የስቃዩን መሰቀል ተሸክማ እስከ ቀራኒዮ የተጓዘችው #Regina_Abelt
ስለ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጀግንነት እልፎች ዛሬ ከአረፈ በኋላ ሲያወድሱ …በመከራው ግዜ ግን የስቃዩን መሰቀል ተሸክማ እስከ ቀራኒዮ የተጓዘችው ብቸኛ ጀግኒት ሴት #Regina_Abelt ናት፡
ጀርመናዊቷ የዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ባለቤት የቤተ መንግስትን ህይወት ብቻ ሳይሆን የደሳሳ ጎጆ ኑሮንም አብራ ተጋርታለች።
ሳናወድሳትና ሳናመሰግናት እነሆ ባለቤቷን ቀብራ ተመልሳለች፡፡
Regina Abelt (born 1954) was the First Lady of Ethiopia from 1995 until 2001, and a German citizen. She is the first person to hold such a government position while being a citizen of a different country.
“እኔ የብሄርን እንቁላል ሰብሬ ወጥቻለሁ” ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ
የኢትዮጵያን ፖለቲካ አሳምረው ያውቁታል። ከ60ዎቹ የተማሪዎች እንቅስቃሴ እስከ «ቅንጅት» በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪም ተሳትፈዋል። ጀርመን ከገቡ ጀምሮ ለ17 ዓመት ያህል ፅዋ ያልጠጡበት የፖለቲካ ማህበር የለም። በአውሮፓ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበርንና የኦሮሞ ፖለቲካ ድርጅቶችን ያውቋቸዋል። እነመኢሶን፣ ኢህአፓን፣ ሻዕቢያን፣ ኦነግን፣ ህወሃትንና ሌሎችን የተዋወቁት በስደት ላይ እያሉ ነው። ከአብዛኞቹም ጋር የፖለቲካ ጠበል ጻዲቅ ተቃምሰዋል።
አዳዲስ የፖለቲካ ማህበራትና የአርነት ድርጅቶችን አዋልደዋል። አያሌ የፖለቲካ ዕድሮች ሲመሰረቱም ሲፈርሱም ታዝበዋል። አንዳንዶቹ መሠረታቸው ሲጣል የፖለቲካ ሲሚንቶና አሸዋ አቀብለዋል። ሆኖም ከየትኛውም የፖለቲካ ስብስብ ጅምር እንጂ ውጤት አላዩም። ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ነጋሶ ለኦሮሞ ህዝብ መብትና ነጻነት የሚታገሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ለመመስረት ታትረዋል። ሆኖም የፖለቲካው አበባ ሲጽደቅ እንጂ ሲደርቅ አሻፈረኝ አሉ። እናም አንጀት የሚያርስ የፖለቲካ ድርጅት ባህር ማዶም ሆነ አገር ቤት መጥፋቱ እያብሰከስካቸው ቁዘማ ያዙ።
ተስፋ ቆርጠው ግን ለፖለቲካው ጀርባቸውን አልሰጡም። ምክንያቱ ደግሞ ሌላ ሳይሆን ከተስፋ መቁረጥ ጋር ስለማይተዋወቁ ብቻ ነው። እናም ለአገራቸው አንድ ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ ለማበርከት ደጅ ደጁን ሲመለከቱ ኢህአዴግን እመንገዳቸው ላይ አገኙት። አጥንተውት እና አስጠንተውት ተጠጉት። ለዓመታት ከኖሩበት ባህር ማዶ ጓዛቸውን ጠቅልለው አገራቸው ገቡና ቃል ኪዳን አሰሩ።
