ET Securities
647 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
287 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
የኢትዮጵያ ሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ሥራ አስፈጻሚ ጥላሁን ካሳሁን፣ ገበያው በርካታ ኩባንያዎችን ለመሳብ የሚያገበያያቸውን ምርቶችና አገልግሎቶች ዓይነት ለማብዛት ማቀዱን እንደነገሩት ጠቅሶ የአሜሪካው ሴማፎር ድረገጽ ዘግቧል።

ኩባንያው፣ ወደፊት ለመጀመር ካሰባቸው አማራጮች መካከል እስላሚክ ቦንድ አንዱ እንደኾነ ዋና ሥራ አስፈጻሚው መግለጣቸውንም ዘገባው አመልክቷል።

ትላልቅ የአክሲዮን ማኅበራትንና በግል ይዞታ ሥር የሚገኙን ጨምሮ የግል ኩባንያዎች ገበያውን ይቀላቀላሉ ብለው እንደሚጠብቁ የጠቆሙት ጥላሁን፣ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ውስጥ በትንሹ 90 ኩባንያዎች በገበያው አማካኝነት የአክሲዮን ገበያውን እንዲቀላቀሉ ዓላማ ተይዞ እየተሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል ተብሏል።

በአገሪቱ ከሚገኙ 30 ንግድ ባንኮች መካከል እስካኹን በገበያው የአክሲዮን ድርሻዎቹን ለማገበያየት የተመዘገበው ወጋገን ባንክ ብቻ ነው።

(ዋዜማ
)
ለውጭ ገበያ ከቀረበ ቡና 908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የቡናና ሻይ ባለስልጣን ገለጸ ፡፡

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ኡመር ባለፈው ስድስት ወር ከ204 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለውጭ ገበያ በማቅረብ 908 ሚሊዮን ዶላር  ገቢ መገኘቱን አስታውቀዋል ።

አፈጻጸሙም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት የ8 ሺህ 251 ነጥብ 17 ቶን ወይም 73 በመቶ ብልጫ እንዳለው ነው የተናገሩት ፡፡
ባለስልጣኑ በ2017 በጀት አመት 400 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዱ ይታወሳል ፡፡

ስማርት መረጃ
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ በኑሮ ውድነት አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች
ቢዝነስ ኢንሳይደር በ2025 መጀመሪያ በአፍሪካ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ያስመዘገቡ ሀገራትን ዝርዝር ባወጣበት መረጃው ኢትዮጵያን ቀዳሚ አድርጓታል፡፡
በባለፈው አመት አራተኛ ደረጃ ላይ የነበረችው ኢትዮጵያ በዚህ አመት ወደ አንደኛ ደረጃ ከፍ ስትል  ሞዛምቢክ ፣ ሴኔጋል እና አይቮሪኮስት በዚህኛው አመት መጠነኛ ማሻሻያዎችን አስመዝግበዋል፡፡
በ2025 መጀመሪያ በኑሮ ውድነት ቦትስዋና ፣ ሞዛምቢክ እና አይቪሪኮስት ኢትዮጵን በመከተል ከሁለተኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውን  አል-ዐይን ቢዝነስ ኢንሳይደርን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል ፡፡
Should Ethiopian banks explore securitization, or is it too soon? As we know, a bank has issued thousands of loans mortgages, car loans, or SME credits. Imagine instead of waiting years to collect repayments, what if the bank could package these loans into securities and sell them to investors. This financial innovation is called securitization (It is the process where banks bundle their loans into asset backed securities and sell them to investors).This allows banks to Free up capital for more lending, Reduce risk exposure and improve liquidity. If Ethiopia's financial system matures and proper risk controls are in place, securitization could unlock new liquidity sources and fuel economic growth.

By~ Biniyame Kebede
ባንኮች የሚጠይቁት የማስያዣ ብር ከወትሮው ከፍ ማለት በእቅዱ መሰረት የውጭ ምንዛሬ ማቅረብ እንዳልተቻለ ተገለፀ፡፡
የኢኮኖሚ ማሻሻያው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እንዲኖር ያስቻለ ቢሆንም የውጭ ምንዛሬ መግዛት የሚፈልጉ አካላት በቂ የመግዣ ብር ያለመኖር በሚፈልጉት መጠን  የውጭ ምንዛሬ እንዳያገኙ እንቅፋት መሆኑ ሲገለፅ ቆይቷል፡፡
የኢንደስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የስድስት ወር አፈፃፀም ሪፖርታቸውን በፓርላማ ሲያቀርቡ እንደገለጹት በበጀት አመቱ ግማሽ አመት 468.4 ሚሊየን ዶላር ለአምራች ኢንደስትሪው ለማቅረብ ታቅዶ 369 ሚሊየን ዶላር መቅረብ ተችሏል፡፡ ይህም የእቅዱን 79 በመቶ ነው፡፡
እንደ አቶ መላኩ ገለጻ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦቱ ከእቅዱ አንፃር ዝቅ ያለው ባንኮች የሚጠይቁት የማስያዣ ብር መጠን ከወትሮው ከፍ ማለቱ ነው ብለዋል፡፡
ሆኖም በ6 ወሩ የቀረበው 369 ሚሊየን ዶላር አምና በተመሳሳይ ወቅት ከነበረው 274 ሚሊየን ዶላር የ 35 በመቶ እድገት ነበረው፡፡
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ያስተዋወቀው  የበይነ-መረብ ቀጥታ የግብይት ሥርዓት ተገበያዮች ካሉበት ኾነው መገበያየት የሚያስችል  ነው ተባለ። በዚህም የሀገራችን ምርት ገዢዎች ካሉበት ኾነው እንዲገበያዩ ዕድልን የሚሰጥ ነው ተብሏል፡፡

