Ethio Job Vacancy
45.4K subscribers
23.2K photos
63 videos
157 files
19.2K links
አዳዲስ እና ወቅታዊ የሥራ ቅጥር ማስታወቂያዎችን ከተለያዩ ጋዜጦችና ድረ ገጾች ለሥራ ፈላጊዎች መረጃ መስጠት ነው።
Post New Job vacancies to Who are looking jobs.
Group discussion https://t.me/+uGe3tVg5jF4yZjk0
Download Telegram
#Update

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ መርሃ ግብር የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ምዝገባ ሰኔ 03 እና 04/2013 ዓ.ም #እንደሚቀጥል አሳውቋል።

የአዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ሰኔ 01 እና 02/2013 ዓ.ም በኦንላይን ይከናወናል ማለቱ ይታወሳል።

የኦንላይን ምዝገባው የተካሄደ ሲሆን የተወሰኑ ችግሮች እንደነበሩበት ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የደረሱ ቅሬታዎች ያሳያሉ።

የኦንላይን ምዝገባው ሰኔ 03 እና 04/2013 ዓ.ም http://portal.aau.edu.et ዶሜይንን በመጠቀም እንደሚቀጥል ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ተማሪዎች በተመደቡበት የዩኒቨርስቲው ካምፓስ ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ሰኔ 19 እና 20/2013 ዓ.ም መሆኑንም አስታውሷል።

የገጽ ለገጽ ትምህርት ሰኔ 21/2013 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
 
www. aau.edu.et በመጠቀም ምዝገባ እንዴት ማከናወን እንደሚቻል፣ የተመደቡበትን ካምፓስ መኝታ ቤት ቁጥር እና ሌሎች ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት እንደሚቻል ዩኒቨርስቲው አሳውቋል።
ምንጭ፦ አ/አ/ዩ ሬጅስትራር