ET Securities
648 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
287 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
አማራ ባንክ ከታክስ በፊት ከ550 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ።

በ2013 ከ180 ሺህ በላይ ባለ አክሲዮኖች የተመሰረተው አማራ ባንክ ባለፉት አመታት ኪሳራዎች ገጥመውት እንደነበር ይታወሳል።

እየተጠናቀቀ ባለው የፈረንጆቹ 2024 ሰኔ ወር ድረስ ከገባበት ኪሳራ በመውጣት ከ550 ሚሊየን ብር በላይ ጠቅላላ ትርፍ ማስመዝገቡን የባንኩ 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተነግሯል።

ባንኩ ከ801 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞችን አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን በዚህም አጠቃላይ የደንበኞቹን ቁጥር ከአንድ ሚሊየን ስምንት መቶ ሺህ በላይ ለማድረስ መቻሉ ነው የገለፀው።

የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ ጋሻው ደበበ ባለፈው አመት በባንክ ኢንደስትሪው አወንታዊና አሉታዊ ሁኔታዎችን የፈጠሩ አለም አቀፋዊና አገራዊ ክስተቶች ማጋጠማቸውን አስታውሰው የተፈጠሩት ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል በኢኮኖሚው ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩን ጠቁመዋል።

በሀገሪቱም በአንዳንድ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችና አለመረጋጋቶች ተደማምረው አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደራቸውን ተናግረዋል።

አማራ ባንክ በ3ኛው የባለ አክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ 43 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመጨመር የቅርንጫፎቹን ብዛት 310 ማድረሱ የተገለፀ ሲሆን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን የሚሰጡ ቅርንጫፎቹም ብዛት 15 ደርሰዋል።
ስኬት ባንክ ክፍተኛ የፋይናንሻል ዕድገት በማሳየት 1.54 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ አስመዝግቧል። ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ50 በመቶ ብልጫ አለው። ይህ አፈጻጸም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚጠይቀው ዝቅተኛ የካፒታል መስፈርት ብልጫ ያለው የተከፈለ ካፒታል የ25 በመቶ እድገት አሳይቷል፣ አሁን 5.46 ቢሊዮን ብር ደርሷል።

ቁልፍ ውጤቶች
📈 በአጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ 36 በመቶ እድገት፣ 4.9 ቢሊዮን ብር ደርሷል
📈 የብድር ፖርትፎሊዮን አሁን በ9 ቢሊዮን ብር ሰፍቷል
📈 8% የተሰበሰበ ዕዳ ጨምሯል፣ በአጠቃላይ 4.2 ቢሊዮን ብር
📈 አጠቃላይ ገቢው 41% ከፍ ያለ ሲሆን 2.37 ቢሊዮን ብር ሲሆን 75% በወለድ ገቢ

በጠቅላላ ወጪው የ28 በመቶ እድገት ቢኖረውም፣ 828.5 ሚሊዮን ብር ቢደርስም፣ ስኬት ባንክ ጤናማ የትርፍ አስመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ጥር ወር 2017 ዓ.ም ስራ እንደሚጀምር ተገለፀ!!

የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን ኢስማኤል (ዶ/ር) ባለፈው አንድ ዓመት ኩባንያውን እውን ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ገልፀዋል።

ገበያው የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ሽያጭ፣ ግዥ እና ልውውጥ በቋሚነት የሚደረግበት ሲሆን ለመንግሥትና የግሉ ዘርፍ የገንዘብ ምንጭ በመሆን ለምጣኔ ኃብት እድገት ጠቃሚ መሆኑን ገልፀዋል።

መንግስት እና የግሉ ዘርፍ ለሚያከናውኗቸው ኢንቨስትመንቶች ካፒታል ለማሰባሰብ አቅም እንደሚጨምር ይጠበቃል።

በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ አክስዮን የሚሸጡ ኩባንያዎች በየጊዜው የሂሳብ ሁኔታቸው እየተገመገመ ይፋ የሚሆንበት አሰራር መዘርጋቱ ተጠቁሟል።

ይህ ጅምር የኢትዮጵያን አዲስ የካፒታል ገበያ ለማራመድ የተቀናጀ ሲሆን ከኢንተር ባንክ ስራዎች ባሻገር ለንግዶች እና ባለሀብቶች አዳዲስ እድሎችን የሚከፍት ቀልጣፋ የገበያ ቦታ ነው።
Vacancy Announcement for Fresh Graduates
-------------------------------------
Abay Bank S.C. invites interested and qualified applicants for Customer Service Officer (CSO)-II position.