Etstocks
ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካፒታል ማሳደጊያ የሚውል የ550 ሚሊዮን ዶላር ብድር በፓርላማ ጸደቀ

ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካፒታል ማሳደጊያ የሚውል 550 ሚሊዮን ዶላርን ያካተተ የብድር ስምምነት፤ ዛሬ ሰኞ ጥር 19፤ 2017 በፓርላማ ጸደቀ። የካፒታል ማሳደጊያው፤ ባንኩን “የተሻለ ተወዳዳሪ” እና በቀጠናው መስራት የሚችል “ጠንካራ ባንክ እንዲሆን የሚያስችለው” ነው ተብሏል።

ለመንግስታዊው ባንክ ካፒታል ማሳደጊያ የሚውለው ገንዘብ፤ ዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ለኢትዮጵያ መንግስት የሰጠው 700 ሚሊየን ዶላር ብድር አካል ነው። በዓለም ባንክ ስር የሚገኘው ዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ብድሩን የሰጠው፤ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ስርዓትን ለማጠናከር በማሰብ ነው።

ተጨማሪ፡ https://www.condoaddis.com/250129-1/

LinkedIn | YouTube | X | Facebook | TikTok
በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ተቀማጭ ገንዘብ ሁለት ነጥብ 74 ትሪሊዮን ብር ደረሰ
የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ተቀማጭ ገንዘብ ሁለት ነጥብ 74 ትሪሊዮን ብር ደርሷል።
በቅርቡ የውጭ ባንኮች ሀገር ቤት ገብተው እንዲሠሩ የጸደቀው አዋጅ በዋናነት የውጭ ባለሀብቶች በባንክ መስክ ተሰማርተው ለኢኮኖሚው አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ነው ያሉት አቶ ማሞ፤ የዘርፉን ተወዳዳሪነት በማሻሻል ባንኮች በኢኮኖሚው ውስጥ የሚጫወቱትን ሚና ከፍ ለማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል።
የባንክ ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ማለት የኢትዮጵያ ባንኮች ችግር ላይ ይወድቃሉ ማለት አይደለም። የሀገር ውስጥ ባንኮች አዳዲስ አሠራርና አገልግሎት ተምረው ለኢኮኖሚ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ይጨምራል።  

ተጨማሪ👉 Condoaddis.com/250130-1
የባንኮች ብድር ጉዳይ‼️
ባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የብድር ጣሪያ መስከረም ላይ ይነሳል‼️
ካለፈው ነሀሴ 2015 ዓ.ም. አንስቶ ተጥሎ የነበረው ባንኮች መስጠት የሚችሉት አዲስ ብድር ገደብ ሙሉ ለሙሉ ሊነሳ መሆኑን ተሰምቷል።

የአለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅትን (IMF) መረጃ እንደሚጠቁመው ባንኮች የሚችሉት የብድር መጠን ላይ ተጥሎ የቆየው ጣሪያ በቀጣይ መስከረም ይነሳል።

በነሀሴ 2015ዓም ወደ ስራ የገባው የብድር ጣሪያ ባንኮች አመታዊ የብድር እድገታቸው ከቀደመው የብድር ክምችት  መጠን በ14 በመቶ ብቻ እንዲያድግ የሚያደርግ ነው።

ባለፈው ወር መጨረሻ እድገቱ ወደ 18 በመቶ እንዲሆን በብሄራዊ ባንክ ተወስኖ ነበር። ሆኖም ውሳኔው በባንኮች በአወንታዊ የታየ አልነበረም።

ተጨማሪ 👇
ET Securities
Ethiopia Primes Exchange Market for Foreign Investors Capped at 30%

Ethiopia’s central bank and its nascent capital market authority are preparing tools to allow foreign investment into the country’s exchange, says Brook Taye (PhD), CEO of Ethiopian Investment Holding (EIH).

https://www.condoaddis.com/news/250203-2
የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ባለሥልጣን በሕዝብ የተያያዙ ኩባንያዎች መረጃዎቻዉን በአንድ ወራት ጊዜ ዉስጥ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ ሰጠ

ባለሥልጣኑ ከ50 በላይ ባለአክሲዮኖች ላሏቸውና በሕዝብ የተያዙ ኩባንያዎች መረጃዎቻችን በአንድ ወራት ዉስጥ እንዲያቀርብ ጠይቋል።

