ቅዳሜ፡- ነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም
የ1980 ዓ/ም ተመራቂ የነበሩ ሰልጣኞች ከ36 ዓመት በኋላ በኮሌጁ ተገናኙ!!
ብዙዎቹ የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ዘርፍ ተማሪዎች የነበሩ የቀድሞዎቹ የ1980 ዓ/ም ተመራቂ ሰልጣኞች ከ36 ዓመታት በኋላ ዛሬ ነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በኮሌጁ ተገናኝተዋል።
በቀድሞው ጀነራል ዊንጌት ኮንስትራክሽንና ሙያ ት/ቤት በአሁኑ ደግሞ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ3 ዓመት የሙያ ስልጠናቸውን 1980 ዓ/ም ላይ አጠናቀው ህይወት በመራቻቸው ጎዳን የተበተኑት የቀድሞዎቹ ተማሪዎች ወደ ኋላ 36 ዓመታትን ቆጥረውና ከተለያዩ ክፍለ ዓለማት ተጠራርተው የወጣትነት ት/ቤታቸውን እንደ መሰብሰቢያ ጥላ በመቁጠር በዛሬው ዕለት ተገናኝተዋል።
ያ የወጣትነት ዕድሜ ልዩ ትዝታ እንደ ማግኔት ስቦ አንድ ላይ ያሰባሰባቸው የቀድሞዎቹ ተማሪዎች በብዙ የህይወት ውጣ ውረድ ተፍትነውና በብዙ የዓለማችን ክፍሎች ተበትነው ዛሬ ላይ መሰባሰብ ሲችሉ በተማሪነት የነበራቸውን ትውስታና ገጠመኝ ለማወጋት ችለዋል።
አንዳንዶቹ ከአገር ውጪ ሆነው ርቀት ገድቧቸው፣ አንዳዶቹ ደግሞ እርፍተ ዘመን ገትቷቸው ሌሎቹም በልዩ ልዩ ምክኒያቶች በዕለቱ ባይገኙም በልቦና መንፈስ ተቃቅፈና ሃሳብ ለሃሳብ ተናበው ተገናኝተዋል።
በዛሬው ዕለት የተሰበሰቡት የቀድሞዎቹ ተማሪዎቹ ብቻ ሳይሆኑ የዚያን ጊዜ የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ዘርፍ መምህራን የነበሩት ባለ አሻራ አዛውንቶች ጭምር ተገኝተዋል። በህይወት የሌሉ አሰልጣኞች ደግሞ በቤተሰቦቻቸው ተውክለው ስብስቡን ወደ ቀረበ ቤተሰብነት አሳድገውታል።
በዛሬው ታሪካዊ ግንኙነት የነበሩ ሁነቶች የልጅነት ፎቶዎችን በመመልከት ከ36 ዓመት በኋላ ያለው አካላዊ ለውጥን ማነጻጸር፣ በህይወት ያሉን የሚኖሩበት ቦታ፣ ስራና ቤተሰባዊ ሁኔታ ማብራራት፣ ለቀድሞ መምህራንና ቤተሰቦቻቸው እወቅና እና ሽልማት ማበርከት፣ በአካል ያልተገኙትን ቀጣይ ለማፈላለግ ምክረ ሃሳብ ማካሄድ፣ በተለያየ ችግር ላይ ለሚገኙ ጓደኞቻቸው በልዩ ልዩ ማህበራዊ ድጋፍ መድረስ፣ ተቋሙ አሁን የደረሰበትን ደረጃ ለማየት ወርክሾፖችን መጎብኘት እና ለቀድሞው ት/ቤታችን ምን አይነት አሻራ እናስቀምጥ የሚሉት ይገኙበታል።
የቀድሞዎቹ የጀነራል ዊንጌት ተማሪዎች በውይይታቸው ቀጣይ የኤሌክትሪክ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ዲፓርትመንት የ1980 ምሩቃን በማስባሰብ ቤተሰብ ለማድረግ እንዳቀዱ ተገልጿል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የ1980 ዓ/ም ተመራቂ የነበሩ ሰልጣኞች ከ36 ዓመት በኋላ በኮሌጁ ተገናኙ!!
