የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራም፤ ተጠቃሚዎች እና መሰረተ ልማቱን በማስፋት ወደ ሽግግር ለማምራት በሚደረገው ሂደት ውስጥ የፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን አዎንታዊ ሚና እንዳለው ተገለጸ።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሪፎርም (Reform)፤ በማስፋት (Scaling Up) እና በሽግግር (Transformation) ዘርፎች ላይ አስራ ሶስት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ለይቶ ለስምንቱ ቅድሚያ በመስጠት ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስራ ሀላፊዎች ገልጸዋል።
ርዕሰ አካዳሚው እንደገለጹት አፍሌክስን ሪፎርም ለማድረግ፤ ለማስፋትና ለማሸጋገር አስራ ሶስት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን በሶስት ዓመት ውስጥ ለመተግበር የሚረዳ ከ2500 በላይ ገጽ ያለው የስትራቴጂ ሰነድ መዘጋጀቱን ጠቅሰው ለስምንቱ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቅድሚያ በመስጠት ወደ ስራ እንደገቡ እና የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራም፤ ተጠቃሚዎች እና መሰረተ ልማቱን በማስፋት ወደ ሽግግር ለማምራት በሚደረገው ሂደት ውስጥ የፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን አዎንታዊ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።
የፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ በበኩላቸው አፍሌክስ ያቀዳቸውን የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ለመደገፍ እና አብሮ ለመስራት ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም አፍሌክስን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ በሚሰራው ስራ ውስጥ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ እና የአፍሪካ የፀረ-ሙስና ኤጀንሲ አባል በመሆኗ በቀጣይ የአስተናጋጅነት ሚናውን ስትወስድ በአፍሌክስ ውስጥ ሊሆን የሚችልበት ሰፊ ዕድል አለ ብለዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሪፎርም (Reform)፤ በማስፋት (Scaling Up) እና በሽግግር (Transformation) ዘርፎች ላይ አስራ ሶስት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ለይቶ ለስምንቱ ቅድሚያ በመስጠት ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስራ ሀላፊዎች ገልጸዋል።
ርዕሰ አካዳሚው እንደገለጹት አፍሌክስን ሪፎርም ለማድረግ፤ ለማስፋትና ለማሸጋገር አስራ ሶስት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን በሶስት ዓመት ውስጥ ለመተግበር የሚረዳ ከ2500 በላይ ገጽ ያለው የስትራቴጂ ሰነድ መዘጋጀቱን ጠቅሰው ለስምንቱ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቅድሚያ በመስጠት ወደ ስራ እንደገቡ እና የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራም፤ ተጠቃሚዎች እና መሰረተ ልማቱን በማስፋት ወደ ሽግግር ለማምራት በሚደረገው ሂደት ውስጥ የፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን አዎንታዊ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።
የፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ በበኩላቸው አፍሌክስ ያቀዳቸውን የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ለመደገፍ እና አብሮ ለመስራት ተቋማቸው ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም አፍሌክስን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ በሚሰራው ስራ ውስጥ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ እና የአፍሪካ የፀረ-ሙስና ኤጀንሲ አባል በመሆኗ በቀጣይ የአስተናጋጅነት ሚናውን ስትወስድ በአፍሌክስ ውስጥ ሊሆን የሚችልበት ሰፊ ዕድል አለ ብለዋል።
የንግዱን ዘርፍ በብቃት ለመምራት ልዩ የንግድ አመራር ልማት ፕሮግራም መቀረጹ ለዘርፉ አመራር የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቀላል ግምት የሚሰጠው እንዳልሆነ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ክቡር ሚኒስትሩ ገብረ መስቀል ጫላ ገለጹ።
ክቡር ሚኒስትሩ ይሕን የተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሪፎርም (Reform)፤ በማስፋት (Scaling Up) እና በሽግግር (Transformation) ዘርፎቹ ላይ ያቀዳቸው ስራዎች ገለጻ በተደረጉላቸው ወቅት ነው።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ስለ አካዳሚው የሶስት ዓመት ስትራቴጂ እና ፕሮግራም ገለጻ አድርገዋል። አቶ ዛዲግ እንደጠቀሱት አፍሌክስ የአህጉሪቱን እና የሀገራችንን አመራሮች ለማብቃት ስልጠና ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በማመኑ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ ተናግረዋል። በእነዚህ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎች ውስጥም ከፍተኛ አመራሮች አቅማቸውን እንደሚገነቡ እና ሀሳብ እያፈለቁ የምርምር ስራዎችን እንደሚያበረክቱ ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳው የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የሚኖረውን ጥቅም አስታውሰው፤ በተለይም ውድድር የበዛበትን የንግዱን ዘርፍ ለሚመሩ የተቋሙ አመራሮች ልዩ የንግድ አመራር ልማት ፕሮግራም መቀረጹ ከፍተኛ ግብዓት እንደሚሆን ተናግረዋል። ተቋማቸውም ለዚህ ፕሮግራም መሳካት በቴክኒክ እና በባለሙያ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ ይሕን የተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሪፎርም (Reform)፤ በማስፋት (Scaling Up) እና በሽግግር (Transformation) ዘርፎቹ ላይ ያቀዳቸው ስራዎች ገለጻ በተደረጉላቸው ወቅት ነው።