#የአክሱም እና ሽሬ ከተሞች ማምሻውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት አገኙ ።
አፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት-ጥር 10 /2013
በትግራይ ክልል በጁንታው ጉዳት ደርሶበት የነበረው የኤሌክትሪክ መስመር ተጠግኖ የአክሱም እና ሽሬ ከተሞች እና አካባቢያቸው ዛሬ የኤሌክትሪክ አገልገሎት ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።
መሠረተ ልማቱን ለመጠገን በተደረገው ከፍተኛ ጥረት ቀደም ሲል አብዛኞቹ የትግራይ አካባቢዎች የመብራት አገልግሎት ማግኘታቸውንና የአድዋ ከተማ ደግሞ ዛሬ ከሰዓት በፊት ኤሌክትሪክ ማግኘቱን አስታውሷል።
በጁንታው ጉዳት ደርሶበት ከጥቅም ውጭ ሆኖ የቆየው የአክሱም እና ሽሬ ከተሞች እና አካባቢያቸው የኤሌክትሪክ መስመር በመጠገኑ ማምሻውን ከተሞቹ የመብራት አገልግሎት አግኝተዋል ብሏል።
የሑመራ እና ወልቃይት ከተሞች እና አካባቢያቸውን ኤሌክትሪክ ለማገናኘትም ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በመሆን የጥገና ሥራውን በሓላፊነት ለተወጡ የተቋሙ ሠራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።
#Addis Media Network
አፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት-ጥር 10 /2013
በትግራይ ክልል በጁንታው ጉዳት ደርሶበት የነበረው የኤሌክትሪክ መስመር ተጠግኖ የአክሱም እና ሽሬ ከተሞች እና አካባቢያቸው ዛሬ የኤሌክትሪክ አገልገሎት ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።
መሠረተ ልማቱን ለመጠገን በተደረገው ከፍተኛ ጥረት ቀደም ሲል አብዛኞቹ የትግራይ አካባቢዎች የመብራት አገልግሎት ማግኘታቸውንና የአድዋ ከተማ ደግሞ ዛሬ ከሰዓት በፊት ኤሌክትሪክ ማግኘቱን አስታውሷል።
በጁንታው ጉዳት ደርሶበት ከጥቅም ውጭ ሆኖ የቆየው የአክሱም እና ሽሬ ከተሞች እና አካባቢያቸው የኤሌክትሪክ መስመር በመጠገኑ ማምሻውን ከተሞቹ የመብራት አገልግሎት አግኝተዋል ብሏል።
የሑመራ እና ወልቃይት ከተሞች እና አካባቢያቸውን ኤሌክትሪክ ለማገናኘትም ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በመሆን የጥገና ሥራውን በሓላፊነት ለተወጡ የተቋሙ ሠራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።
#Addis Media Network