ረቡዕ:- ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም
የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ!!
የጀ/ ታደሰ ብሩ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ ከ100 በላይ የሚሆኑ እና ከ10ኛ እና ከ12ኛ ክፍሎች የተውጣጡ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የልዩ ልዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ ተማሪዎቹ ቀጣይ የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከወሰዱ በኋላ የተወሰኑት ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲያመሩ ቀሪዎቹ ደግሞ ወደ ተቋማችን የሚቀላቀሉ በመሆናቸው ከአሁኑ አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖራቸው እና ለምርጫ እንዳይቸገሩ ያግዛቸዋል ተብሏል፡፡
ከዚህ ባሻገር አሁን ላይ 10ኛ ክፍል የሆኑ ተማሪዎች ቀጣይ የሙያ ስልጠናን ከቀለም ትምህርት ጋር አቀናጅተው ይማሩ ዘንድ አቅጣጫ በመቀመጡ እና ትግበራ በመጀመሩ ለእነሱም መሰረታዊ መረጃ ለማሰጨበጥ ይረዳል መባሉን ሰምተናል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም እንደተደሰቱ ገልፀው የሙያ ትምህርት ለመማር ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ምስክርነትን ሰጥተዋል፡፡
በተመሳሳይ ከሳምንታት በፊት ከአስራ ስምንት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕርሳነ መምህራን እና ከሶስት ክፍለ ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች የተውጣጡ የስራ ኃላፊዎች በኮሌጁ ተገኝተው የጋራ ምክክርና ጉብኝት ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ!!
የጀ/ ታደሰ ብሩ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በዕለቱ ከ100 በላይ የሚሆኑ እና ከ10ኛ እና ከ12ኛ ክፍሎች የተውጣጡ ተማሪዎች ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የኮሌጁን ተቋማዊ ስነ ምህዳር እና አጠቃላይ የስራ እንቅሰቃሴ ገለፃ ተሰጥቷቸው የልዩ ልዩ ዲፓርትመንቶችን ወርክሾፖች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
የጉብኝቱ መሰረታዊ ዓላማ ተማሪዎቹ ቀጣይ የ12 ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከወሰዱ በኋላ የተወሰኑት ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲያመሩ ቀሪዎቹ ደግሞ ወደ ተቋማችን የሚቀላቀሉ በመሆናቸው ከአሁኑ አዎንታዊ አመለካከት እንዲኖራቸው እና ለምርጫ እንዳይቸገሩ ያግዛቸዋል ተብሏል፡፡
ከዚህ ባሻገር አሁን ላይ 10ኛ ክፍል የሆኑ ተማሪዎች ቀጣይ የሙያ ስልጠናን ከቀለም ትምህርት ጋር አቀናጅተው ይማሩ ዘንድ አቅጣጫ በመቀመጡ እና ትግበራ በመጀመሩ ለእነሱም መሰረታዊ መረጃ ለማሰጨበጥ ይረዳል መባሉን ሰምተናል፡፡
ተማሪዎቹ በተሰጣቸው ማብራሪያ እና በጉብኝት ወቅቱ ባዩት የስራ እንቅስቃሴ በጣም እንደተደሰቱ ገልፀው የሙያ ትምህርት ለመማር ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ምስክርነትን ሰጥተዋል፡፡
በተመሳሳይ ከሳምንታት በፊት ከአስራ ስምንት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕርሳነ መምህራን እና ከሶስት ክፍለ ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች የተውጣጡ የስራ ኃላፊዎች በኮሌጁ ተገኝተው የጋራ ምክክርና ጉብኝት ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍9❤2
ሐሙስ:- ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም
ዜና ስፖርት
ኮሌጁ በዲኖች የሩጫ ውድድር ሚዲያሊያ ተሸለመ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዲኖች የ400 ሜትር የዱላ ቅብብል ሩጫ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሚዲያሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም 4፡00 ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲዮም እንደ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ተቋማት በተደረገ የዱላ ቅብብሎሽ ሩጫ የኮሌጁ ምክትል ዲኖች አቶ ሰባሁዲን ሁሴን እና አቶ ደሜ መርሻ ባደረጉት ከፍተኛ ፉክክር ለኮሌጁ የብር ሚዳያሊያ አስገኝተዋል፡፡
14ኛውን የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ ከ7 ኮሌጆች የተውጣጡ 14 ዲኖች በተሳተፉበት የዱላ ቅብብሎሽ ሩጫ ልደታ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ቀዳሚ ሆኖ ወርቅ ሲያገኝ ምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ደግሞ በ3ኛ ደረጃ አጠናቋል፡፡
በመሰረቱ በቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ታሪክ የዲኖች የዱላ ቅብብሎሽ ሩጫ ሲደረግ ዘንድሮ የመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ሳምንቱ ቴክኒክ እና ሙያ ለዘላቂ ልማት በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ዜና ስፖርት
ኮሌጁ በዲኖች የሩጫ ውድድር ሚዲያሊያ ተሸለመ!!
