African Leadership Excellence Academy
2.15K subscribers
2.38K photos
90 videos
6 files
105 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
በሥልጠናው ማጠናቀቂያ መርሐ ግብር ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት ሠልጣኞች የሥልጠናው ርእሰ ጉዳዮች ዘመኑን የዋጁ እና ተቋማዊ ተልዕኮን ለመወጣት የሚያግዙ ናቸው ብለዋል፡፡ አሚኮ በቴክኖሎጂ የዘመነ እና አሁን ያለውን የዓለም የሚዲያ ዕድገት ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች ለመሥራት ዝግጅቶች እያደረገ እንደኾነ ያነሱት ሠልጣኞቹ በየደረጃው ያለውን የሰው ኀይል በዕውቀት እና ክህሎት ለማብቃት የሚደረገው ጥረትም አበረታች ነው ብለዋል፡፡

ሥልጠናው በተለይም በሙያቸው የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው፣ ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታውን እንዲረዱ ያደረገ እና ለሥራቸው አጋዥ የኾኑ እይታዎችን ያገኙበት መኾኑን ጠቅሰዋል። በቀጣይም ራሳቸውን ለማብቃት፣ ለማሻሻል እና ተወዳዳሪ ለመኾን ዝግጅት የሚያደርጉበት እንደሚኾን አንስተዋል፡፡

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ጋዜጠኛ ሙሉቀን ሰጥዬ ኮርፖሬሽኑ ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር ለመሪዎች የተሰጠው ሥልጠና የኮርፖሬሽኑን ስትራቴጂክ ዕቅዶች ለማሳካት እና ኮርፖሬሽኑ የተጣለበትን ኀላፊነት ለመወጣት የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡ ከአሚኮ ጋር በመተባበር ሥልጠናውን ለሰጠው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚም ምሥጋና አቅርበዋል፡፡

ሥልጠናውን የሰጡት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ሚዲያው ተፅዕኖ ፈጣሪ ኾኖ የሕዝብን እውነተኛ ማንነት በበጎ መግለጽ እስኪችል ድረስ አልሞ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

አሁን ላይ በበጎም ይሁን በመጥፎ የምናውቃቸው ሀገራት የሚዲያ ተፅዕኖ ውጤት ናቸው ያሉት አቶ ዛዲግ "አሚኮን መለወጥ እና ማሻሻል ክልሉን በሁለንተናዊ መንገድ ማሻሻል ነው" ብለዋል፡፡ የሰው ኀይሉን በሥልጠና ለማብቃት የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፉም ተናግረዋል፡፡

የአፍሌክስ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇

https://shorturl.at/1Pirn

https://www.tiktok.com/@aflex_academy?_t=ZM-8t1gJsnIFgT&_r=1

https://x.com/Afleexacademy?s=09

https://t.me/afleexac

https://web.facebook.com/@aflexacademy.gov.et

https://aflexacademy.gov.et

http://www.youtube.com/@AfricanLeadershipExcellence
“የመደመር የፍትህ ማዕቀፍ አንድ ነን የሚል አይደለም:: ልዩነትን አክብሮ እና አስተናግዶ በጋራ የሚሰራበት ማዕቀፍ ነው::” አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሌክስ ፕሬዚደንት

አዲስ አበባ: ግንቦት 4/2017 (አፍሌክስ):-የመደመር የፍትህ ማዕቀፍ አንድ ነን የሚል ሳይሆን ልዩነትን አክብሮ እና አስተናግዶ በጋራ የሚሰራበት ማዕቀፍ እንደሆነ ተገለፀ::

ይህ የተገለፀው የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለፍትህ ሚንስቴር ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና በሰጡበት ወቅት ነው::

አቶ ዛዲግ political economy and justice in Ethiopia perspective በሚል ርዕሰ በሰጡት ስልጠና ላይ እንደጠቀሱት የፍትህ ስርአታችን ማዕቀፍ ከሀገር በቀል እውቀቶች ባለመቀዳቱ የምእራባውያን ባህል እና ታሪክ እንደተጫነው አስታውሰው የመደመር የፍትህ ማዕቀፍ ግን ይህንን ችግር የሚፈታ እና የሚያሻግር መሆኑን ገልፀዋል::

የመደመርን የፍትህ እይታ ከሌሎች ዓለም አቀፍ የፍትህ እይታዎች አንፃር በሰፊው የተነተኑት አቶ ዛዲግ: መደመር ፍትህን የሚያይበት እይታ ተለዋዋጭ መሆኑን አስታውሰው: ሀዘን የሚረሳው ፀጋ የሚጎላው እንደ መደመር ባሉ የፍትህ እይታዎች ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል::

“አንዳንድ ነገሮችን ሆን ብለን መርሳት እና ሆን ብለን ማስታወስ አለብን” ያሉት አቶ ዛዲግ “ትውስታ ስልታዊ (Strategic) መሆን አለበት የምናስታውሰው ዛሬን የትናንት እስረኛ ለማድረግ መሆን የለበትም::” ብለዋል::
የተዛባ የፍትህ ስርአት ከአንድ ትውልድ በላይ ተሻግሮ የትውልድ እዳ እንደሚሆነው የጠቆሙት አቶ ዛዲግ በአንፃሩ ፍትህ ከሰፈነ ድምፁ ከፍ ብሎ የሚሰማና በስርአት የሚያምን ህዝብ ለመፍጠር ፍትህ ጉልህ ሚና እንድሚኖረውም በስልጠናው ላይ እንስተዋል::

ፍትህ የበርካታ ተዓምራት ውጤት እንደሆነም በስልጠናው ላይ የተጠቀሰ ሲሆን በዋናነትም ፍትህ ከድህነት ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር እና የተለያየ ቋንቋዎች እየተነጋገርን እንድንግባባ የሚያደርግ ሀይል እንዳለውም ተገልፆል::
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
100K ተከታዮች በፌስቡክ💪 !

በጉዞአችን አብራችሁን ስለሆናችሁ 🇪🇹በሃገር ውስጥም 🌍ከሃገር ውጪም ያላችሁ ተከታዮቻችንን ከልብ እናመሰግናለን 🙏

አብሮነታችሁ ስንቃችን ነው!

ልዩ ልዩ ስልጠናዎችን💡፣ አዳዲስ ሁነቶችን🎉 እና ሌሎች አስተማሪ መረጃዎችን📰 ወደናንተ ማድረሳችንን እንቀጥላለን!

በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ያገኙናል። ይከተሉን!👇

ቲክቶክ: https://www.tiktok.com/@aflex_academy?_t=ZM-8t1gJsnIFgT&_r=1
ዩ ቲዩብ: http://www.youtube.com/@AfricanLeadershipExcellenceAca
ቴሌግራም: https://t.me/afleexac
ዌብሳይት: https://aflexacademy.gov.et
ሊንክድዒን: https://shorturl.at/1Pirn
ኤክስ/ትዊተር: https://x.com/Afleexacademy?s=09