ብዙዎቹ የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ዘርፍ ተማሪዎች የነበሩ የቀድሞዎቹ የ1980 ዓ/ም ተመራቂ ሰልጣኞች ከ36 ዓመታት በኋላ ዛሬ ነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በኮሌጁ ተገናኝተዋል።
በቀድሞው ጀነራል ዊንጌት ኮንስትራክሽንና ሙያ ት/ቤት በአሁኑ ደግሞ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ3 ዓመት የሙያ ስልጠናቸውን 1980 ዓ/ም ላይ አጠናቀው ህይወት በመራቻቸው ጎዳን የተበተኑት የቀድሞዎቹ ተማሪዎች ወደ ኋላ 36 ዓመታትን ቆጥረውና ከተለያዩ ክፍለ ዓለማት ተጠራርተው የወጣትነት ት/ቤታቸውን እንደ መሰብሰቢያ ጥላ በመቁጠር በዛሬው ዕለት ተገናኝተዋል።
ያ የወጣትነት ዕድሜ ልዩ ትዝታ እንደ ማግኔት ስቦ አንድ ላይ ያሰባሰባቸው የቀድሞዎቹ ተማሪዎች በብዙ የህይወት ውጣ ውረድ ተፍትነውና በብዙ የዓለማችን ክፍሎች ተበትነው ዛሬ ላይ መሰባሰብ ሲችሉ በተማሪነት የነበራቸውን ትውስታና ገጠመኝ ለማወጋት ችለዋል።
አንዳንዶቹ ከአገር ውጪ ሆነው ርቀት ገድቧቸው፣ አንዳዶቹ ደግሞ እርፍተ ዘመን ገትቷቸው ሌሎቹም በልዩ ልዩ ምክኒያቶች በዕለቱ ባይገኙም በልቦና መንፈስ ተቃቅፈና ሃሳብ ለሃሳብ ተናበው ተገናኝተዋል።
በዛሬው ዕለት የተሰበሰቡት የቀድሞዎቹ ተማሪዎቹ ብቻ ሳይሆኑ የዚያን ጊዜ የኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ዘርፍ መምህራን የነበሩት ባለ አሻራ አዛውንቶች ጭምር ተገኝተዋል። በህይወት የሌሉ አሰልጣኞች ደግሞ በቤተሰቦቻቸው ተውክለው ስብስቡን ወደ ቀረበ ቤተሰብነት አሳድገውታል።
በዛሬው ታሪካዊ ግንኙነት የነበሩ ሁነቶች የልጅነት ፎቶዎችን በመመልከት ከ36 ዓመት በኋላ ያለው አካላዊ ለውጥን ማነጻጸር፣ በህይወት ያሉን የሚኖሩበት ቦታ፣ ስራና ቤተሰባዊ ሁኔታ ማብራራት፣ ለቀድሞ መምህራንና ቤተሰቦቻቸው እወቅና እና ሽልማት ማበርከት፣ በአካል ያልተገኙትን ቀጣይ ለማፈላለግ ምክረ ሃሳብ ማካሄድ፣ በተለያየ ችግር ላይ ለሚገኙ ጓደኞቻቸው በልዩ ልዩ ማህበራዊ ድጋፍ መድረስ፣ ተቋሙ አሁን የደረሰበትን ደረጃ ለማየት ወርክሾፖችን መጎብኘት እና ለቀድሞው ት/ቤታችን ምን አይነት አሻራ እናስቀምጥ የሚሉት ይገኙበታል።
የቀድሞዎቹ የጀነራል ዊንጌት ተማሪዎች በውይይታቸው ቀጣይ የኤሌክትሪክ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ዲፓርትመንት የ1980 ምሩቃን በማስባሰብ ቤተሰብ ለማድረግ እንዳቀዱ ተገልጿል።
"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍24🙏2🏆1
ይህ ከታች ያለው የ youtube ቻናል በጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተከፈተ ሲሆን አላማው በTVET ዘርፍ ላይ እየተተገበሩ ያሉ የሚተገበሩ እና መተግበር ስለሚገባቸው አዳዲስ እይታዎች፣ስልጠናዎች እና የአዲሱን ምዘናን(Model COC) በተመለከተ መረጃዎች እና ስልጠናዎች በስፋት እና በጥራት የሚለቀቅበት በመሆኑ Subscribe አድርገው ቤተሰብ በመሆን በብዙ ያትርፉ።
https://m.youtube.com/@TvetInsight
https://m.youtube.com/@TvetInsight
👍21❤1
አርብ፡- ጳጉሜ 1 ቀን 2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን ሠራተኞች በሙሉ
ነገ ቅዳሜ ማለትም ጳጉሜ 2 ቀን 2016 ዓ.ም የሪፎርም ቀን ሲሆን ዕለቱ ''ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት'' በሚል መሪ ቃል ሁሉም የአዲስ አበባ አስተዳደር መሥሪያ ቤቶች ለተገልጋዮች መደበኛ አገልግሎት ይሰጣሉ።
ስለሆነም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ሁላችሁም የኮሌጃችን ሠራተኞች በነገው ዕለት በመደበኛ ስራችሁ ተገኝታችሁ ስራችሁን እንዲትሰሩ እያሳወቅን የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎትም መኖሩን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ፦ አገልግሎቱ እንደመደበኛው ሰዓት ሲሆን የሰዓት ፊርማውም በጣት አሻራ መሆኑን እንጠቁማለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን ሠራተኞች በሙሉ