ከኢህአዴግ ጋር 10 ዓመት የሚያህል የፖለቲካ መንገድ ተጉዘዋል። የለውጥን ተስፋ ሰንቀው በኦህዴድ አመራርነት፣ በሚኒስትርነትና በርዕሰ ብሔርነት በጽናት አገልግለዋል። ነጋሶ የዓላማ ሰው ናቸው፤ ላመኑበት በጽናት የሚቆሙ፡፡ ነገር ግን ለቃሉ የሚታመን የፖለቲካ ድርጅት በባትሪ ፈልገው አጡ፡፡ የሚገጥሟቸው የፖለቲካ ድርጅቶች ሃሳባቸውንና አቋማቸውን እየቀያየሩ መከራቸውን አበሏቸው፡፡ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ በኩል ሶሻሊዝምን እንገነባለን ያላቸው ኢህአዴግ እንኳን የምመራው በነጭ ካፒታሊዝም ነው ብሎ እምነታቸውን አፈረሰባቸው ፤የዓለም ተጨባጭ ሁኔታ ስላልፈቀደ ለጊዜው ሶሻሊዝምን መሳቢያ ውስጥ ከተነዋል ሲባሉ «መታለላቸው» አሳዘናቸው፡፡ ሊጠይቁ እና ሊሞግቱ ሞከሩ፤ ውጤቱ ውግዘት ሆነባቸው::
እኚህ አንጋፋ ፖለቲከኛ የህይወት ታሪክ ውስጥ የራሳቸውን ነጠላ የፖለቲካ መንገድ ብቻ አይደለም የምናየው፡፡ ከሞላ ጎደል የዘመኖቻቸውን የፖለቲካ ጎዳናም ተንሰላስሎ እናገኘዋለን፡፡
ለአገር የኖሩ የአገር አድባር የሆኑት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ በስኳር ህመም እና በደም ግፊት ምክንያት በሳኡዲ አረቢያ በአሜሪካ እና በመጨረሻም በጀርመን ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በ75 ዓመታቸው ሕይወታቸው አልፏል። እኛም ዛሬ እኚህን ታላቅ የአገር ባለውለታ በ«ሕይወት እንዲህ ናት» አምዳችን ልንዘክራቸውና የሕይወት ጉዞአቸውን ልናወሳ ወደናል፤ መልካም ንባብ!
ልጅነት
በደምቢ ዶሎ መሀል ከተማ በቤተል ቤተክርስቲያን መንደር ልዩ ስሙ ከቾ በምትባል አካባቢ ነው ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የፈለቁት። ከወላጅ እናታቸው ዲንሴ ሾሊ እና ከቄስ ጊዳዳ ሶለን ጳጉሜን 5 ቀን በ1935 ዓ.ም ተወለዱ:: ነጋሶ ልጅነታቸውን ያሳለፉት በምቾት አይደለም፤ለእግራቸው ሸራ ጫማ አያውቁም። ለትምህርት ሲሉም ከወላጆቻቸው ቤት ወጥተው በየዘመድ አዝማዱ ተንከራተዋል።
የነጋሶ የልጅነት ሕይወት በችግር የተሞላ ብቻ አልነበረም፡፡ እርሳቸውም «ልጅነቴ ማር እና ወተቴ»ን አሳምረው ያውቁታል:: ጣፋጭ የልጅነት ትዝታም ነበራቸው፤ «ጢሎ» የምትባለውን ጥቁሯን ላማቸውን አይረሷትም፡፡ ሌላው የልጅነት ሕይታቸውን «ዳንዲ የነጋሶ መንገድ» በሚለው መጽሐፍ ላይ ስለ ገጠመኛቸው ሲናገሩ «በኦሮሞ ባህል እናት ልጇን ከአንድ ዓመት ተኩል እስከ ሁለት ዓመት የምታጠባ ቢሆንም እኔ ግን ቶሎ ጡት አልተውኩም ነበር፡፡ እናቴ ሲጨንቃቸው ጡታቸውን የሚመር የግራዋ ቅጠል ጨምቀው ቀቡት፤ አሁንም አልተው አልኩኝ፡፡ ብዙ ቆይቼ ነው ያቆምኩት፡፡»ጡት መጥባት እንዳቆሙ አጎታቸው በማረፋቸው እና አጎታቸው ወንድ ልጅ ስለሌላቸው በባህሉ መሰረት ቤተሰብ ደግሞ የሚወከለው በወንድ ነው፡፡ ለዚህም ነው ዶክተር ነጋሶ ለአጎታቸው ቤተሰብ ተሰጡ፡፡
የትምህርት ሕይወት
