Genius Tutorial Service
142 subscribers
191 photos
4 videos
51 links
Empowering Genius Mind
Download Telegram
#ZENA
#ATTENTION የትምህርት ሚኒስቴር የብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ ፦

(ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ - የትምህርት ሚኒስትር)

- የፈተና ንክኪው በእጅጉ ተቀንሷል።

- ከዚህ በፊት በፈተና አሰጣጥ ወቅት የነበረውን " የኔ አካባቢ ሰው ፣ የኔ ዘመድ " የሚለውን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት ማንኛውም የአንድ አካባቢ ተወላጅ እዛው አካባቢ ያሉ ተማሪዎችን አይፈትንም። ማንኛውም የአንድ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ እራሱ የሚያስተምርበት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አይፈትንም።

- ተማሪዎች አንዴ ዩኒቨርሲቲ (ካምፓስ) ከገቡ በኃላ ከሌለው የውጪ ማህበረሰብ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አይኖራቸውም። ምንም ስልክ ወይም ሌላ የግንኙነት ነገር ይዘው አይገቡም።

- ተፈታኝ ተማሪዎች ለ4 ቀናት ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ እናበላቸዋለን ፣ እናጠጣቸዋል፣ እንከባከባቸዋለን ነገር ግን በፍፁም ከሌላው ዓለም ጋር አይገናኙንም።

- ተማሪዎች ከሚነሱበት ቦታ የተከለከሉ ነገሮችን ይዘው እንዳይሄዱ የክልል የፀጥታ ኃላፊዎች የፍተሻ ስራ ይሰራሉ፤ የክልል የፀጥታ አከላት ስራ ተማሪዎቹ ዩኒቨርሲቲ በር ላይ እስኪደርሱ ብቻ ነው ከዛ በኃላ ያለውን የፍተሻ እና ጥበቃ ስራ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ይሆናሉ።

- ስልክ ይዞ አንድ ተማሪ ቢገኝ ስልክ ይቀማል ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ፈተናውን እንዳይወስድ ይደረጋል።

- ተማሪዎች በምንም ሁኔታ ፈተና ከሚወስዱበት ግቢያቸው ውጭ መውጣት አይችሉም፤ ከማንም ጋር መገናኘት አይችሉም።

- ከፍተኛ ዝግጅት እያደረግን ስለቆየን ችግር ይኖራል ብለን አናምንም።

- በእስር ላይ ላሉ፣ በውጭ ላሉ የኮሚኒቲ ት/ቤቶች ፣ በፀጥታ ምክንያት ፈተናውን ለመውሰድ ለማይችሉ ሌላ ሁለተኛ ፈተና ተዘጋጅቶላቸዋል። በአንድ ወር ውስጥ ይሰጣቸዋል።

የተፈጥሮ እና ሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች በተለያየ ጊዜ መፈተናቸውን ተከትሎ ተመሳሳይ የሆኑ ትምህርቶች እንዴት ይሰጣሉ ?

በትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ላይ እንደተገለፀው የፈተና ስርቆትን ለማስቀረት እና ኩረጃን ለመከላከል በ2ቱ ዙር ተፈታኞች መካከል ምንም አይነት ግኝኑነት አይኖርም።

የመጀመሪያው ዙር ተፈታኞች ፈተናቸውን ጨርሰው ከወጡ ከቀናት በኃላ ነው ሁለተኛው ዙር ተፈታኞች የሚፈተኑት።

ሁለቱም የሚወስዷቸው (የናቹራል እና ሶሻል) አንድ አይነት ትምህርቶች ላይ ጥንቃቄ ተደርጎ የተለያዩ ፈተናዎች ናቸው የተዘጋጁት።

ተማሪዎች ስልክ ይዘው ባለመሄዳቸው ከወላጆቻቸው ጋር እንዴት ይገናኛሉ ?