ነገ ቅዳሜ ማለትም ጳጉሜ 2 ቀን 2016 ዓ.ም የሪፎርም ቀን ሲሆን ዕለቱ ''ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት'' በሚል መሪ ቃል ሁሉም የአዲስ አበባ አስተዳደር መሥሪያ ቤቶች ለተገልጋዮች መደበኛ አገልግሎት ይሰጣሉ።
ስለሆነም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ሁላችሁም የኮሌጃችን ሠራተኞች በነገው ዕለት በመደበኛ ስራችሁ ተገኝታችሁ ስራችሁን እንዲትሰሩ እያሳወቅን የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎትም መኖሩን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ፦ አገልግሎቱ እንደመደበኛው ሰዓት ሲሆን የሰዓት ፊርማውም በጣት አሻራ መሆኑን እንጠቁማለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
👍5👎3❤2🏆2
አርብ:- ጳጉሜ 1 ቀን 2016 ዓ.ም
የመሻገር ቀን
ዛሬ የመሻገር ቀንን ምክኒያት በማድረግ ‹‹የመሻገር ጥረቶች፤ የአዲስ ብርሃን ወረቶች›› በሚል መሪ ሐሳብ ጳጉሜ 1 ቀንን በትጋት እየሰራን እናስባለን፡፡
መሻገር ከትናንት ወደ ነገ፣ ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከወንዙ ባሻገር ወደ ሌላኛው መንደር፣ ከአንድ ዘመን ወደ ሌላ፣ ከመጥፎ ወደ ጥሩ፣ ከድካም ወደ እረፍት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ወዘተ ነው፡፡
እኛ እንደ ተቋም ባሳለፍነው ጊዜ በርካታ ድንቅና ብርቅ የሆኖ እምርታዊና መሰረታዊ ለውጦችን በማምጣት የላቀ ስኬት አስመዝግበናል፡፡ እነዚህ ተግባራት ደግሞ እንደ ኮሌጅ ለመሻገር ጓጉተን ለመድረስ ቸኩለን ያስመዘገብናቸው አስደናቂ ውጤቶች ናቸው፡፡
ሁላችንም እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን ለመሻገር በሩቅ ያቀድናቸውን ጭምር በቅርብ ማጠናቀቅ ችለናል፡፡ ለዚህ ስኬት ደግሞ የሁሉም አካል ርብርብ እና ቀና አመለካከት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይህም ይቻላል የሚለውን አቅም አሳይቶናል፡፡
ያለፈው ጊዜ ውጤታማነታችን ለቀጣይ እቅዳችን ስንቅ ለጉዟችን ደግሞ ትጥቅ ስለሆነ መጪው ጊዜ እንደ ግልም ሆነ እንደተቋም የመሻገር ይሆንልን ዘንድ መልካም ምኞታችንን እንገልፃን፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የመሻገር ቀን
ዛሬ የመሻገር ቀንን ምክኒያት በማድረግ ‹‹የመሻገር ጥረቶች፤ የአዲስ ብርሃን ወረቶች›› በሚል መሪ ሐሳብ ጳጉሜ 1 ቀንን በትጋት እየሰራን እናስባለን፡፡
መሻገር ከትናንት ወደ ነገ፣ ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከወንዙ ባሻገር ወደ ሌላኛው መንደር፣ ከአንድ ዘመን ወደ ሌላ፣ ከመጥፎ ወደ ጥሩ፣ ከድካም ወደ እረፍት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ወዘተ ነው፡፡
እኛ እንደ ተቋም ባሳለፍነው ጊዜ በርካታ ድንቅና ብርቅ የሆኖ እምርታዊና መሰረታዊ ለውጦችን በማምጣት የላቀ ስኬት አስመዝግበናል፡፡ እነዚህ ተግባራት ደግሞ እንደ ኮሌጅ ለመሻገር ጓጉተን ለመድረስ ቸኩለን ያስመዘገብናቸው አስደናቂ ውጤቶች ናቸው፡፡
ሁላችንም እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን ለመሻገር በሩቅ ያቀድናቸውን ጭምር በቅርብ ማጠናቀቅ ችለናል፡፡ ለዚህ ስኬት ደግሞ የሁሉም አካል ርብርብ እና ቀና አመለካከት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይህም ይቻላል የሚለውን አቅም አሳይቶናል፡፡
ያለፈው ጊዜ ውጤታማነታችን ለቀጣይ እቅዳችን ስንቅ ለጉዟችን ደግሞ ትጥቅ ስለሆነ መጪው ጊዜ እንደ ግልም ሆነ እንደተቋም የመሻገር ይሆንልን ዘንድ መልካም ምኞታችንን እንገልፃን፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍9❤4