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ስለ አካዳሚው የሶስት ዓመት ስትራቴጂ እና ፕሮግራም ገለጻ አድርገዋል። አቶ ዛዲግ እንደጠቀሱት አፍሌክስ የአህጉሪቱን እና የሀገራችንን አመራሮች ለማብቃት ስልጠና ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በማመኑ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ ተናግረዋል። በእነዚህ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎች ውስጥም ከፍተኛ አመራሮች አቅማቸውን እንደሚገነቡ እና ሀሳብ እያፈለቁ የምርምር ስራዎችን እንደሚያበረክቱ ገልጸዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳው የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፍ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የሚኖረውን ጥቅም አስታውሰው፤ በተለይም ውድድር የበዛበትን የንግዱን ዘርፍ ለሚመሩ የተቋሙ አመራሮች ልዩ የንግድ አመራር ልማት ፕሮግራም መቀረጹ ከፍተኛ ግብዓት እንደሚሆን ተናግረዋል። ተቋማቸውም ለዚህ ፕሮግራም መሳካት በቴክኒክ እና በባለሙያ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ማዕከልን በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ ለመገንባት መወሰኑን አስታወቀ።
አፍሌክስ እና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረጉት ውይይት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ማዕከልን ሱሉሉታ በሚገኘው የአፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕከል ውስጥ በቅንጅት ለመገንባት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡
ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (አፍሌክስ) ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ እንደገለጹት በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ የሚገነባው የፖሊስ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ማዕከል (Police Peace Keeping Mission Center) ለሠላም ማስከበር ተግባራት መጠናከርና ለቀጠናው የሚኖረው ሚና ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው ግንባታውን ለማስጀመር የሚያስችል ዝርዝር የአፈጻጸም ዕቅድም ከፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በመሆን እንዲዘጋጅ ሀሳብ አቅርበዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች በተመለከተ ባቀረቡት ገለጻ ላይ እንደጠቀሱት የኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመደገፍ የወሰነውን ውሳኔ አድንቀው በሚገነባው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ማዕከል ውስጥ ለሀገራችን እና ለአህጉሪቷ ሰላም መስፈን አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ሀሳቦች እንደሚመነጩ ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ማዕከሉ በአፍሌክስ ውስጥ መገንባቱም ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ውስጥ ያላትን የሰላም ማስከበር ሚና እንደሚያሳድግ ተናግረዋል።
የማዕከሉ ግንባታ በቅርቡ እንዲጀመርም የሁለቱ ተቋማት አመራሮች የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል።
አፍሌክስ እና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደረጉት ውይይት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ማዕከልን ሱሉሉታ በሚገኘው የአፍሌክስ የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕከል ውስጥ በቅንጅት ለመገንባት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡
ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (አፍሌክስ) ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ እንደገለጹት በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ የሚገነባው የፖሊስ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ማዕከል (Police Peace Keeping Mission Center) ለሠላም ማስከበር ተግባራት መጠናከርና ለቀጠናው የሚኖረው ሚና ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው ግንባታውን ለማስጀመር የሚያስችል ዝርዝር የአፈጻጸም ዕቅድም ከፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር በመሆን እንዲዘጋጅ ሀሳብ አቅርበዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች በተመለከተ ባቀረቡት ገለጻ ላይ እንደጠቀሱት የኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመደገፍ የወሰነውን ውሳኔ አድንቀው በሚገነባው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ማዕከል ውስጥ ለሀገራችን እና ለአህጉሪቷ ሰላም መስፈን አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ሀሳቦች እንደሚመነጩ ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ማዕከሉ በአፍሌክስ ውስጥ መገንባቱም ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ውስጥ ያላትን የሰላም ማስከበር ሚና እንደሚያሳድግ ተናግረዋል።