ትምህርት ሚኒስቴር ኩረጃን እና ስርቆት ለመከላከል ሲባል ተማሪዎች ወደ ሚፈተኑበት ተቋም ስልክ ይዘው መግባት እንደማይችሉ አሳውቋል።

ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ፈታኞችም የፈተና ክፍሎች አቅራቢያ እና ፈተናው የሚሰጥበት አካባቢ ስልክ ይዘው መገኘት አይችሉም።

በየዩኒቨርሲቲዎቹ አንድ አንድ ተወካይ የሚኖር ሲሆን በተወካዩ አማካኝነት ወላጆች ልጆቻቸውን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ይችላሉ።

የህትመት ዝግጅቱ ምን ይመስላል ? የፈተናው ኮዶች ስንት ናቸው ?

በአጠቃላይ የህትመት ዝግጅቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ እና ጥንቃቄ የተደረገበት ሲሆን የፈተናው ኮዶች በፊት ከነበረው " 4 ኮድ " ወደ " 12 ኮድ " ከፍ ተደርጓል።

ለወላጆች የተላለፈ መልዕክት ፦

ወላጆች ተማሪዎች ይዘው መሄድ የሌለባቸው ፣ እና ስለሚጠበቅባቸው ግዴታቸው አስገንዝበው መላክ አለባቸው።
#ZENA #ATTENTION ስልክ ይዞ የተገኘ ተማሪ ስልኩ አይቀማም በቀጥታ ከፈተናው ይወገዳል ፤ ፈተና አይፈተንም ፦ ትምህርት ሚኒስቴር

- ሶሻል እና ናቹራል ላይ ላሉ ተመሳሳይ የትምህርት ዓይነቶች የተለያዩ ፈተናዎች ተዘጋጅተዋል

- ተማሪዎች ከግቢ በምንም ዓይነት ምክንያት መውጣት አይችሉም

- በስህተት እንኳን ስልክ ይዞ የተገኘ ተማሪ ከፈተናው ይወገዳል ፤ ከግቢውም እንዲርቅ ይደረጋል

- ተማሪዎቹ አንዴ ካምፓስ ውስጥ ከገቡ በኋላ ከሌላው ዓለም ጋር ግኑኝነት አይኖራቸውም

- ግቢ ከገቡ በኋላ ፈተናው ቢወጣ እንኳን ተማሪዎች ሊጠቀሙ የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል

- ተፈታኞች በግቢ ቆይታቸው እናበላቸዋለን፣እናጠጣቸዋለን፣እንከባከባቸዋለን፣... ከሌላው ዓለም ግን ግንኙነት የላቸውም

- የአንድ አካባቢ ተወላጅ አካባቢው ላይ ያሉ ተማሪዎችን አይፈትንም

- ማንኛውም የአንድ ዩንቨርሲቲ አስተማሪ የሚያስተምርበት ዩንቨርሲቲ ውስጥ አይፈትንም

source-@Temhert_Minister
#ZENA
#ATTENTION የፈታኝ መምህራን ጉዳይ !

የትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚፈትኑ መምህራንን ምደባ አካሂዷል።

መምህራኑ ወደ ተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ወዳሉ የመፈተኛ ማዕከላት የተመደቡ ሲሆን ከዚህ ጋር በተያያዘ ሚቀርቡ ማንኛውም አይነት ጥያቄዎችን እንደማያስተናግዱ ዩኒቨርሲቲዎች እያሳወቁ ይገኛሉ።

በሚኒስተሮች ም/ቤት ደንብ ቁጥር 260/2004 አንቀፅ 9(2) በተሰጠው ሥልጣንና እንዲሁም በሀገር አቀፍ የፈተና አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 1/2012 መሰረት ፈተና ለመፈተን ወደ ሌላ መፈተኛ ማዕከል የተመደበ መምህር በተዘጋጀው የፈተና አሰጣጥ እና አፋጻጸም ማንዋል 01/2014 መሰረት የፌደራል ት/ሚ/ር እና ፈተናዎች አገልግሎት ኤጄንሲ ወደ ተመደበበት ቦታ የመገኘት ኃላፊነት ያለበት መሆኑን ይገልጻል፡፡