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዲኖች የ400 ሜትር የዱላ ቅብብል ሩጫ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሚዲያሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም 4፡00 ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲዮም እንደ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ተቋማት በተደረገ የዱላ ቅብብሎሽ ሩጫ የኮሌጁ ምክትል ዲኖች አቶ ሰባሁዲን ሁሴን እና አቶ ደሜ መርሻ ባደረጉት ከፍተኛ ፉክክር ለኮሌጁ የብር ሚዳያሊያ አስገኝተዋል፡፡
14ኛውን የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ምክኒያት በማድረግ ከ7 ኮሌጆች የተውጣጡ 14 ዲኖች በተሳተፉበት የዱላ ቅብብሎሽ ሩጫ ልደታ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ቀዳሚ ሆኖ ወርቅ ሲያገኝ ምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ደግሞ በ3ኛ ደረጃ አጠናቋል፡፡
በመሰረቱ በቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ታሪክ የዲኖች የዱላ ቅብብሎሽ ሩጫ ሲደረግ ዘንድሮ የመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ሳምንቱ ቴክኒክ እና ሙያ ለዘላቂ ልማት በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍8👏4🙏4😢1
አርብ፡- ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓ.ም
የተመራቂዎች መከታተያ ጥናት ግኝት ቀረበ!!
የ2015 ተመራቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል መከታተያ ጥናት ግኝት /graduates tracer study findings/ ቀረበ።
ጥናቱ በኮሌጁ ጥናትና ምርምር ቡድን አባላት ተሰርቶ የቀረበ ሲሆን የተመራቂ ሰልጣኞችን የስራ ሁኔታ በዲፓርትመንት፣ በፆታ እና በስራ ዓይነት ተንትኖ ያስቀመጠ ነው።
በኮሌጁ የ2015 ዓ.ም አጠቃላይ ተመራቂዎች ዉስጥ ከ80 ፐርሰንት በላይ የሚሆኑት በተመረቁ 6 ወራት ውስጥ በተማሩት የሙያ መስክ ወደ ስራ መግባታቸው ተረጋግጧል።
ወደ ስራ ኢንዱስትሪው ከተቀላቀሉ ተመራቂ ሰልጣኞች ውስጥ ከ85 ፐርሰንት በላይ የሚሆኑት በኮሌጁ ባገኙት ስልጠና እና አሁን እየሰሩት ባለው የስራ መስክ መደሰታቸውን ገልፀዋል።
ተመራቂዎቹ በመንግስት መስሪያ ቤት እና በኢንዱስትሪዎች በመቀጠር እንዲሁም በግላቸው እና ተደራጅተው በመስራት ወደ ክፍለ ኢኮኖሚው አበርክቶ መግባታቸው ታውቋል።
በሌላ በኩል ጥናቱ በአሰልጣኞች፣ በሰልጣኞች እንዲሁም በትብብር ስልጠና ሰጭ ድርጅቶች ያለውን አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ተንትኖ አሳይቷል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
የተመራቂዎች መከታተያ ጥናት ግኝት ቀረበ!!
