ET Securities
646 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
286 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
ባለፉት 10 ዓመታት ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ (Gross Domestic Product per capital) ከፍተኛ ዕድገት ያስመዘገቡ 10 ምርጥ የአፍሪካ ሀገራት

የነፍስ ወከፍ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ብዙውን ጊዜ ከግለሰብ ገቢ እና ፍጆታ መጨመር ጋር ይዛመዳል። ይህ የሚያሳየው በአማካይ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች ካለፈው አመት በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘታቸውን ነው።

ሌላው የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ ገፅታ ደግሞ የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ የግዢ ሃይል እኩልነት(Purchasing power parity) ሲሆን ይህም በእያንዳንዱ ሰው አማካይ የኢኮኖሚ ውጤትን የሚያመለክት እና በአገሮች ያለውን የኑሮ ውድነት ታሳቢ ያደረገ ነው።

መረጃ ምንጭ - World Economics
አሜሪካ በሬሚታንስ ላይ ታክስ የመጣል ዕቅድ እንዳላት ተገለፀ።

በዚህ ሳምንት ታክስን በተመለከተ በቀረበው ዕቅድ ላይ በአሜሪካ ከሚኖሩ ሰዎች ወደ ሌላ ሃገር የሚደረጉ ክፍያዎች (ሬሚታንስ) ላይ የ5 በመቶ ተብሎ ታክስ ለመጣል ታቅዷል ተብሏል።

በታክሱ አብዛኞቹ በአሜሪካ ዜጎች የሚፈፀሙ ዝውውሮች ባይካተቱም በሌሎች ሀገር ዜጎች እና አንዳንድ በአሜሪካ ዜጎች የሚላኩ ገንዘቦች ግን ታክሱ ይፈፀምባቸዋል።

በ2023 ብቻ በአሜሪካ የሚኖሩ ሰዎች ከ93 ቢሊየን ዶላር በላይ ሬሚታንስ ወደ ሀገሮቻቸው የላኩ ስለመሆኑ የዓለም ባንክ ሪፖርት ያሳያል።

እንደ ኬንያ፣ ጋና እና ናይጄሪያ ያሉ ብዙ ሬሚታንስ ተቀባይ የሆኑ አፍሪካውያንም በጉዳዩ ስጋት ገብቷቸዋል።

በእነዚህ ሀገራት ሬሚታንስ ከሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዝ ሲሆን ከሬሚታንስ የሚገኘው ገንዘብ አንዳንዴ በእርዳታ እና ኢንቨስትመንት መልኩ ከሚያገኙት ገንዘብ ጭምር እንደሚበልጥም ተነግሯል።

ኢትዮጵያ በ2023/24 ከሬሚታንስ 6 ቢሊየን ዶላር ያገኘች ሲሆን ታክሱ ተግባራዊ ከሆነ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታት ይሆናል።

Source: tikvahethmagazine
@Etstocks
Ethiopian Securities Exchange (ESX) and IFC - International Finance Corporation ) have made an agreement and officially launched the Ethiopia Money Market Capacity Building Project. The initiative is expected to play a pivotal role in shaping the future of Ethiopia’s capital markets by investing in critical human capital and institutional development.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዛሬ ጀምሮ የወሰዳቸው የለውጥ እርምጃዎች ……

1. ለአስመጪዎች የቅድመ ክፍያ (አድቫንስ ፐይመንት) መጠንን ከ5 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወደ 50 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ከፍ ተደርጓል።

2. ለውጭ ሀገር ተጓዦች የሚፈቀደውን የውጭ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ መጠን 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር፣ ለንግድ ሥራ መንገደኞች ደግሞ 15 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ሆኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሂሳብ ያላቸው ግለሰቦች ከሂሳባቸው ላይ በካርድ መጠቀም የሚችሉት የውጭ ምንዛሪ መጠን ከ10 በመቶ ወደ 20 በመቶ ከፍ እንዲል ሆኗል፡፡