For detail information, please visit our website with the link attached below.
https://www.abaybanksc.com/vacancy-announcement-8/

Follow our social media pages for new vacancy announcements.
ፌስቡክ (http://www.facebook.com/abaybanksharecompany)
ቴሌግራም (https://t.me/abaybanksharecompany)
ትዊተር (https://twitter.com/AbayBank)
ሊንክድኢን (https://www.linkedin.com/company/abaybank)
ዩትዩብ (https://www.youtube.com/@abaybank4665)
ቲክቶክ (https://www.tiktok.com/@abaybank)

Good Luck!p
አንበሳ ኢንሹራንስ በኢንዱስትሪዉ ከፍተኛዉን የአርቦን ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አስታውቋል

በኢንዱስትሪ ደረጃ በበጀት ዓመቱ በጠቅላላ መድን ዘርፉ ብር 28.3 ቢሊዮን አረቦን የተሰበሰበ ሲሆን፤ የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ ደግሞ ብር 1.178 ቢሊዮን የእረቦን ገቢ በማስመዝገብ የገበያ ድርሻውን 4.38 በመቶ ማድረስ መቻሉን ገልጿል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከጠቅላላ መድን ዘርፍ ብር 1.15 ቢሊዮን እና ከህይወትና ጤና መድን ዘርፍ 23.1 ሚሊዩን በድምሩ ብር 1.173 ቢሊዮን የአረቦን ገቢ በማስመዝገብና ግብርና ህጋዊ መጠባበቂያ ተቀንሶ የተገኘው የተጣራ ትርፍ 185.3 ሚሊዮን ብር መሆኑን በሪፖርቱ ጠቁሟል።

ይህ የተባለው ኩባንያው ባካሄደው 17ኛ የባለ-አክሲዮኖች መደበኛ ጉባኤ ላይ ነዉ ። በዚህም በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አንበሳ ኢንሹራንስ አጠቃላይ ሃብት ብር 2.78 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃጸር የብር 705.9 ሚሊዮን ወይም 33.9 በመቶ እድገት ማስመዝገብ ችሏል ብሏል።
የኢትዮጵያ ሠነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያሞሮኮ አክሲዮን ገበያ ጋር የትብብር ስምምነት ፈጸመ!!

የኢትዮጵያ ሠነደ ሙዓለ-ንዋዮች ገበያ ከሞሮኮ ካዛብላንካ አክሲዮን ገበያ ጋር ስትራቴጂካዊ የትብብር ስምምነት መፈራረሙ ተገለፀ።

አላማውም በዋናነት በእውቀት ማጋራት እና ተግባራዊ ድጋፍ መስጠት ላይ የሚያተኩር መሆኑ ተገልጿል።

ደኅንነቱን የጠበቀ እና ቀልጣፋ የንግድ ሥርዓት እንዲፈጥር የቴክኖሎጂ ማዕቀፍን፣ የአሠራር አቅም እና የአደጋ አሥተዳደር አቅምን የሚያጎለብቱ ሥራዎች ለመስራት ያስችላል ተብሏል።

በተጨማሪም ኢንቨስትመንትን እና ዘላቂ እድገትን ለማበረታታት እንደሚያግዝ ተገልጿል፡።
ከታክስ በፊት 930 ሚሊየን ብር ትርፍ አተረፍኩ! – ቡና ባንክ
ከተመሰረተ 15 አመት የሞላው ባንኩ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ትርፉ በ4መቶ29 ሚሊየን ብር ቅናሽ ማሳየቱንም አስታውቋል።

በበጀት አመቱ እንደ አገር የተከሰተው ከፍተኛ የዋጋ ንረት ፣ የውጭ ምንዛሬ ዕጥረት ፣ ተደራራቢ የሆኑ የተቆጣጣሪ አካላት መመሪያዎች መውጣት እንዲሁም ተግባራዊ መሆን ለባንኩ ዘርፍ አስቸጋሪ ሁኔታ እንደነበር ተገልጿል።

የባንኩ የቦርድ ሊቀመንበር አምባሳደር አለማየሁ ሰዋገኝ፤ እነዚህ ችግሮች የባንኮችን የማበደር ብቻ ሳይሆን ተቀማጭ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ ላይም ተፅዕኖ ማሳደራቸውን ተናግረዋል።

ነገርግን ባንኩ ላስመዘገበው የሀብት ዕድገት የተሰጡ የብድር አቅርቦቶች ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙም ገልጸዋል።

በዚህም የባንኩ አጠቃላይ የሀብት መጠን ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ8.14 ቢሊየን ብር ዕድገት በማሳየት 54.53 ቢሊየን ብር መድረሱን አስታውቀዋል።

በበጀት አመቱ የተመዘገበው የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ549.2 ሚሊየን ብር ጭማሪ በማሳየት ወደ ብር 4.83 ቢሊየን ማደግ ችሏል ነው የተባለው።

ባንኩ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የተቀመጠውን ዝቅተኛ የካፒታል መጠን እንዲሁም የተከፈለ ካፒታል መጠን ከተቀመጠው ጊዜ ቀደም ብሎ ለማሟላት ዕቅድ አውጥቶ እየሰራ መሆኑም ተገልጿል።

ከዕቅዱ አንፃር ዝቅ ያለ ቢሆንም 4መቶ90 ሚሊየን 1መቶ16 ሺህ ብር ለባንኩ ባለአክሲዮኖች በትርፍ ክፍያ እንዲከፋፈል ውሳኔ መደረሱንም ገልፀዋል።

ባንኩ በያዝነው በጀት አመት ሩብ አመት መጀመሪያ ላይ ከዕቅዱ በላይ 1.2 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንም ሰምተናል።

ቡና ባንክ የባለአክሲዮኖች 15ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛል።
ገቢዎች ቢሮ ድርጅቶች ሊኖራቸው የሚገባውን የሰራተኞችን ቁጥር እና ሊከፈል የሚገባውን ዝቅተኛ ደመወዝ ወለል ወሰነ!

በዚህ ውሳኔ በሆቴሎች እና ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ አሰሪዎች ለሰራተኞቻቸው የደሞዝ ጭማሪ እንዲያደርጉ የሚያስገድድ ተመን ይሆናል።

ከአስተናጋጅ፣ ጥበቃና የፅዳት ሙያ ውጭ ላሉ ሰራተኞች ትንሹ የሚከፍሉት ደመወዝ 5,000 ብር ሆኖ ተተምኗል።

በዚህም የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በግብር  ሂደት  ውስጥ የሚፈጠሩ ማጭበርበሮችን ለመቀነስ ዓላማው ያደረገ ለሆቴሎች፣ ለስጋ ቤቶች፣ ለመጠጥ ቤቶች እና ለተለያዩ የተመረጡ የንግድ ዘርፎች ለሰራተኞቻቸው አነስተኛ የደመወዝ ወለል እና የሰራተኞችን ብዛት የሚተምን ተመን ይፋ አድርጓል።

Source: theethiopianeconomistview
@Etstocks
የውጭ ሀገራት ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ የሚፈቅደው የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ መርምሮ እንደሚያፀድቅ ተገለፀ፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ከተወያየ በኃላ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡

በነገው መደበኛ ስብሰባ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የባንክ ስራ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ለምክር ቤቱ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ሰኔ 18 ቀን ፣ 2ዐ16 ዓ/ም ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የተመራ ሲሆን ምክር ቤቱ፤ ቋሚ ኮሚቴው የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ሲጸድቅ የውጭ ባንኮች በሃገር ውስጥ ተቀጥላ ወይም ሰብሲዲያሪ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲከፍቱ ከመፍቀዱ በተጨማሪም የሀገር ውስጥ ባንኮችን ድርሻ መግዛት እንዲችሉ የሚፈቅድም ነው፡፡

ከዚህም ባሻገር የውጭ ባንኮች ቅርንጫፎቻቸውን እንዲከፍቱ፣ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገራት ዜጎችም በባንኮቻቸው የሥራ እድልን ማግኘትና የቦርድ ሊቀመንበር አባላት እንዲሆኑ መንገዱን የሚያቀናላቸው ነው ይኸው ረቂቅ አዋጅ፡፡

መንግስትም የአዋጁን መጽደቅ ተከትሎ ለአምስት የውጭ ባንኮች ፈቃድ ለመስጠት ያስችለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ገበያ ለመሥራት ፍላጎት ካሳዩ የውጭ ባንኮች ውስጥ የኬንያው ኬሲቢ እንዲሁም ስታንዳርድ ባንኮች ይጠቀሳሉ፡፡
ኦሮሚያ ባንክ አጠቃላይ ሀብቱ ከ 68 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አስታወቀ

ኦሮሚያ ባንክ የተከፈለ ካፒታል 6.5 ቢሊየን ብር መድረሱን ያስታወቀ ሲሆን አጠቃላይ ሀብቱ ደግሞ ወደ 68 ቢሊዮን ብር ማደጉን በሪፖርቱ ገልጿል።

ዘንድሮ አለም አቀፍ እና ሀገራዊ ተግዳሮቶች የባንኪንግ ዘርፉን በተለያየ መልኩ ቢፈትኑትም፣ ኦሮሚያ በንክ ይህን መቋቋም መቻሉን ነዉ በሪፖርቱ የገለፀዉ። ይህን ተከትሎ በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት ከወለድ ነፃ የባንክ ገቢ 56.4 ቢሊዮን ብር መድረጉን አመልከቷል ።

15ኛ የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት ያደረገው ባንኩ ኦሮዲጂታል የተሰኘ ዲጂታል የባንክ አገልግሎት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ2.9 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራት መቻሉን አስታዉቋል።

በዚህም አጠቃላይ የባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 3.7 ሚሊዮን ከባለፈው ተመሳሳይ የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ157 % እድገት አሳይቷል ብሏል።
የኢትዮጵያ ፓርላማ የውጭ ባንኮች በኢትዮጵያ የሚፈቅደውን ታሪካዊ አዋጅ አፀደቀ።

Read more