ትምህርት ቤት ሳይገቡ ሀሙስ ሀሙስ ሚሲዮናውያን የአካባቢውን ልጆች ይጋብዞቸው ነበር፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፣ ፀሎት እና መዝሙርም ያስጠኗቸዋል፡፡ ስለ ትምህርት አጀማመራቸው ዶክተር ነጋሶ ሲያስረዱ «መጀመሪያ ሚሲዮን ትምህርት ቤት አልገባሁም፡፡ ደምቢ ዶሎ የቤተል ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ተቋቁሞ ስለነበር ስድስት ዓመት ሲሞላኝ እዚያ ገባሁ፡፡ በትምህርት ቤታችን የጉራጌ፣ የአማራ፣ ትግሬ፣ የኤርትራውያንና ሌሎችም ልጆች ነበሩ፤ ልዩነት አልነበረም፡፡»
ሀ ሁ… ያስተማሯቸው አባታቸው ናቸው:: አባታቸው ዶክተር ነጋሶን ብቻ ሳይሆን የልጅነት ጓደኞቻቸውን እነደገመኝ ዳቃ፣ ክፍሌ ወሰኑን ፊደል አስተምረዋቸዋል፡፡ ዶሎ የቤተል ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት እየተማሩ ባሉበት ወቅት ጃነሆይ ይመጣሉ ተብለው ተሰልፈው ወደ አውራጃ ጽሕፈት ቤት ሄዱ፡፡ ሁኔታውን ሲያስረዱ ‘ኃይለሥላሴ ድል አድራጊው ንጉሣችን…’ እያልን በስሜት እየዘመርን ከስድስት ሰዓት በፊት ደረስን፡፡ ንጉሡ ግን ሳይመጡ ቀሩ፤ እኛም እግራችን እስኪቃጠል ድረስ ከጠበቅናቸው በኋላ ወደ ቤታችሁ ሂዱ ስለተባልን ንጉሡን ሳናገኝ ተመለስን።»
ትምህርት ቤቱ ሲዘጋ የእርሳቸውም ትምህርት አብሮ ተዘግቶ እንደነበር በዛው መጽሐፍ ላይ ገልጸዋል። ከወራት በኋላ ግን ብርሃን ኢየሱስ የሚባል ትምህርት ቤት ገቡ፡፡ በዛም ሁለተኛ ክፍል እየተማሩ ሳለ አባታቸው ከአዲስ አበባ ተመልሰው መጡ፡፡ በወቅቱ ሚዛን ተፈሪ የአሜሪካን ሚሲዮኖች ሥራ ጀምረው ስለነበር ቤተክርስቲያን ለማቋቋም ቄስ ፈልገው ለቤተክርስትያኒቱ ደብዳቤ ጽፈው «ቄስ ላኩልን» አሉ። በዚህ አጋጣሚ አባታቸው ወደ ማጂ ዞን የድሮ ጊሜራ ዞን ዋና ከተማ ሚዛን ተፈሪ እንዲሄዱ ተመረጡ፡፡
ሚዛን ተፈሪ የቤንች ማጂ ዋና ከተማ ነበረች፤ አማርኛ ይነገርባታል። እናም ከአባታቸው ጋር ወደዛ ያቀኑት ዶክተር ነጋሶ በቆይታቸው አማርኛ እየለመዱ መጡ፡፡ ከቋንቋው ጋር ብቻ ሳይሆን የቤንችንና ከፊቾን ባህል ተላመዱ፡ ፡ከሌሎችም ጋር መግባባት ጀመሩ፡፡ ባህል፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት አኗኗር ማህበረሰብን የሚያስተሳስር ገመድ ነውና በዚህ መካከል ተሳስረው ይኖሩ ነበር፤ መለያየት አልነበረም፡፡
ስለ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጀግንነት እልፎች ዛሬ ከአረፈ በኋላ ሲያወድሱ …በመከራው ግዜ ግን የስቃዩን መሰቀል ተሸክማ እስከ ቀራኒዮ የተጓዘችው ብቸኛ ጀግኒት ሴት #Regina_Abelt ናት፡
ጀርመናዊቷ የዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ባለቤት የቤተ መንግስትን ህይወት ብቻ ሳይሆን የደሳሳ ጎጆ ኑሮንም አብራ ተጋርታለች።
ሳናወድሳትና ሳናመሰግናት እነሆ ባለቤቷን ቀብራ ተመልሳለች፡፡
Regina Abelt (born 1954) was the First Lady of Ethiopia from 1995 until 2001, and a German citizen. She is the first person to hold such a government position while being a citizen of a different country.