3. የባንኮችን የውጭ ምንዛሪ ክፍያዎችን ሥርዓት ለማስያዝ በማሰብ ባንኮች ከገቢ ንግድ፣ ከአገልግሎት ክፍያ ወይም ከጥሬ ገንዘብ ጋር በተያያዘ ለውጭ ምንዛሪ አገልግሎት የሚያስከፍሏቸው ማናቸውም አስተዳደራዊ ወጪዎችና ክፍያዎች ከግንቦት 18፣ 2017 ጀምሮ ከ4 በመቶ እንዳይበልጡ ተወስኗል፡፡
ብሔራዊ ባንክ ሸቀጦችን ከውጭ ለማስገባት የሚከፈለው የቅድመ ክፍያ መጠን ወደ 50 ሺህ ዶላር ከፍ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያ ሥርዓትን ለማሻሻል ያለመ አዲስ የለውጥ እርምጃዎችን ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል።

ይህን ተከትሎ ከተወሰዱ እርምጃዎች ዉስጥ ከውጭ ለማስገባት ሊከፈል የሚችለው የቅድመ ክፍያ መጠን ከ5 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወደ 50 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ከፍ  እንዲል ማድረጉን አስታውቋል።

ባለፈው ሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም. ስራ ላይ የዋለው አዲሱ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ስርዓት በውጭ ምንዛሪ ገበያ እና በሀገሪቱ የውጭ ክፍያ ሚዛን ላይ ከፍተኛ መሻሻል ማምጣቱን ባንኩ አስታዉሷል።

የውጭ ምንዛሪ ገበያ ማሻሻያዎች በተመለከተ ብሔራዊ ባንክ ባወጣዉ መግለጫ ላይ ለግል ተጓዦች የሚፈቀደው የውጭ ምንዛሪ በጥሬ ገንዘብ ወደ 10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ሲጨምር፣ ለንግድ ስራ መንገደኞች ደግሞ 15 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ደርሷል።

በተጨማሪም የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሂሳብ ያላቸው ግለሰቦች ከሂሳባቸው በካርድ መጠቀም የሚችሉት የውጭ ምንዛሪ መጠን ከ10 በመቶ ወደ 20 በመቶ ከፍ ብሏል።
ብሔራዊ ባንክ ስድስተኛውን የዉጪ ምንዛሪ ጨረታ በ50 ሚሊዮን ዶላር ሊያካሂድ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማረጋጋትና የውጭ መረጋጋትን ለመቆጣጠር ያለመ 50 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ዛሬ ሐሙስ እንደሚያካሂድ አስታውቋል።

ይህ ጨረታ ለንግድ ባንኮች የቀረበ ሲሆን፣ ባንኩ በየሁለት ሳምንቱ ከሚያካሂዳቸው ተከታታይ ጨረታዎች ስድስተኛው ነው።

ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደው አምስተኛው ዙር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር የመገበያያ ዋጋ 132.96 ብር ሆኖ ተመዝግቦ ነበር። በዚያ ጨረታ ላይ ባንኩ 60 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ያቀረበ ሲሆን፣ በጠቅላላው 16 የንግድ ባንኮች የጠየቁትን የውጭ ምንዛሪ ድልድል ማግኘት ችለው እንደነበር ይታወቃል።

Source: capitalethiopia
@Etsrocks
NBE Foreign Exchange Auction: Weighted Average Rate at 133.1715 Birr per USD

The National Bank of Ethiopia (NBE) today announced the results of its latest Foreign Exchange Auction.

According to the NBE's official announcement, the weighted average rate of all successful bids in the auction was Birr 133.1715 per US Dollar showing inclement from last auction result of Birr 132.9643 per US Dollar.

The auction saw a total of 14 banks participate, submitting demands for foreign exchange allocations.

