የኢትዮጵያ ሰነድ ሙዓለ ንዋይዮች ገበያ ደንበኞች የኢንቨስትመንት ሂሳብ እንዲከፍቱ ጥሪ አቀረበ።
የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ ገበያው በተፈለገው መንገድ እየሄደ ሲሆን፣ ባንኮች እና ሌሎች ድርጅቶችም በገበያው እየተመዘገቡ ነው።
ይህ ጥሪ የቀረበው የገዳ ባንክ በገበያው ላይ ሦስተኛው ተመዝጋቢ ድርጅት በሆነበት ወቅት ነው። ባንኩ የደንበኛ ሳቢ መግለጫውን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ካስመዘገበ በኋላ በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ላይ ቀርቧል።
ሸገር እንደዘገበዉ የገዳ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ቡልቶ፣ ባንኩ በዚህ ገበያ በመመዝገቡ ባለአክሲዮኖች ሰፊ የገንዘብ ተደራሽነት እንዲኖራቸው ያደርጋል ብለዋል። በESX የተመዘገቡት ድርጅቶች ወጋገን ባንክ እና ገዳ ባንክ መሆን ችለዋል።
የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ ገበያው በተፈለገው መንገድ እየሄደ ሲሆን፣ ባንኮች እና ሌሎች ድርጅቶችም በገበያው እየተመዘገቡ ነው።
ይህ ጥሪ የቀረበው የገዳ ባንክ በገበያው ላይ ሦስተኛው ተመዝጋቢ ድርጅት በሆነበት ወቅት ነው። ባንኩ የደንበኛ ሳቢ መግለጫውን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ካስመዘገበ በኋላ በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ላይ ቀርቧል።
ሸገር እንደዘገበዉ የገዳ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ቡልቶ፣ ባንኩ በዚህ ገበያ በመመዝገቡ ባለአክሲዮኖች ሰፊ የገንዘብ ተደራሽነት እንዲኖራቸው ያደርጋል ብለዋል። በESX የተመዘገቡት ድርጅቶች ወጋገን ባንክ እና ገዳ ባንክ መሆን ችለዋል።