“እኔ የብሄርን እንቁላል ሰብሬ ወጥቻለሁ” ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ
የኢትዮጵያን ፖለቲካ አሳምረው ያውቁታል። ከ60ዎቹ የተማሪዎች እንቅስቃሴ እስከ «ቅንጅት» በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪም ተሳትፈዋል። ጀርመን ከገቡ ጀምሮ ለ17 ዓመት ያህል ፅዋ ያልጠጡበት የፖለቲካ ማህበር የለም። በአውሮፓ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበርንና የኦሮሞ ፖለቲካ ድርጅቶችን ያውቋቸዋል። እነመኢሶን፣ ኢህአፓን፣ ሻዕቢያን፣ ኦነግን፣ ህወሃትንና ሌሎችን የተዋወቁት በስደት ላይ እያሉ ነው። ከአብዛኞቹም ጋር የፖለቲካ ጠበል ጻዲቅ ተቃምሰዋል።
አዳዲስ የፖለቲካ ማህበራትና የአርነት ድርጅቶችን አዋልደዋል። አያሌ የፖለቲካ ዕድሮች ሲመሰረቱም ሲፈርሱም ታዝበዋል። አንዳንዶቹ መሠረታቸው ሲጣል የፖለቲካ ሲሚንቶና አሸዋ አቀብለዋል። ሆኖም ከየትኛውም የፖለቲካ ስብስብ ጅምር እንጂ ውጤት አላዩም። ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ነጋሶ ለኦሮሞ ህዝብ መብትና ነጻነት የሚታገሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ለመመስረት ታትረዋል። ሆኖም የፖለቲካው አበባ ሲጽደቅ እንጂ ሲደርቅ አሻፈረኝ አሉ። እናም አንጀት የሚያርስ የፖለቲካ ድርጅት ባህር ማዶም ሆነ አገር ቤት መጥፋቱ እያብሰከስካቸው ቁዘማ ያዙ።
ተስፋ ቆርጠው ግን ለፖለቲካው ጀርባቸውን አልሰጡም። ምክንያቱ ደግሞ ሌላ ሳይሆን ከተስፋ መቁረጥ ጋር ስለማይተዋወቁ ብቻ ነው። እናም ለአገራቸው አንድ ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ ለማበርከት ደጅ ደጁን ሲመለከቱ ኢህአዴግን እመንገዳቸው ላይ አገኙት። አጥንተውት እና አስጠንተውት ተጠጉት። ለዓመታት ከኖሩበት ባህር ማዶ ጓዛቸውን ጠቅልለው አገራቸው ገቡና ቃል ኪዳን አሰሩ።
ከኢህአዴግ ጋር 10 ዓመት የሚያህል የፖለቲካ መንገድ ተጉዘዋል። የለውጥን ተስፋ ሰንቀው በኦህዴድ አመራርነት፣ በሚኒስትርነትና በርዕሰ ብሔርነት በጽናት አገልግለዋል። ነጋሶ የዓላማ ሰው ናቸው፤ ላመኑበት በጽናት የሚቆሙ፡፡ ነገር ግን ለቃሉ የሚታመን የፖለቲካ ድርጅት በባትሪ ፈልገው አጡ፡፡ የሚገጥሟቸው የፖለቲካ ድርጅቶች ሃሳባቸውንና አቋማቸውን እየቀያየሩ መከራቸውን