Afar Mass Media Agency (AFMMA)
1.09K subscribers
3.65K photos
161 videos
2 files
655 links
This channel is an official channel of Afar Mass Media Agency (AFMMA).
AFMMA is an autonomous government organization accountable to the regional Council of the Afar region.
Download Telegram
#አረሙ ህወሓት ተነቅሎ ኢትዮጵያ እፎይ የምትልበት ጊዜ ተቃርቧል❗️

አሸባሪው ህወሓት በሽብር ተወልዶ በሽብር የኖረ የኢትዮጵያውያን የዕድገት ፀር ነው። ቡድኑ ገና ከምሥረታው ጀምሮ በያዘው የጦረኝነት መንገድ ለ17 ዓመታት ከደርግ ጋር ጦርነት በማካሄድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ህይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ ይህንን አካሄድ ዘወትር እንደጀግንነት በመቁጠር ጦርነትን እንደ ብቸኛ የችግር መፍቻ አማራጭ ያደረገ ማህበረሰብ እንዲፈጠር ትልቅ ስራ ሰርቷል።

ወደ ስልጣን ሲመጣ እታገልለታለሁ ላለው ማህበረሰብ አንዳችም ቁምነገር ሳይፈይድ ለ27 ዓመታት የራሱን ኪስ ብቻ ሲያደልብ ኖሯል። ኢትዮጵያውያን ግን ሸክሙ ሲከብዳቸው ከጫንቃቸው አወረዱት። ሆኖም ስግብግብነትና አልጠግብ ባይነት የተጠናወተው ይህ ቡድን መልሶ በህዝብ ጫንቃ ላይ ካልተፈናጠጥኩ አልኖርም በሚል የሆዳምነት አባዜ በመለከፉ ለሌላ ጦርነት ታጥቆ ተነሳ።

ይህ ቡድን ለ27 ዓመታት ከፈፀመው አስፀያፊ ተግባሩ በኋላ ዳግም በለውጡ ምክንያት ራሱን የሚያድስበትና ከጥፋት ሃጢያቱ የሚነፃበት ዕድል ቢሰጠውም ይህንን ዕድል ግን አልተጠቀመበትም። በዚህም የተነሳ መልካም አጋጣሚዎችን ሁሉ ሲያበላሽ ቆይቶ በመጨረሻም የሠላምን ቀይ መስመር በመዝለል በሃገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የማይገባ ድርጊት ፈፀመ። “አይጥ ለሞቷ የድመትን አፍንጫ ታሸታለች” እንዲሉ ይህ ታዲያ ከትዕግሥት በላይ በመሆኑ የሕግ ማስከበር ዘመቻው ተጀመረ።

በዚህ አሣፋሪ ድርጊቱ በከፍተኛ ሁኔታ የተቀጣው ይህ ቡድን ታዲያ በሁለት ሣምንት ጊዜ ውስጥ እንዳልነበረ ሆኖ በዱር በገደሉ የተበታተነበትና ከፊሎችም የድርጊቱ መሪዎች በየጫካውና በየጎሬው ተደብቀው ከጉድጓድ ተጎትተው የወጡበት ሁኔታ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። ቡድኑም ከዚያ በፊት ቡራ ከረዩ እያለ ትግራይ የጠላቶቻችን መቀበሪያ ትሆናለች እንዳላለ በአጭር ጊዜ ራሱ ተቀበረባት።

#EPA