በመመሪያው መሰረት የዩኒቨርሲቲ መምህራን ወደ ተመደቡበት አካባቢ ሄደው የተጣለባቸው #ሀገራዊ_ኃላፊነት የመወጣት ግዴታ ያለባቸው መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከጉዞ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ማንኛውንም ጥያቄ እንደማያስተናግዱ ከወዲሁ እያሳወቁ ይገኛሉ።

ትላንት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ፤ " ከዚህ በፊት የነበረውን የኔ አካባቢ ሰው ፣ የኔ ዘመድ የሚለውን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት ማንኛውም የአንድ አካባቢ ተወላጅ እዛው አካባቢ ያሉ ተማሪዎችን አይፈትንም። ማንኛውም የአንድ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ እራሱ የሚያስተምርበት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አይፈትንም " ሲሉ አሳውቀዋል።

(ከላይ የተያያዘው ደብዳቤ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከፈታኝ መምህራን ምደባ ጋር በተያያዘ ማንኛውም አይነት ጥያቄ እንደማያስተናግድ ያሳወቀበት ነው)

source-@Temhert_Minister
Genius Tutorial Service

የጥናት አገልግሎት በማቅረብ የምታውቁት ድርጅታችን በተጨማሪ ለልዩ ፍላጎት አመልካች ተማሪዎች በምልክት ቋንቋ የቀድሞውን አገልግሎት መስጠት መጀመራችንን ስናሳውቅ በታላቅ ደስታ ነው።

ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መመዝገብ ይችላሉ👇

website: https://www.genius.novahnm.com

ለበለጠ መረጃ:+251118676489

https://www.t.me/geniustutorialservice

https://www.facebook.com/geniustutorialservice

https://www.instagram.com/geniustutorialservice

https://www.twitter.com/geniustservice

https://www.linkedin.com/in/geniustutorialservice

https://www.tiktok.com/@geniustutorialservice
#ZENA
#ATTENTION
#እንድታውቁት

መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መስከረም 26-28 ተጠቃለው በመግባት መስከረም 29 ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ገለጻ የሚደረግበት ዕለት መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቆ ነበር።

ሆኖም የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 ዓም እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

የፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ /Orientation/ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እሁድ ከሰዓት በኋላ እንዲሰጥ የተደረገ ሲሆን የእምነቱ ተከታይ ተማሪዎችም ይህንን አውቀው በተጠቀሰዉ ሰዓት በመገኘት ገለጻ /Orientation/ እንዲከታተሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።

Source-@tikvahethiopia
#zena
#ATTENTION
#NationalExam

የ2014 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከነገ መስከረም 30 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።

ነገ ፈተናቸውን የሚፈተኑት በመጀመሪያ ዙር ወደ መፈተኛ ማዕከላት / ዩኒቨርሲቲ የገቡ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ናቸው።

ተማሪዎቹ ስለፈተናው አጠቃላይ (ኦረንቴሽን) ገለፃ ተደርጎላቸዋል።

በፈተና ወቅት መከተል ስላለባቸው የስነምግባር መርሆች፣ የሰዓት አከባበርን በተመለከተ ፣ የተብራራላቸው ሲሆን የመፈተኛ ጣቢያ እና ክፍላቸውን ለይተውም እንዲያውቁ መደረጉን ሰምተናል።

ከተፈታኝ ተማሪዎች በተጨማፊ ፈታኞች፣ ለፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ማየት ለተሳናቸው ተፈታኝ አንባቢዎችና ለመልስ ወረቀት ቆጣሪዎች ገለፃ (ኦረንቴሽን) ተሰጥቷቸዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከነገ ጥዋት ጀምሮ እስከ ጥቅምት 2 ድረስ ይሰጣል፤ ከጥቅምት 3 - ጥቅምት 4 ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ።

የ12ኛ መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናው ጥብቅ በሆነ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ተገልጾልናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተፈታኞች በሙሉ መልካም ፈታናን ይመለኛል!