አበሏቸው፡፡ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ በኩል ሶሻሊዝምን እንገነባለን ያላቸው ኢህአዴግ እንኳን የምመራው በነጭ ካፒታሊዝም ነው ብሎ እምነታቸውን አፈረሰባቸው ፤የዓለም ተጨባጭ ሁኔታ ስላልፈቀደ ለጊዜው ሶሻሊዝምን መሳቢያ ውስጥ ከተነዋል ሲባሉ «መታለላቸው» አሳዘናቸው፡፡ ሊጠይቁ እና ሊሞግቱ ሞከሩ፤ ውጤቱ ውግዘት ሆነባቸው::
እኚህ አንጋፋ ፖለቲከኛ የህይወት ታሪክ ውስጥ የራሳቸውን ነጠላ የፖለቲካ መንገድ ብቻ አይደለም የምናየው፡፡ ከሞላ ጎደል የዘመኖቻቸውን የፖለቲካ ጎዳናም ተንሰላስሎ እናገኘዋለን፡፡
ለአገር የኖሩ የአገር አድባር የሆኑት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ በስኳር ህመም እና በደም ግፊት ምክንያት በሳኡዲ አረቢያ በአሜሪካ እና በመጨረሻም በጀርመን ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በ75 ዓመታቸው ሕይወታቸው አልፏል። እኛም ዛሬ እኚህን ታላቅ የአገር ባለውለታ በ«ሕይወት እንዲህ ናት» አምዳችን ልንዘክራቸውና የሕይወት ጉዞአቸውን ልናወሳ ወደናል፤ መልካም ንባብ!
ልጅነት
በደምቢ ዶሎ መሀል ከተማ በቤተል ቤተክርስቲያን መንደር ልዩ ስሙ ከቾ በምትባል አካባቢ ነው ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የፈለቁት። ከወላጅ እናታቸው ዲንሴ ሾሊ እና ከቄስ ጊዳዳ ሶለን ጳጉሜን 5 ቀን በ1935 ዓ.ም ተወለዱ:: ነጋሶ ልጅነታቸውን ያሳለፉት በምቾት አይደለም፤ለእግራቸው ሸራ ጫማ አያውቁም። ለትምህርት ሲሉም ከወላጆቻቸው ቤት ወጥተው በየዘመድ አዝማዱ ተንከራተዋል።
የነጋሶ የልጅነት ሕይወት በችግር የተሞላ ብቻ አልነበረም፡፡ እርሳቸውም «ልጅነቴ ማር እና ወተቴ»ን አሳምረው ያውቁታል:: ጣፋጭ የልጅነት ትዝታም ነበራቸው፤ «ጢሎ» የምትባለውን ጥቁሯን ላማቸውን አይረሷትም፡፡ ሌላው የልጅነት ሕይታቸውን «ዳንዲ የነጋሶ መንገድ» በሚለው መጽሐፍ ላይ ስለ ገጠመኛቸው ሲናገሩ «በኦሮሞ ባህል እናት ልጇን ከአንድ ዓመት ተኩል እስከ ሁለት ዓመት የምታጠባ ቢሆንም እኔ ግን ቶሎ ጡት አልተውኩም ነበር፡፡ እናቴ ሲጨንቃቸው ጡታቸውን የሚመር የግራዋ ቅጠል ጨምቀው ቀቡት፤ አሁንም አልተው አልኩኝ፡፡ ብዙ ቆይቼ ነው ያቆምኩት፡፡»ጡት መጥባት እንዳቆሙ አጎታቸው በማረፋቸው እና አጎታቸው ወንድ ልጅ ስለሌላቸው በባህሉ መሰረት ቤተሰብ ደግሞ የሚወከለው በወንድ ነው፡፡ ለዚህም ነው ዶክተር ነጋሶ ለአጎታቸው ቤተሰብ ተሰጡ፡፡