እነዚህ ኩባንያዎች የአክሲዮኖቻቸውን ዝርዝር መረጃዎች፣ የባለአክሲዮኖችን ዝርዝር እና የአክሲዮን አወጣጥ ዝርዝሮችን ጨምሮ፣ እስከ መጋቢት 1 ቀን 2017 ድረስ ለባለስልጣኑ እንዲያቀርቡ ይጠበቅባቸዋል።

ይህ እርምጃ ግልጽነትን ለማሳደግ እና ጠንካራ የካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር ያለመ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በቀነ ገደብ መሰረት ትዕዛዙን ያለመፈፀም ቅጣት ሊያስከትል ይችላል ብሏል።

ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከታቸዉ በህዝብ ባለቤትነት የተያዙ ወይም በኢትዮጵያ የንግድ ህግ መሰረት ከህዝብ ገንዘብን በመሰብሰብ የተቋቋሙ ኩባንያዎች መሆናቸው ተገልጿል።

ይህን ተከትሎ ለነባር ዋስትናዎች፣ ላልተጠናቀቁ ሽያጮች እና ለአዳዲስ የአክሲዮን ሽያጮች የምዝገባ መስፈርቶችን በሚመለከት በመረጃው ዉስጥ መካከተት እንዳለባቸው ተመላክቷል።

ተጨማሪ 👇
Etstocks.com
African Top Stock Markets & Their Potential
የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ለጅምር(Start-up) ቀላል ማድረግ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ (ኢሰመገ) የኢትዮጵያን የፋይናንሺያል መልክዓ ምድር ላይ ለውጥ የማድረግ አቅም አለው። ስለዚህ የግብይቱ ህግጋት ከፍተኛ እድገት ለሚያስመዘግቡ ዘርፎች እድሎችን ለመስጠት የተነደፉ መሆን አለባቸው።

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ (ESX) ዝርዝር ውስጥ ምዝገባ ለማድረግ ከሚያስፈልጉት ቁልፍ መስፈርቶች አንዱ እንደሚገልፀው ኩባንያዎች “ከማመልከቻ ቀን ቀደም ብለው ካሉት ሶስት የፋይናንስ ዓመታት ውስጥ ከታክስ በኋላ ትርፍን ለባለ አክሲዮኖች ቢያንስ አንድ ጊዜ ማስታወቅ አለባቸው” ይላል ። ይህ መረጋጋትን የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ እንደ ቴክኖሎጂ፣ ኢ-ኮሜርስ፣ ታዳሽ ሃይል እና ግብርና ያሉ ኢንዱስትሪዎችን የበለጠ ሊያገለግል ይችላል፣ ይህም መልሶ ኢንቨስትመንት ማድረግን ከአጭር ጊዜ ትርፋማነት ይልቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ነው።

ከፍተኛ የእድገት ዘርፎችን ለማበረታታት ሊሆኑ የሚችሉ መንገዶች፡-

▶️ ለጀማሪዎች እና ከፍተኛ ዕድገት ላሳዩ ኩባንያዎች የተለየ ክፍል በማስተዋወቅ ከትርፍ ይልቅ በእድገታቸው ላይ በማተኮር።

▶️ ቀደምት ደረጃ ላይ ያሉ ንግዶች ለመመዝገብ እንዲዘጋጁ ለመርዳት መመሪያ እና ምክር ይስጡ።

▶️ ጠንካራ የስትራቴጂክ አጋሮች ወይም የፈጠራ የንግድ ሞዴሎች ላሏቸው ኩባንያዎች አማራጮችን ያቅርቡ።

ተለዋዋጭ የትርፋማነት መስፈርቶችን መቀበል ገበያውን ያበዛል፣ ፈጠራን ያሳድጋል፣ እና ተለዋዋጭ ኢንዱስትሪዎችን ወደ የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ይስባል።

ሀሳባችሁ ምንድን ነው? እንደ ግብርና እና ቴክኖሎጅ ያሉ እንደገና ኢንቨስት የሚያደርጉ ከባድ ኢንዱስትሪዎችን በተሻለ ሁኔታ ለማስተናገድ ESX መስፈርቶቹን ማበጀት አለበት ይላሉ?
ዩኤንዲፒ ኢትዮጵያ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በመተባበር የፈጠራ ጅምሮች እና አነስተኛ አነስተኛ ድርጅቶች ለክሬዲት ስጋት ዋስትና ፈንድ እንዲያመለክቱ ጥሪውን አቅርቧል።

ተነሳሽነት የብድር ዋስትና ፈንድ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ አዳዲስ እና ነባር ኢንተርፕራይዞችን በአዳዲስ የንግድ ሀሳቦች እና ምርቶች ለመደገፍ ያለመ ነው። ብቁ የሆኑ ንግዶች ይህንን እድል እንዲጠቀሙ ይበረታታሉ። ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም ያመልክቱ።

እዚህ ያመልክቱ

ምንጭ፡ linkupbusiness
@Etstocks
#Quiz

What term describes investing in foreign assets such as stocks and bonds without obtaining significant influence?
Anonymous Quiz
28%
Direct investment
10%
Venture capital
56%
Portfolio investment
5%
Leverage buyout