የ2015 ተመራቂ ሰልጣኞች የስራ ዕድል መከታተያ ጥናት ግኝት /graduates tracer study findings/ ቀረበ።
ጥናቱ በኮሌጁ ጥናትና ምርምር ቡድን አባላት ተሰርቶ የቀረበ ሲሆን የተመራቂ ሰልጣኞችን የስራ ሁኔታ በዲፓርትመንት፣ በፆታ እና በስራ ዓይነት ተንትኖ ያስቀመጠ ነው።
በኮሌጁ የ2015 ዓ.ም አጠቃላይ ተመራቂዎች ዉስጥ ከ80 ፐርሰንት በላይ የሚሆኑት በተመረቁ 6 ወራት ውስጥ በተማሩት የሙያ መስክ ወደ ስራ መግባታቸው ተረጋግጧል።
ወደ ስራ ኢንዱስትሪው ከተቀላቀሉ ተመራቂ ሰልጣኞች ውስጥ ከ85 ፐርሰንት በላይ የሚሆኑት በኮሌጁ ባገኙት ስልጠና እና አሁን እየሰሩት ባለው የስራ መስክ መደሰታቸውን ገልፀዋል።
ተመራቂዎቹ በመንግስት መስሪያ ቤት እና በኢንዱስትሪዎች በመቀጠር እንዲሁም በግላቸው እና ተደራጅተው በመስራት ወደ ክፍለ ኢኮኖሚው አበርክቶ መግባታቸው ታውቋል።
በሌላ በኩል ጥናቱ በአሰልጣኞች፣ በሰልጣኞች እንዲሁም በትብብር ስልጠና ሰጭ ድርጅቶች ያለውን አዎንታዊ እና አሉታዊ ጎኖች ተንትኖ አሳይቷል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"
👍9
Forwarded from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
በሚኒስቴሩ የለሙ መተግበሪያዎች አጠቃቀም ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የለሙ የቀጠሮ ማስያዣ እና ቅሬታ እና አስተያየት ማቅረቢያ መተግበሪያዎች አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሚኒስቴሩ አመራርና ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡
ሚኒስቴሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋም እንደመሆኑ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ እና በተቋሙ የሚቀርቡ አቤቱታ እና ቅሬታዎችን መቀበል እና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ የቀጠሮ ማስያዣ(appointment system) እና አስተያየት እና ቅሬታ መቀበያ(public feedback system) በአግባቡ እንዲጠቀሙ ታሳቢ ተደርጎ መድረኩን መዘጋጀቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈጻሚ አቶ ኃ/እየሱስ ደምሴ ገልጸዋል፡፡
ሀገራት አገልግሎታቸውን ለማዘመን ወደ ዲጃታል ዓለም እየገቡ መሆኑ የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው ሚኒስቴሩም ዘመኑና ጊዜውን የሚመጥን አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉትን ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ መተግበረያዎችን በማልማት ወደ ሥራ እያስገባ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የተቋሙ ሠራተኞች መረጃ መለዋወጥ የሚያስችላቸውን አፕሊኬሽን( MOLS Family chat application) እና የተቋሙ ሰራተኞች የሀሳብ ባንክ(Idea bank) ሲስተሞች አጠቃቀም አስመልክቶ ገለጻ ተደርጓል፡፡
ባለጉዳዮች ወይም ተገልጋዮች ወደ ሚኒስቴሩ ለመምጣት ቢፈልጉ አስቀድመው ቀጠሮ ለማስያዝ appointment.mols.gov.et እና አስተያየት እና ቅሬታ ለማቅረብ ደግሞ pfs.mols.gov.et በመግባት መስተናገድ እና አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
ሰኔ 14/2016 ዓ.ም
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የለሙ የቀጠሮ ማስያዣ እና ቅሬታ እና አስተያየት ማቅረቢያ መተግበሪያዎች አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሚኒስቴሩ አመራርና ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡
ሚኒስቴሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋም እንደመሆኑ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ እና በተቋሙ የሚቀርቡ አቤቱታ እና ቅሬታዎችን መቀበል እና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችሉ የቀጠሮ ማስያዣ(appointment system) እና አስተያየት እና ቅሬታ መቀበያ(public feedback system) በአግባቡ እንዲጠቀሙ ታሳቢ ተደርጎ መድረኩን መዘጋጀቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስራ አስፈጻሚ አቶ ኃ/እየሱስ ደምሴ ገልጸዋል፡፡