The National Bank of Ethiopia also indicated its schedule for future foreign exchange auctions. The next Foreign Exchange Auction is planned to be held in two weeks.
#Free_Training

Deloitte, in collaboration with the Ethiopian Securities Exchange and the Ethiopian Capital Markets Authority, presents this crucial masterclass designed to equip you with unparalleled insight into navigating the landscape of Initial Public Offerings and Mergers & Acquisitions in Ethiopia.​
https://www.deloitte.com/et/en/events/deloitte-academy-events/ethiopia-ipo-and-m-a-masterclass-2025.html
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ143 ቀናት በኋላ የምንዛሬ ዋጋ በ4 ብር አሻሻለ!

ከጥር 1 ጀምሮ አንድ ዶላር በ124 ብር ገዝቶ በ126 ይሸጥ የነበረው ባንኩ ከ143 ቀናት (ከ January 1 እስከ May 24) በኋላ ዛሬ 4 ብር ጨምሮ አንድ ዶላር በ128 ብር ገዝቶ በ130 ብር መሸጥ ጀምሯል!
የኢንሹራንስ ዘርፉ ለዉጪ ባለሃብቶች ክፍት እንዲሆን የሚያስችል አዲስ አዋጅ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተነገረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የኢንሹራንስ ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት የሚያደርግ አዲስ አዋጅ በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታውቋል።

ውሳኔው የኢትዮጵያን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ለማዘመን እየተደረገ ካለው ሰፊ ጥረት አንዱ አካል ነው ተብሏል።

ይህ የተገለጸው 51ኛው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ተቋም ዓመታዊ ኮንፈረንስ እና አጠቃላይ ስብሰባ በአዲስ አበባ በተጀመረበት ወቅት ነው።

የብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እንደተናገሩት፣ የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባንኮች ክፍት ያደረገው አዲሱ አዋጅ "የፋይናንስ ዘርፋችንን ለማዘመን በተደረገው ጥረት ትልቅ ምዕራፍ" እንደሆነ ተደርጎ ይታያል። በዚህ ስኬት ላይ በመመስረት፣ ባንኩ አሁን ደግሞ ትኩረቱን የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪውን በማሻሻል ላይ አድርጓል።
The 51st African Insurance Organization (AIO) Conference and Annual General Assembly is currently taking place in Addis Ababa, Ethiopia[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://www.ena.et/web/eng/w/eng_6662553?citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054 "1"). The summit, running from May 26 to May 28, 2025, brings together delegates from 93 countries, including policymakers, regulators, insurers, and industry leaders[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://www.plenglish.com/news/2025/05/26/conference-of-the-african-insurance-organization-meets-in-ethiopia/?citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054 "2").

### Key Highlights:
- Theme: *Balancing the Books: Africa’s Debt Problem - Why Does Country Debt Impact Insurers?*[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://www.ena.et/web/eng/w/eng_6662553?citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054 "1")
- Ethiopia’s Deputy Prime Minister Temesgen Tiruneh emphasized that insurance must evolve into a pillar of economic development, supporting families, credit access, and investment[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://www.ena.et/web/eng/w/eng_6662553?citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054 "1").
- National Bank of Ethiopia Governor Mamo Mihretu highlighted the impact of sovereign debt on the insurance industry, stressing the need for strong international coordination[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://www.ena.et/web/eng/w/eng_6664887?citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054 "3").
- Artificial Intelligence (AI) in Insurance: AI-driven insurers are using technology to offer tailored solutions, dynamically adjusting policies and pricing based on user data[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://www.ena.et/web/eng/w/eng_6664887?citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054 "3").
- Regulatory Reforms: Ethiopia is establishing an independent insurance regulatory authority to modernize the sector and attract investment[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://press.et/herald/?p=116096&citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054 "4").

This summit is a major step toward strengthening Africa’s insurance industry and addressing economic challenges. If you’d like more details, you can check out the full coverage [here](https://www.ena.et/web/eng/w/eng_6662553).
ET Securities pinned «The 51st African Insurance Organization (AIO) Conference and Annual General Assembly is currently taking place in Addis Ababa, Ethiopia[43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054](https://www.ena.et/web/eng/w/eng_6662553?citationMarker=43dcd9a7-70db-4a1f-b0ae-981daa162054…»