በዛሬው ዕለት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ክቡር ሙሳ ፋኪ ማህማትን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተቀብለን በክብር አስተናግደናል። ክቡር ሊቀ መንበሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ቅጥር ግቢ እና የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ከአየር መንገዳችን ዋና ስራ አስፈፃሚ እና ከፍተኛ የአመራር አባላት ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።
ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታና ስኬት ጋር ቅርብ ቁርኝት ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በምስረታው ወቅት የህብረቱ መስራች የነበሩ ታላላቅ የአፍሪካ መሪዎችን ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገሮች በማጓጓዝ የተጫወተውን ቁልፍ ሚና ዛሬም አፍሪካውያንን እርስ በርስ ብሎም ከተቀረው ዓለም ጋር ይበልጥ በማስተሳሰር አይተኬ ሚናውን በትጋት እንደሚወጣ ይገልፃል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ፓንአፍሪካዊ
ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታና ስኬት ጋር ቅርብ ቁርኝት ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በምስረታው ወቅት የህብረቱ መስራች የነበሩ ታላላቅ የአፍሪካ መሪዎችን ወደተለያዩ የአፍሪካ ሀገሮች በማጓጓዝ የተጫወተውን ቁልፍ ሚና ዛሬም አፍሪካውያንን እርስ በርስ ብሎም ከተቀረው ዓለም ጋር ይበልጥ በማስተሳሰር አይተኬ ