አቶ ዛዲግ አብርሃ ከሳውዘርን ኮፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን ሴክሬተሪ ጄኔራል መንሱር ቢን ሙሳላም Mansssour Bin Mussallam Secretary General of the Organization of Southeren Cooperation (OSC)ጋር ተወያዩ።
ለሴክሬተሪ ጄኔራሉ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ ሰፊ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመው፤ ለዚህም የሚሆን አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው አፍሪካዊ መልክና ይዘት እንዲኖረውም እየተሰራ እንደሆነ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ፤ የታቀደውን ለመፈጸም የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።
አፍሌክስን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት መቀረጹን ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ሸገር ሲቲን ከዳቮስ ከተማ ጋር በእህትማማች ከተማ ለማገናኘት ስራ መጀመሩንም ተናግረዋል።
ሳውዘርን ኮፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን በአፍሪካ ፕሮግራሞች ላይ በዲዛይን እና ፕሮግራም ቀረጻ ፤ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርጉ እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ ከአፍሌክስ ጋር በትብብር እንዲሰራ አቶ ዛዲግ ግብዣ አቅርበዋል።
ለሴክሬተሪ ጄኔራሉ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ ሰፊ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመው፤ ለዚህም የሚሆን አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው አፍሪካዊ መልክና ይዘት እንዲኖረውም እየተሰራ እንደሆነ ያስታወሱት አቶ ዛዲግ፤ የታቀደውን ለመፈጸም የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።
አፍሌክስን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት መቀረጹን ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ሸገር ሲቲን ከዳቮስ ከተማ ጋር በእህትማማች ከተማ ለማገናኘት ስራ መጀመሩንም ተናግረዋል።
ሳውዘርን ኮፐሬሽን ኦርጋናይዜሽን በአፍሪካ ፕሮግራሞች ላይ በዲዛይን እና ፕሮግራም ቀረጻ ፤ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርጉ እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ ከአፍሌክስ ጋር በትብብር እንዲሰራ አቶ ዛዲግ ግብዣ አቅርበዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ በበኩላቸው ክቡር አቶ ዛዲግ በአፍሌክስ ውስጥ በተመደቡ በወራት ውስጥ ታላቅ ሀገራዊ የአመራር ልማት ፕሮግራም እና ፕሮጀክቶችን ቀርጸው ወደ ስራ ለመግባት ያደረጉትን ጥረት አድንቀው፤ ከአመራር ጋር በተያያዘ ያለውን የኢትዮጵያን ፖለቲካል ኢኮኖሚ ስብራት ለመጠገን የአመራር ልማት ፕሮግራሞቹ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖራቸው ተናግረዋል።
በአፍሌክስ ውስጥ ውጤታማ አመራር ማፍራት እና ማብቃት ከተቻለ ምርት እና ምርታማነትን መጨመር እንደሚቻል የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትሩ ከአካዳሚው ጋር በመሆን ለአመራር ልማት ዕድገት የበኩላቸውን አሻራ ማሳረፍ እንደሚፈልጉ ተናግረው በዝርዝር በማየት በምን መልኩ ከአፍሌክስ ጋር መስራት እንደሚችሉ መነሻ ጥናት እንዲዘጋጅ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ከሁለቱም ተቋማት የተውጣጡ የቴክኒክ ኮሚቴም በሁለት ሳምንት ውስጥ መነሻ ሀሳብ እንዲያቀርብ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
በአፍሌክስ ውስጥ ውጤታማ አመራር ማፍራት እና ማብቃት ከተቻለ ምርት እና ምርታማነትን መጨመር እንደሚቻል የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትሩ ከአካዳሚው ጋር በመሆን ለአመራር ልማት ዕድገት የበኩላቸውን አሻራ ማሳረፍ እንደሚፈልጉ ተናግረው በዝርዝር በማየት በምን መልኩ ከአፍሌክስ ጋር መስራት እንደሚችሉ መነሻ ጥናት እንዲዘጋጅ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ከሁለቱም ተቋማት የተውጣጡ የቴክኒክ ኮሚቴም በሁለት ሳምንት ውስጥ መነሻ ሀሳብ እንዲያቀርብ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ ጋር ተወያዩ።
አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ እና ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች አብራርተዋል።
አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ለይቶ ለስምንቱ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ፤ አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመታት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
አፍሌክስን የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተሰራ እንደሆነ ይህንኑ ዓላማ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአፍሌክስ ጋር አብሮ እንዲሰራ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም በአፍሌክስ ውስጥ ከሚገነቡ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ውስጥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል አመራር ማዕከል እንዲገነባ እና የሚኒስቴሩ አመራሮችና ባለሙያዎች በማእከሉ በመጠቀም በጥናትና ምርምር ስራ ውስጥ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ ለኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ እና ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች አብራርተዋል።
አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ለይቶ ለስምንቱ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ፤ አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመታት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
አፍሌክስን የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተሰራ እንደሆነ ይህንኑ ዓላማ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአፍሌክስ ጋር አብሮ እንዲሰራ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም በአፍሌክስ ውስጥ ከሚገነቡ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ውስጥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል አመራር ማዕከል እንዲገነባ እና የሚኒስቴሩ አመራሮችና ባለሙያዎች በማእከሉ በመጠቀም በጥናትና ምርምር ስራ ውስጥ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።
በኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የዋር ኮሌጅ ከፍተኛ አመራሮች እና ተማሪዎች የአፍሌክስን ፋሲሊቲ ጎበኙ።
ለከፍተኛ አመራሮቹና ተማሪዎቹ አቀባበል ያደረጉት የአፍሌክስ የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ሲሆኑ አካዳሚው የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ውስጥ እንደሆነ ጠቅሰው ከኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን ልዩ የአርሚ የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመቅረጽ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ለልኡካን ቡድኑ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ገለጻ ያደረጉት አቶ መስፍን በሀይሉ ሲሆኑ አፍሌክስ በአመራር ስርአት ውስጥ ያሉ ስብራቶችን ለመጠገን እንዲችል አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እንደገባ ጠቅሰው አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ተቀርጸዋል ብለዋል።
ጉብኝት ካደረጉ እና ገለጻውን ከተከታተሉ የዋር ኮሌጅ ከፍተኛ አመራሮች እና ተማሪዎች ውስጥ አራት ብርጋዴር ጄኔራሎች፤ ሁለት የውጭ ሀገር ጄኔራሎች፤ የረጅም እና የአጭር ኮርስ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
ለከፍተኛ አመራሮቹና ተማሪዎቹ አቀባበል ያደረጉት የአፍሌክስ የኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ሲሆኑ አካዳሚው የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ውስጥ እንደሆነ ጠቅሰው ከኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመሆን ልዩ የአርሚ የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመቅረጽ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ለልኡካን ቡድኑ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ገለጻ ያደረጉት አቶ መስፍን በሀይሉ ሲሆኑ አፍሌክስ በአመራር ስርአት ውስጥ ያሉ ስብራቶችን ለመጠገን እንዲችል አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እንደገባ ጠቅሰው አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ተቀርጸዋል ብለዋል።
ጉብኝት ካደረጉ እና ገለጻውን ከተከታተሉ የዋር ኮሌጅ ከፍተኛ አመራሮች እና ተማሪዎች ውስጥ አራት ብርጋዴር ጄኔራሎች፤ ሁለት የውጭ ሀገር ጄኔራሎች፤ የረጅም እና የአጭር ኮርስ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
ከአፍሌክስ ጋር ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ዋና ዳይሬክተሩ በአመራር ልማት ፕሮግራም: በአፍሌክስ አዋርድ: በውጭ ሀገር የሚካሄዱ አጫጭር ስልጠናዎችን በመቀነስ እና በማስቀረት አብሮ መስራት እንደሚቻል ጠቁመው: በስራቸው ካሉ ኢንተርፕራይዞች ጋር በመወያየት የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ለመገንባት የሚቻልበት ሁኔታ እንዳለ ተናግረዋል::
አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሌክስን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለኢፌዴሪ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ገለጻ አደረጉ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከኢፌዴሪ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ እንደገለጹት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የአመራር ልማት ፕሮግራም የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አፍሌክስ ከኢፌዴሪ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር ጋር በመሆን በዘርፉ ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራም በመቅረጽ ወደ ስራ ለመግባት ዝግጁ መሆኑን የገለጹት አቶ ዛዲግ፤ ተቋሙ ያለውን ሰፊ የባለሙያ አቅም እና ልምድ በመጠቀም ከአፍሌክስ ጋር እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል። የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል በመገንባትም በዘርፉ ያለውን የጥናትና ምርምር ስራዎች በማጎልበት ሳይንሳዊ እና ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን ማፍለቅ እንደሚገባ ርዕሰ አካዳሚው ተናግረዋል።