የትምህርት ሕይወት
ትምህርት ቤት ሳይገቡ ሀሙስ ሀሙስ ሚሲዮናውያን የአካባቢውን ልጆች ይጋብዞቸው ነበር፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፣ ፀሎት እና መዝሙርም ያስጠኗቸዋል፡፡ ስለ ትምህርት አጀማመራቸው ዶክተር ነጋሶ ሲያስረዱ «መጀመሪያ ሚሲዮን ትምህርት ቤት አልገባሁም፡፡ ደምቢ ዶሎ የቤተል ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ተቋቁሞ ስለነበር ስድስት ዓመት ሲሞላኝ እዚያ ገባሁ፡፡ በትምህርት ቤታችን የጉራጌ፣ የአማራ፣ ትግሬ፣ የኤርትራውያንና ሌሎችም ልጆች ነበሩ፤ ልዩነት አልነበረም፡፡»
ሀ ሁ… ያስተማሯቸው አባታቸው ናቸው:: አባታቸው ዶክተር ነጋሶን ብቻ ሳይሆን የልጅነት ጓደኞቻቸውን እነደገመኝ ዳቃ፣ ክፍሌ ወሰኑን ፊደል አስተምረዋቸዋል፡፡ ዶሎ የቤተል ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት እየተማሩ ባሉበት ወቅት ጃነሆይ ይመጣሉ ተብለው ተሰልፈው ወደ አውራጃ ጽሕፈት ቤት ሄዱ፡፡ ሁኔታውን ሲያስረዱ ‘ኃይለሥላሴ ድል አድራጊው ንጉሣችን…’ እያልን በስሜት እየዘመርን ከስድስት ሰዓት በፊት ደረስን፡፡ ንጉሡ ግን ሳይመጡ ቀሩ፤ እኛም እግራችን እስኪቃጠል ድረስ ከጠበቅናቸው በኋላ ወደ ቤታችሁ ሂዱ ስለተባልን ንጉሡን ሳናገኝ ተመለስን።»
ትምህርት ቤቱ ሲዘጋ የእርሳቸውም ትምህርት አብሮ ተዘግቶ እንደነበር በዛው መጽሐፍ ላይ ገልጸዋል። ከወራት በኋላ ግን ብርሃን ኢየሱስ የሚባል ትምህርት ቤት ገቡ፡፡ በዛም ሁለተኛ ክፍል እየተማሩ ሳለ አባታቸው ከአዲስ አበባ ተመልሰው መጡ፡፡ በወቅቱ ሚዛን ተፈሪ የአሜሪካን ሚሲዮኖች ሥራ ጀምረው ስለነበር ቤተክርስቲያን ለማቋቋም ቄስ ፈልገው ለቤተክርስትያኒቱ ደብዳቤ ጽፈው «ቄስ ላኩልን» አሉ። በዚህ አጋጣሚ አባታቸው ወደ ማጂ ዞን የድሮ ጊሜራ ዞን ዋና ከተማ ሚዛን ተፈሪ እንዲሄዱ ተመረጡ፡፡
ሚዛን ተፈሪ የቤንች ማጂ ዋና ከተማ ነበረች፤ አማርኛ ይነገርባታል። እናም ከአባታቸው ጋር ወደዛ ያቀኑት ዶክተር ነጋሶ በቆይታቸው አማርኛ እየለመዱ መጡ፡፡ ከቋንቋው ጋር ብቻ ሳይሆን የቤንችንና ከፊቾን ባህል ተላመዱ፡ ፡ከሌሎችም ጋር መግባባት ጀመሩ፡፡ ባህል፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት አኗኗር ማህበረሰብን የሚያስተሳስር ገመድ ነውና በዚህ መካከል ተሳስረው ይኖሩ ነበር፤ መለያየት አልነበረም፡፡