#የምዕራባውያኑ ሁሉን አቀፍ ግልፅ ጦርነት‼️
የአሸባሪው ህወሓት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ ሳት ብሏቸው ይመስለኛል አንድ ምስጢር አውጥተዋል። ለነገሩ ገና ብዙ ያወጣሉ። በአንድ ወቅት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት አንድ ሃላፊ ጋር ማውራታቸውን ተናገሩ፤ ሃላፊው መፈንቅለ መንግስት አታደርጉም ለምን ብለውኝ ነበር አሉን። መፈንቅለ መንግስት ህገወጥ ነው የሚለው ተቋም ሃላፊ ናቸው እንግዲህ ይህን ያሉዋቸው።
ይህ ነገር ዓለም አቀፉ ተቋም ምን ያህል በኢትዮጵያ ሉአላዊነት ውስጥ ጣልቃ አንደገባ አንድ ማሳያ ሊሆን ይችል ይሆናል እንጂ፣ እኛ ግን የለየለት ጣልቃ ገቢ ስለመሆኑ ሌሎች በርካታ መረጃዎችን መጥቀስ አንችላለን። ለማናቸውም አቶ ጌታቸው ሌላ አንድ ጥሩ መረጃ ሰጥተውናል።
እኛ ድርጅቱና የተለያዩ ተቋማቱ እንዲሁም አሜሪካን ጨምሮ አውሮፓውያኑ ለአሸባሪው ቡድን ድጋፍ በማድረግ ላይ ስለመሆናቸው ነጋሪም ሳንሻ አሳምረን እናውቃለን። ዛሬ አይደለም፤ ቡድኑ በህግ ማስከበሩ አከርካሪውን ከተመታ ጀምሮ ሲያደርጉ የነበረውን ሁሉ አሳምረን እናውቃለን። ቡድኑ ድል የቀናው ሲመስላቸው ጮቤ ሲረግጡ ሌላ ጊዜ ሲያደፍጡ፣ ሲመታ ወይም ሊመታ ሲል ደግሞ ያላዝናሉ፤ ያስፈራራሉ። የሚገርመው ደግሞ አብረው መጮሃቸው፤ ማስፈራራታቸው ነው።
#EPA
የአሸባሪው ህወሓት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ ሳት ብሏቸው ይመስለኛል አንድ ምስጢር አውጥተዋል። ለነገሩ ገና ብዙ ያወጣሉ። በአንድ ወቅት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት አንድ ሃላፊ ጋር ማውራታቸውን ተናገሩ፤ ሃላፊው መፈንቅለ መንግስት አታደርጉም ለምን ብለውኝ ነበር አሉን። መፈንቅለ መንግስት ህገወጥ ነው የሚለው ተቋም ሃላፊ ናቸው እንግዲህ ይህን ያሉዋቸው።
ይህ ነገር ዓለም አቀፉ ተቋም ምን ያህል በኢትዮጵያ ሉአላዊነት ውስጥ ጣልቃ አንደገባ አንድ ማሳያ ሊሆን ይችል ይሆናል እንጂ፣ እኛ ግን የለየለት ጣልቃ ገቢ ስለመሆኑ ሌሎች በርካታ መረጃዎችን መጥቀስ አንችላለን። ለማናቸውም አቶ ጌታቸው ሌላ አንድ ጥሩ መረጃ ሰጥተውናል።
እኛ ድርጅቱና የተለያዩ ተቋማቱ እንዲሁም አሜሪካን ጨምሮ አውሮፓውያኑ ለአሸባሪው ቡድን ድጋፍ በማድረግ ላይ ስለመሆናቸው ነጋሪም ሳንሻ አሳምረን እናውቃለን። ዛሬ አይደለም፤ ቡድኑ በህግ ማስከበሩ አከርካሪውን ከተመታ ጀምሮ ሲያደርጉ የነበረውን ሁሉ አሳምረን እናውቃለን። ቡድኑ ድል የቀናው ሲመስላቸው ጮቤ ሲረግጡ ሌላ ጊዜ ሲያደፍጡ፣ ሲመታ ወይም ሊመታ ሲል ደግሞ ያላዝናሉ፤ ያስፈራራሉ። የሚገርመው ደግሞ አብረው መጮሃቸው፤ ማስፈራራታቸው ነው።
#EPA