የኢፌዴሪ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ አቶ ኃብታሙ ኃይለሚካኤል በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳውን አህጉር አቀፍ የሪፎርም፤ የማስፋት እና የሽግግር ዕቅድ አድንቀው ለተግባራዊነቱ ተቋማቸው ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከኢፌዴሪ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ እንደገለጹት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የአመራር ልማት ፕሮግራም የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አፍሌክስ ከኢፌዴሪ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር ጋር በመሆን በዘርፉ ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራም በመቅረጽ ወደ ስራ ለመግባት ዝግጁ መሆኑን የገለጹት አቶ ዛዲግ፤ ተቋሙ ያለውን ሰፊ የባለሙያ አቅም እና ልምድ በመጠቀም ከአፍሌክስ ጋር እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል። የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል በመገንባትም በዘርፉ ያለውን የጥናትና ምርምር ስራዎች በማጎልበት ሳይንሳዊ እና ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን ማፍለቅ እንደሚገባ ርዕሰ አካዳሚው ተናግረዋል።
የኢፌዴሪ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ አቶ ኃብታሙ ኃይለሚካኤል በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳውን አህጉር አቀፍ የሪፎርም፤ የማስፋት እና የሽግግር ዕቅድ አድንቀው ለተግባራዊነቱ ተቋማቸው ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ ከኖርዌይ አምባሳደር ስቲአን ክሪስተንሰን Stian Christensen, Ambassador and Permanent Representative to AU, IGAD and UNECA ጋር ተወያዩ።
ለአምባሳደሩ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አቶ ዛዲግ እንዳብራሩት አካዳሚው አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ ሰፊ ዕቅድ መታቀዱን ጠቅሰው፤ ለዚህም የሚሆን አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው በሚቀርጻቸው የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ላይ ከኖርዌይ መንግስት እና በኖርዌይ ካሉ የስልጠና እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር መስራት እንደሚፈልጉ የጠቆሙት አቶ ዛዲግ፤ ለዚህም አምባሳደሩ በጎ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉም ግብዣ አቅርበዋል።
በኖርዌይ ከሚገኙ ትልልቅ ተቋማት ጋርም ስትራቴጂያዊ አጋርነት በመመስረት አፍሌክስ ያቀደውን ተግባራዊ ለማድረግ ይፈልጋል ያሉት አቶ ዛዲግ፤ በተለይም ከከፍተኛ የስልጠና ተቋማት ጋር በመሆን የአሰልጣኞች እና የተመራማሪዎች ልውውጥ ማድረግ የአፍሌክስን ልህቀት ማረጋገጥ ተገቢ እንደሆነ ተናግረዋል።
በአፍሌክስ ውስጥ ከሚገነቡ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ውስጥም ኤምባሲው የመሰረተ ልማት ግንባታ እንዲያደርግ እና የተሻለ ሀሳብ እንዲፈልቅ በትውልድ ግንባታ ላይ እንዲሳተፍ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
ለአምባሳደሩ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አቶ ዛዲግ እንዳብራሩት አካዳሚው አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ ሰፊ ዕቅድ መታቀዱን ጠቅሰው፤ ለዚህም የሚሆን አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
አካዳሚው በሚቀርጻቸው የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ላይ ከኖርዌይ መንግስት እና በኖርዌይ ካሉ የስልጠና እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር መስራት እንደሚፈልጉ የጠቆሙት አቶ ዛዲግ፤ ለዚህም አምባሳደሩ በጎ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉም ግብዣ አቅርበዋል።
በኖርዌይ ከሚገኙ ትልልቅ ተቋማት ጋርም ስትራቴጂያዊ አጋርነት በመመስረት አፍሌክስ ያቀደውን ተግባራዊ ለማድረግ ይፈልጋል ያሉት አቶ ዛዲግ፤ በተለይም ከከፍተኛ የስልጠና ተቋማት ጋር በመሆን የአሰልጣኞች እና የተመራማሪዎች ልውውጥ ማድረግ የአፍሌክስን ልህቀት ማረጋገጥ ተገቢ እንደሆነ ተናግረዋል።
በአፍሌክስ ውስጥ ከሚገነቡ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ውስጥም ኤምባሲው የመሰረተ ልማት ግንባታ እንዲያደርግ እና የተሻለ ሀሳብ እንዲፈልቅ በትውልድ ግንባታ ላይ እንዲሳተፍ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
የኖርዌይ አምባሳደር ስቲአን ክሪስተንሰን Stian Christensen, Ambassador and Permanent Representative to AU, IGAD and UNECA በበኩላቸው አፍሌክስ ያቀረበውን ገለጻ አድንቀው በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር ኤምባሲያቸው ፈቃደኛ መሆኑን ጠቅሰው በሚቀርቡ ዝርዝር ጥናቶች ላይ ተመስርተው በስፋት ለመነጋገር ቀጠሮ በመያዝ ውየዕይቱ ተጠናቋል።