕራፎችም የተከፋፈለ ነው።
መፅሐፉ የዓባይ ተፋሰስ እና የባሕር በር ጉዳይ ዐቢይ ስትራቴጂ አዲስ ዕይታ፣ በዓባይ ተፋሰስ የውኃ ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና መጫወት፣ የሕግና የፖሊሲ ጉዳዮች እንዲሁም ስለ ባሕር በር የዓለም አቀፍ ሕግ፣ የሀገራት ተሞክሮ እና የባሕር በር ታሪካችን በስፋት ተዳሰውበታል።
የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ መፅሐፍ በሁለቱ የውኃ አካላት ላይ ጥቅሞቻችን፣ ልንከተላቸው የሚገቡ መርሆችና ስትራቴጂዎችም ተካተውበታል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በመፅሃፉ ላይ ዳሰሳ አቅርበዋል::
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይየመንግስት ኃላፊዎችና አመራሮች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ ጋዜጠኞች እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከUNDP Regional Service Center for Africa ዳይሬክተር እና ከሳሙኤል ግባይዴ ዶኤ (Samuel Gbaydee Doe, UNDP, Resident Representative) ጋር ተወያዩ::
ርዕሰ አካዳሚው ለማትያስ ዘ. ናብ (ዶ/ር) Matthias Z. Naab (PhD) እና ለሳሙኤል ግባይዴ ዶኤ (Samuel Gbaydee Doe, UNDP, Resident Representative) አፍሌክስ በሶስት ዓመት ውስጥ ስለሚተገብራቸው የአመራር ልማት ፕሮጀክቶች ገለፃ አድርገውላቸዋል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በጠቅላላ (General) አራት እና በልዩ (Specialized )ሰላሳ ስምንት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርፆ ወደ ስራ እንደገባ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ለሁሉም ፕሮግራሞች ማስፈፀሚያ የሚሆን ከ2,500 በላይ ገፆች ያሉት ዝርዝር ስትራቴጂ እንደተዘጋጀ ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል::
አቶ ዛዲግ አያይዘውም አፍሌክስ ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሀገራት ባለ ድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሆነ እና ከ ዩ ኤን ዲ ፒ ጋርም በትብብር በመስራት ያቀደውን ማሳካት እንደሚፈልግ ጠቅሰዋል።
ርዕሰ አካዳሚው ለማትያስ ዘ. ናብ (ዶ/ር) Matthias Z. Naab (PhD) እና ለሳሙኤል ግባይዴ ዶኤ (Samuel Gbaydee Doe, UNDP, Resident Representative) አፍሌክስ በሶስት ዓመት ውስጥ ስለሚተገብራቸው የአመራር ልማት ፕሮጀክቶች ገለፃ አድርገውላቸዋል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በጠቅላላ (General) አራት እና በልዩ (Specialized )ሰላሳ ስምንት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርፆ ወደ ስራ እንደገባ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ለሁሉም ፕሮግራሞች ማስፈፀሚያ የሚሆን ከ2,500 በላይ ገፆች ያሉት ዝርዝር ስትራቴጂ እንደተዘጋጀ ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል::
አቶ ዛዲግ አያይዘውም አፍሌክስ ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ ሀገራት ባለ ድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሆነ እና ከ ዩ ኤን ዲ ፒ ጋርም በትብብር በመስራት ያቀደውን ማሳካት እንደሚፈልግ ጠቅሰዋል።
ማትያስ ዘ. ናብ (ዶ/ር) Matthias Z. Naab (PhD) በበኩላቸው አፍሌክስ የአመራር ለውጥ ባደረገ በአጭር ጊዜ ውስጥ ያቀደው የሪፎርም፤ የማስፋት እና የሽግግር ስትራቴጂ የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ የአፍሌክስ የአመራር ልማት ማዕቀፍ እንዲሳካ ዩ ኤን ዲ ፒ ከአፍሌክስ ጋር ለመስራት ፍላጎት እንዳለው አሳውቀዋል።
ከአፍሌክስ ጋር በትብብር ለመስራትም ጉዳዩን የሚከታተል የዩ ኤን ዲ ፒ ከፍተኛ ባለሙያ እንደተመደበም ማትያስ ዘ. ናብ (ዶ/ር) Matthias Z. Naab (PhD ገልጸዋል::
ከሳሙኤል ግባይዴ ዶኤ (Samuel Gbaydee Doe, UNDP, Resident Representative) በበኩላቸው ከአቶ ዛዲግ ጋር ከዚህ ቀደም የተጀመረውን ግንኙነት ወደ ተግባር ለማሸጋገር የዛሬው ውይይት ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ የሁለቱን ተቋማት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ መርሀ ግብር እንደሆነ ተናግረዋል።
የUNDP Regional Service Center for Africa ዳይሬክተር እና ከሳሙኤል ግባይዴ ዶኤ (Samuel Gbaydee Doe, UNDP, Resident Representative) የአፍሌክስን ፋሲለቲ ጎብኝተዋል።
ከአፍሌክስ ጋር በትብብር ለመስራትም ጉዳዩን የሚከታተል የዩ ኤን ዲ ፒ ከፍተኛ ባለሙያ እንደተመደበም ማትያስ ዘ. ናብ (ዶ/ር) Matthias Z. Naab (PhD ገልጸዋል::
ከሳሙኤል ግባይዴ ዶኤ (Samuel Gbaydee Doe, UNDP, Resident Representative) በበኩላቸው ከአቶ ዛዲግ ጋር ከዚህ ቀደም የተጀመረውን ግንኙነት ወደ ተግባር ለማሸጋገር የዛሬው ውይይት ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ የሁለቱን ተቋማት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ መርሀ ግብር እንደሆነ ተናግረዋል።
የUNDP Regional Service Center for Africa ዳይሬክተር እና ከሳሙኤል ግባይዴ ዶኤ (Samuel Gbaydee Doe, UNDP, Resident Representative) የአፍሌክስን ፋሲለቲ ጎብኝተዋል።