የማዕከሉ ግንባታ በቅርቡ እንዲጀመርም የሁለቱ ተቋማት አመራሮች የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአመራር ልማት ፕሮግራም ላይ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች በተመለከተ ባቀረቡት ገለጻ ላይ እንደጠቀሱት አካዳሚው ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሆን ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን የቀረጸ መሆኑን ገልጸው፤ የዘርፉን አመራርና ባለሙያዎች በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማብቃት ከአገልግሎቱ ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ የአፍሌክስን የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ ማብራሪያ ከተከታተሉ በሁዋላ በሰጡት አስተያየት ተቋማቸው ከአፍሌክስ ጋር ለመስራት ያለውን ፍላጎት ገልጸው በተለይም ከተቋሙ ተልዕኮ አንጻር በአረንጓዴ ኢኮኖሚ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ምስረታ ላይ ለመሳተፍ እንደሚፈልጉ እና ለዚህም ስራውን የሚከታተልና የሚመራ የሰው ሀይል መድበዋል።
በአፍሌክስ ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ውስጥም የአገልግሎቱን አመራርና ባለሙያ ለማብቃት እንደሚሰሩ የገለጹት ዋና ስራ አስፈጻሚው አያይዘውም በአመራር ልማት ፕሮግራም ሽልማት ላይም ከአፍሌክስ ጋር አብረው በመስራት በዘርፉ ያለውን የአመራር ሀይል ለማብቃትና ለሌላውም ሞዴል የሚሆኑ አመራሮችን ለማፍራት የአፍሌክስ የሽልማት ፕሮጀክት ላይ መሳተፍ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች በተመለከተ ባቀረቡት ገለጻ ላይ እንደጠቀሱት አካዳሚው ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሆን ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን የቀረጸ መሆኑን ገልጸው፤ የዘርፉን አመራርና ባለሙያዎች በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማብቃት ከአገልግሎቱ ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ የአፍሌክስን የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ ማብራሪያ ከተከታተሉ በሁዋላ በሰጡት አስተያየት ተቋማቸው ከአፍሌክስ ጋር ለመስራት ያለውን ፍላጎት ገልጸው በተለይም ከተቋሙ ተልዕኮ አንጻር በአረንጓዴ ኢኮኖሚ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ምስረታ ላይ ለመሳተፍ እንደሚፈልጉ እና ለዚህም ስራውን የሚከታተልና የሚመራ የሰው ሀይል መድበዋል።
በአፍሌክስ ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ውስጥም የአገልግሎቱን አመራርና ባለሙያ ለማብቃት እንደሚሰሩ የገለጹት ዋና ስራ አስፈጻሚው አያይዘውም በአመራር ልማት ፕሮግራም ሽልማት ላይም ከአፍሌክስ ጋር አብረው በመስራት በዘርፉ ያለውን የአመራር ሀይል ለማብቃትና ለሌላውም ሞዴል የሚሆኑ አመራሮችን ለማፍራት የአፍሌክስ የሽልማት ፕሮጀክት ላይ መሳተፍ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና በኢትዮጵያ የሚገኘው የደቡብ ኮሪያ ኤምባሲ በአመራር ልማት ፕሮግራም እና በስትራቴጂያዊ ትብብር ላይ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች በተመለከተ ባቀረቡት ገለጻ ላይ እንደጠቀሱት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያንን እና አፍሪካውያንን በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማብቃት ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በጋራ በትብብር መስራት ተገቢ በመሆኑም የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ድጋፍ እንዲያደርግም አቶ ዛዲግ ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የሚገኘው የደቡብ ኮሪያ ኤምባሲ ቆንስል ጄኔራል ጆ ሱንግ ዉክ JO Sung Wook በበኩላቸው አፍሌክስ ስምንት የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎችን ቀርጾ ወደ ስራ ለመግባት ዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡን ማነጋገሩ እና ድጋፍ መጠየቁን አድንቀው ኤምባሲያቸው የኮርያን ልምድ እና አሰራር በማካፈል በኩል አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በሀሳብ ማመንጫ ማእከሉ ላይ ሊሰሩ የሚችሉ ባለሙያዎችን እና ሙሁራንን በማነጋገርም የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመደገፍ እነደሚሰራ የገለጹት ቆንስል ጄኔራሉ በፕሮግራም ቀረጻው እና ዲዛይን ላይ አብረው ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል። በመሰረተ ልማት ስራ ላይ ለመሳተፍም ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ እንደሚፈልጉም ተናግረዋል። አካዳሚውንም ጎብኝተዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች በተመለከተ ባቀረቡት ገለጻ ላይ እንደጠቀሱት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያንን እና አፍሪካውያንን በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማብቃት ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በጋራ በትብብር መስራት ተገቢ በመሆኑም የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ድጋፍ እንዲያደርግም አቶ ዛዲግ ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የሚገኘው የደቡብ ኮሪያ ኤምባሲ ቆንስል ጄኔራል ጆ ሱንግ ዉክ JO Sung Wook በበኩላቸው አፍሌክስ ስምንት የአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎችን ቀርጾ ወደ ስራ ለመግባት ዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡን ማነጋገሩ እና ድጋፍ መጠየቁን አድንቀው ኤምባሲያቸው የኮርያን ልምድ እና አሰራር በማካፈል በኩል አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በሀሳብ ማመንጫ ማእከሉ ላይ ሊሰሩ የሚችሉ ባለሙያዎችን እና ሙሁራንን በማነጋገርም የአፍሌክስን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመደገፍ እነደሚሰራ የገለጹት ቆንስል ጄኔራሉ በፕሮግራም ቀረጻው እና ዲዛይን ላይ አብረው ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል። በመሰረተ ልማት ስራ ላይ ለመሳተፍም ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ እንደሚፈልጉም ተናግረዋል። አካዳሚውንም ጎብኝተዋል።