Source- @tikvahethiopia
#ZENA
#ATTENTION
" ተማሪዎቹ ከተሳሳተ ውሳኔያቸው እንዲመለሱና ወርቃማ ዕድላቸውን እንዲጠቀሙ የተቻለንን አድርገናል " - ዶክተር የህይስ አረጉ

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር የህይስ አረጉ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና አንፈተንም ብለው ማዕከሉን ለወቀው በወጡ ተማሪዎች ጉዳይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዶ/ር የህይስ ፤ " በጤና ካምፓስ " የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል የተወሰኑ ተማሪዎች ፈተና ከበደን ወይም ቁጥጥር በዛብን በሚል ሰበብ ፈተና አቋርጠዉ ወጥተዋል ብለዋል።

አብዛኞቹ ተማሪዎች ግን ፈተናቸዉን በሰላም በመዉሰድ ላይ ይገኛሉ ሲሉ ገልፀዋል።

" ፈተና ጥለዉ የወጡ ተማሪዎች በአከባቢው አስተዳደር አማካኝነት ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝተዋል። " ያሉት ምክትል ፕሬዜዳንቱ " ከዚህ ውጭ የሚወራውና የሚዟዟረው መረጃ ፍፁም ስህተት ነዉ። " ብለዋል።

" ተማሪዎቹ ከተሳሳተ ውሳኔያቸው እንዲመለሱና ወርቃማ ዕድላቸውን እንዲጠቀሙ የተቻለንን ሁሉ አድርገናል " ሲሉም ገልፀዋል።

ትላንት በደብረ ማርቆስ እንዲሁም በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲዎች ከፈተጠረው ክስተት በተጨማሪ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተና አቋርጠው የወጡ ተማሪዎች መኖራቸውን ፈታኝ መምህራን የሆኑ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት አሳውቀውናል።

ፈተናውን ሳይፈተኑ የመፈተኛ ማዕከላቸውን ለቀው ወጡ ከተባሉ ተማሪዎች በኩል ምን እንደተፈጠረ እና እንዳጋጠመ ፤ ለምንስ ይህን እንዳደረጉ ለማወቅ @officialtikvahethiopiaBOT ላይ መልዕክታቸውን ማግኘት አልቻልንም።

Source- @tikvahethiopia
Genius Tutorial Service
Contact Us - +251118676479
https://www.genius.novahnm.com
https://www.t.me/geniustutorialservicetalk
Empowering Genius Mind!
[In reply to TIKVAH-ETHIOPIA]
[ Album ]
#Update

የ12ኛ ክፍል " የተፈጥሮ ሳይንስ " ብሔራዊ ፈተና ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ/ም በሚሰጠው የሥነ ዜጋና ሥነምግባር ትምህርት ፈተና ይጠናቀቃል።

የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ ዩኒቨርሲቲዎች / የፌዴራል ተቋማት ውስጥ ከመስጠትም ባሻገር የተለያዩ ተቋማት ፈተናውን #በደህንነት_ካሜራ ጭምር ለመቆጣጠር ጥረት ሲያደርጉ ለመመለከት ተችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ላለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ስርዓትን እንደመከታተሉ ይሄ ፈተና ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነፃፀር በተለይም በፈተና ስርቆት እና በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ #ቀድሞ ማሰራጨትን #በመከላከል በኩል እጅግ ከፍተኛ ለውጥ የታየበት ሆኖ አግኝቶታል።

