Lualawi ሉዓላዊ
2.7K subscribers
262 photos
38 videos
8 files
590 links
Download Telegram
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሕንድ እና ፓኪስታን በካሽሚር ሊንኮች
Telegram
https://t.me/+tfZYjOsLvR00YzRh
TikTok
https://www.tiktok.com/@lualawi2016
YouTube
www.youtube.com/@Lualawi-2016
Instagram
https://www.instagram.com/lualawi2016/
Telegram/Whatsapp/viber
571-531-5892
Email lualawi2016@gmail.com
የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተጀመረ፥  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  በመክፈቻው ሥነሥርዓግ ያስተላለፉት መልዕክት።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ ኣሜን!

ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጰጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!

እንደዚሁም በዚህ ቀኖናዊና ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ በሙሉ፤ ጸጋንና ሓዋርያነትን ያጐናጸፈን ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ትንሣኤውን በሰላም ኣክብረን ይህንን ዓመታዊውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለማካሄድ ስለ ሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ የጉባኤው ኣባላት የሆናችሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም እንኳን ለረክበ ካህናት ጉባኤ ኣደረሳችሁ! እንኳንም በሰላም መጣችሁ!
“ረከብነ ጸጋ ወተሰየምነ ሓዋርያተ ከመ ናስምዖሙ ለኣሕዛብ ወይእመኑ በስሙ፡- ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሓዋርያነትን ተቀበልን” (ሮሜ.፩÷፭)፤
ይህ ሐዋርያዊ ኣስተምህሮ የኛን ተእልኮና ተልእኮው ያስፈለገበትን ምክንያት ኣጉልቶ ያሳያል፤ የተቀበልነው ስጦታም ምን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ ምንባቡ ያስረዳል፤ ሓዋርያው በዚህ መልእክት የቅዱስ ወንጌል ኣስተምህሮ ዋና ግብ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ማድረግ ነው በማለት ያስተምረናል፤ እውነት ነው ድሮውኑም ቢሆን ለእግዚኣብሔር መታዘዝ ኣቅቶን ነው የወደቅነው፤ ዛሬም የምንነሣው ከእምነት የተነሣ መታዘዝን ገንዘብ ስናደርግ ነው፤ ከሁሉ በፊት እምነት ይቀድማል፤ ከሱ በኋላ ደግሞ ለእምነቱ በሙሉ ልብ መታዘዝ ይከተላል፤ ይህ ሲሆን መዳንና ትንሣኤ ይገኛል፤ ዓለም በእግዚአብሔር እየተደረገላት ያለ ጥሪ ይኸው የመታዘዝ ጥሪ ነው፤
ይህንን መለኮታዊ ጥሪ ለዓለም የማድረስ ኃላፊነትም ለኛ ለቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት የተሰጠ እንደሆነ ሐዋርያው አስገንዝቦኣል፤ ኃላፊነቱ ሲሰጠን ከነመሳርያው ነው፤ እሱም ጸጋና ሓዋርያነት ነው፤ እኛም እሱን ተቀብለናል፤ እንግዲያውስ የተቀበልነውን ጸጋና ሓዋርያነት በዓለም ውስጥ ላለው ሕዝበ እግዚአብሔር ኣገልግሎት ማዋል ከኛ ይጠበቃል፡፡

ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣበላት!! 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጊዜ የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም፤ ምክንያቱም የዚህ ሲኖዶስ ወኪሎች ሊቃነ ጳጳሳት በኣፍሪካ፣ በኣውሮፓ፣ በሰሜን ኣሜሪካ፣ በላቲን ኣሜሪካ፣ በካናዳና በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያና በኣውስትራሊያ ወዘተ የሚገኙ ሕዝበ እግዚአብሔር ምእመናንን በማገልገል ላይ ይገኛሉና ነው፤ ይህ ዕድል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መለኮታዊ ተልኮውን በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ለማድረስ ምቹ መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ከዚህም በመነሣት በየክፍለ ዓለሙ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃነ ጳጳሳት ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሻገር የየአካባቢውን ሕዝብ በማስተማርና በማቀፍ የተጣለባችሁን ሓዋርያዊ ተልእኮ በትጋትና በንቃት መወጣት ይኖርባችኋል፡፡
በማእከል ሆኖ እየመራ የሚገኝ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚህ ተልእኮ ምቹ መደላድል የመፍጠር ኃላፊነቱን በኣግባቡ መወጣት ይገባዋል፡፡ በተለይም ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን  የተማሩና በጥልቀት የተገነዘቡ፣ ብስለትም ያላቸው፤ እንዲሁም በቋንቋና በሥነ ልቦና ዕውቀት የላቀ ሀብተ ጸጋ ያላቸውን በሐዋርያነት እያሠለጠነ በአጽናፈ ዓለም ሁሉ  ሊያሰማራ ይገባል፡፡

ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣበላት! 
በብሂለ አበው (ፀሐይ ለመስኮቷ ሳታበራ…) እንደሚባለው ለሌላው በብቃት መድረስ እንችል ዘንድ እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሲኖዶሱ መንበር በሚገኝባት ምድረ ኢትዮጵያ ከመቸውም የተሻለ ስራ በመስራት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ሕዝቡንም ማገልገል ይገባናል፤ ሁላችንም እንደ ምንገነዘበው በሲኖዶሳችን ያልታቀፉ ብዙ ወገኖች በሀገር ውስጥ ኣሉን፤ እነዚህ ወገኖች አንዳንዶቹ በተለያየ ምክንያት ከኛ የወጡ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የሄዱት ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ ሌሎችም ወደ መንጋው እንዲቀላቀሉ በርትቶ መስራት የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተልእኮ ነው፤ ምክንያቱም ጸጋንና ሐዋርያነትን የተቀበልንበት ዋናው ምክንያት ይህንን ለማድረግ ነውና፡፡ ከዚህ አኳያ የቤተ ክርስቲያናችን ተደራሽነት በሳሳበት ኣካባቢ ሁሉ የተለየ ትኵረት ሰጥተን መስራትና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል፤               
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውሉደ ክህነትና ምእመናን የሆን ሁላችን፣ ከሁሉ በፊት ያለንን ዓቅምና ብቃት በኣግባቡ መገንዘብ ይኖርብናል፤ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንና ለፈጣሪው በቈራጥነት የሚታዘዝ ምእመን፣ ወጣት፣ ካህን ኣለን፤ ይህ ትልቅ ጸጋ ነው፤ ይህንን ጸጋ እግዚአብሔር፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት በሚመች ሁናቴ ዝቅ ብሎ ማገልገል የክብር ክብር ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሓቅ፣ በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ቆመን ካገለገልነውና ኣባትነታችንንና መሪነታችንን በመልካም አሰራር በትክክል በኅሊናው እንዲቀረጽ ካደረግን፣ ይህ ኃይል ከጐናችን እንደማይለይ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ይህንን ካሳካን ለኛ የተሰጠ ኃይልና ብቃት በየትም ኣይገኝም፡፡
በዚህም በዚያም ሃይማኖቱ የሚጠይቀውን ሰብእና እና ቁመና ይዘን ከተገኘን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ ያለውን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሳይቀር ለመስጠት ወደ ኋላ የማይል የእግዚአብሔር ሕዝብ ኣለን፤ ስለዚህ ይህንን ማሳካት እንችል ዘንድ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንድናስገኝ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በክብር እንያዝ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!
ለሕዝበ እግዚአብሔር የምናበረክተው ኣገልግሎት በመንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው ኣገልግሎትም ጭምር ነው፤ ከዚህ ኣንጻር ሕዝባችን የተሻለ ማኅበራዊ ኣገልግሎት እንዲያገኝ፣ በኢኮኖሚውም ከድህነት የተላቀቀ እንዲሆን፤ እንደዚሁም ሰላሙና ኣንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን፣ በማስተማርም በተግባር በመሳተፍም የሕዝቡ መሪዎችና ኣርኣያ ሆነን መስራት ይገባናል፤በተለይም ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም ተግተን መስራት ኣለብን፤
እንዳጋጣሚ ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእንግልት የተላቀቀበት ጊዜ ብዙ እንዳልሆነ ይታወቃል፤ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው፤ እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ ኣሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት ኣካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ፤ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ፤ በዚህ ኣማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ ኣድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ ኣድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው፤በመጨረሻም
የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ኣስተዳደራዊ ኣፈጻጸማችን በመገምገም ለቀጣዩ ጊዜ የስራ ኣቅጣጫን የሚያስቀምጠው የረክበ ካህናቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለኦርቶዶክሳውያን ሕዝበ ክርስቲያን እናበስራለን፤

እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣
ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እና የፓትርያርኩ የሰላም መልዕክት
“የፓርቲው ምዝገባ እንዲሰረዝ ቦርዱ ወስኗል"
መንግሥት በ3 ወር ይወርዳል ብለን . . . አቶ ጌታቸው ረዳ
ከመከላከያ ጋር ሰው የሚያዛወሩ ሕወሐቶች
“ሊገድሉኝ ወስነው ነበር’’
https://youtu.be/CmW1FJgBGiQ
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕወሐት መሰረዙን በይፋ አስታወቀ
ወደ ሀገር እንዳይገቡ ታግደው የቆዩት 3ቱ ሊቃነጳጳሳት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል፣ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ እና ብጹዕ አቡነ ያዕቆብ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በሊቃነጳጳስት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የሕወሐት መሪዎች እና የጦር አዛዦች በስጋት መኖሪያቸውን ቀየሩ
በትግራይ ወፍጮ ቤቶች ያላቸውን እህል እንዲፈጩ ታዘዋል
የሕወሐት ንብረት እንዲወረስ ምርጫ ቦርድ ወሰነ
የአልሻባብ አጥፍቶ ጠፊዎች በኢትዮጵያ ?
https://youtu.be/PXXzmzFa2AY
ኢሳይያስ በላይ ከተባለ ኢትዮጵያዊ ሞት ጋር በተያያዘ የሚሰራጨው መረጃ ሐሰተኛ ነው ሲል የኢትዮጵያ ፌድረራል ፖሊስ ሰነድ አያይዞ ማብራርያ ሰጥቷል።ፌደራል ፖሊስ ያወጣው መግልጫ የሚከተለው ነው።
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ):-የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኢሳያስ በላይ የተባለ ግለሰብ በምርመራ ክፍል ውስጥ አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተገደለ ተብሎ በአንዳንድ ሚዲያዎች እየተዘዋወረ የሚገኘው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል።
በወቅቱ የተገኘው የሕክምና ማስረጃ እንደሚያሳየው የግለሰቡ ሕይወት ያለፈው በግል ጤና ችግር ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እየገለፀ፤ ለዚህም የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሞቱን ምክንያት ለማረጋገጥ በወቅቱ የአስክሬን ምርምራ እንዲደረግ በደብደቤ ቁጥር ፌፎ/አስ/83/16 ዳግማዊ ሚኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታልን ጠይቆ ሆስፒታሉም በደብዳቤ ቁጥር 5453/44/2016 በቀን 16/9/2016 ዓ.ም በላከው የአስክሬን ምርመራ ውጤት በአካሉ ላይ የደረሰ ምንም ውጫዊ ጉዳት የሌለው መሆኑንና የግለሰቡ ሞት በሳምባ ምች በሽታ ምክንያት የደም ዝውውሩና የትንፋሽ ስርዓቱ በማቆሙ እንደሆነ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አረጋግጧል፡፡
የግለሰቡ አሟሟት እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ የፖሊስን መልካም ስም ለማጉደፍ በየትኛውም ቦታ ሆነው በዚህ መልኩ ሐሰተኛ መረጃዎችን እየፈጠሩ በሚያሰራጩ የሚዲያ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ያሳስባል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ከሪፎርሙ በፊት እንደነበረው ኃይል የተቀላቀለበት ምርመራ የሚያካሄድ ሳይሆን አሁን ላይ ዓለም በደረሰበት ቴክኖሎጂ እየታገዘ ዛሬም ወደ ፊትም ሰብዓዊ መብትን የሚያከብርና ባህሉ አድርጎ የሚቀጥል መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ያረጋግጣል።
“የፌደራል መንግስት ሊያፈርሰን አማጺ እያደራጀብን ነው ‘’
የአሜሪካው አምባሳደር ሰለ ሰላም ለመምከር ሽሬ ገቡ
የዶ/ር ደብረጽዮን ቡድን አዲስ ጥሪ
“የሰላሙ እና የጦርነቱ ሕወሐት ቡድኖች”
ልማት የሚጠላ እና ቴክኖሎጂ የሚጠየፍ ፖለቲካ
https://youtu.be/dJJg1Hqe3Gk