ሀገራት አገልግሎታቸውን ለማዘመን ወደ ዲጃታል ዓለም እየገቡ መሆኑ የገለጹት ሥራ አስፈጻሚው ሚኒስቴሩም ዘመኑና ጊዜውን የሚመጥን አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉትን ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ መተግበረያዎችን በማልማት ወደ ሥራ እያስገባ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የተቋሙ ሠራተኞች መረጃ መለዋወጥ የሚያስችላቸውን አፕሊኬሽን( MOLS Family chat application) እና የተቋሙ ሰራተኞች የሀሳብ ባንክ(Idea bank) ሲስተሞች አጠቃቀም አስመልክቶ ገለጻ ተደርጓል፡፡
ባለጉዳዮች ወይም ተገልጋዮች ወደ ሚኒስቴሩ ለመምጣት ቢፈልጉ አስቀድመው ቀጠሮ ለማስያዝ appointment.mols.gov.et እና አስተያየት እና ቅሬታ ለማቅረብ ደግሞ pfs.mols.gov.et በመግባት መስተናገድ እና አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
ሰኔ 14/2016 ዓ.ም
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
👍5
ቅዳሜ፡- ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም
14ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ተጀመረ፡፡
14ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ዛሬ ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቪሸን ማዕከል ለጎብኝዎች እይታ ክፍት ተደረገ፡፡
በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነን ጨምሮ የፌደራል እና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ የመዲናይት ከንቲባ በመልዕክታቸው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ኢንተርፕራይዞቻችን እንዳይከስሙ፣ ይልቁኑ በስራ ባህልና ክህሎት እየታነጹ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የስራ ዕድል በመፍጠር ተኪ ምርት ለገበያ እንዲያቀርቡ ትርጉም ያለው አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ብለዋል።
በዚህ ኤግዚቪሽን ላይ በ15 የመንግስት እና በ6 የግል ኮሌጆች የተሰሩ አስደናቂ የማምረቻ እና የምርት ፈጠራ ስራዎች ለተመልካቾች ቀርበዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ የተሰሩ 3 የማምረቻ እና 4 የምርት ውጤቶች ለእይታ ቀርበው የተመልካችን ቀልብ መሳብ ችለዋል፡፡
በተጨማሪም በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞች የፈጠራ ምርታቸውን ይዘው ተገኝተዋል፡፡
ኤግዚቪሽኑ ''ቴክኒክና ሙያ ለዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ለ6 ተከታታይ ቀናት ለጎበኝዎች ክፍት ተደርጎ እንደሚቆይ ታውቋል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
14ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ተጀመረ፡፡
14ኛው የቴክኒክ እና ሙያ ሳምንት ዐውደ ርዕይ ዛሬ ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቪሸን ማዕከል ለጎብኝዎች እይታ ክፍት ተደረገ፡፡
በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነን ጨምሮ የፌደራል እና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ የመዲናይት ከንቲባ በመልዕክታቸው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ኢንተርፕራይዞቻችን እንዳይከስሙ፣ ይልቁኑ በስራ ባህልና ክህሎት እየታነጹ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የስራ ዕድል በመፍጠር ተኪ ምርት ለገበያ እንዲያቀርቡ ትርጉም ያለው አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ብለዋል።
በዚህ ኤግዚቪሽን ላይ በ15 የመንግስት እና በ6 የግል ኮሌጆች የተሰሩ አስደናቂ የማምረቻ እና የምርት ፈጠራ ስራዎች ለተመልካቾች ቀርበዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ የተሰሩ 3 የማምረቻ እና 4 የምርት ውጤቶች ለእይታ ቀርበው የተመልካችን ቀልብ መሳብ ችለዋል፡፡
በተጨማሪም በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞች የፈጠራ ምርታቸውን ይዘው ተገኝተዋል፡፡
ኤግዚቪሽኑ ''ቴክኒክና ሙያ ለዘላቂ ልማት'' በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ለ6 ተከታታይ ቀናት ለጎበኝዎች ክፍት ተደርጎ እንደሚቆይ ታውቋል።
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
👍21❤3