ነገር ግን በዚህኛውም " የተፈጥሮ ሳይንስ " ፈተና ወቅትም ሆነ በባለፈው " የማህበራዊ ሳይንስ " ፈተና ወቅት በጥብቅ የተከለከለውን ስልክ / ሌላ የመገናኛ ዘዴ / ይዘው ወደ ክፍል በመግባት ፈተና በሚሰጥበት ሰዓት የፈተናውን ወረቀት ፎቶ በማንሳት በ " ቴሌግራም " ሲያሰራጩ የነበሩ ተፈታኞችን ተመልከተናል።

ይህንን ድርጊት ለመቆጣጠር ይመስላል ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት " ቴሌግራም " እንዲገደብ እየተደረገ የሚገኘው። አብዛኛው ተማሪም ወደ ፈተና ማዕከል ስልክ ይዞ እንዳይገባ በመደረጉ ተደራሽነቱ አነስተኛ ነው።

በፈተና ተቋማት ውስጥ ስለነበረው ጠንካራ ጎን፣ ክፍተት / ችግር ደግሞ የፈተናውን መጠናቀቅ ተከትሎ ከተፈታኞች ፣ ወላጆች ፣ ፈታኝ መምህራን አስተያየቶችን አሰባስበን እንክላችኃለን።

NB. ከብሔራዊ ፈተናው ጋር በተያያዘ እየተገደበ ያለው " ቴሌግራም " ከዛሬ ፈተና መጠናቀቅ በኃላ ሙሉ አገልግሎቱ ይመለሳል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia[In reply to TIKVAH-ETHIOPIA]
[ Album ]
#Update

የ12ኛ ክፍል " የተፈጥሮ ሳይንስ " ብሔራዊ ፈተና ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ/ም በሚሰጠው የሥነ ዜጋና ሥነምግባር ትምህርት ፈተና ይጠናቀቃል።

የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ ዩኒቨርሲቲዎች / የፌዴራል ተቋማት ውስጥ ከመስጠትም ባሻገር የተለያዩ ተቋማት ፈተናውን #በደህንነት_ካሜራ ጭምር ለመቆጣጠር ጥረት ሲያደርጉ ለመመለከት ተችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ላለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ስርዓትን እንደመከታተሉ ይሄ ፈተና ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነፃፀር በተለይም በፈተና ስርቆት እና በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ #ቀድሞ ማሰራጨትን #በመከላከል በኩል እጅግ ከፍተኛ ለውጥ የታየበት ሆኖ አግኝቶታል።

ነገር ግን በዚህኛውም " የተፈጥሮ ሳይንስ " ፈተና ወቅትም ሆነ በባለፈው " የማህበራዊ ሳይንስ " ፈተና ወቅት በጥብቅ የተከለከለውን ስልክ / ሌላ የመገናኛ ዘዴ / ይዘው ወደ ክፍል በመግባት ፈተና በሚሰጥበት ሰዓት የፈተናውን ወረቀት ፎቶ በማንሳት በ " ቴሌግራም " ሲያሰራጩ የነበሩ ተፈታኞችን ተመልከተናል።

ይህንን ድርጊት ለመቆጣጠር ይመስላል ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት " ቴሌግራም " እንዲገደብ እየተደረገ የሚገኘው። አብዛኛው ተማሪም ወደ ፈተና ማዕከል ስልክ ይዞ እንዳይገባ በመደረጉ ተደራሽነቱ አነስተኛ ነው።

በፈተና ተቋማት ውስጥ ስለነበረው ጠንካራ ጎን፣ ክፍተት / ችግር ደግሞ የፈተናውን መጠናቀቅ ተከትሎ ከተፈታኞች ፣ ወላጆች ፣ ፈታኝ መምህራን አስተያየቶችን አሰባስበን እንክላችኃለን።

NB. ከብሔራዊ ፈተናው ጋር በተያያዘ እየተገደበ ያለው " ቴሌግራም " ከዛሬ ፈተና መጠናቀቅ በኃላ ሙሉ አገልግሎቱ ይመለሳል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia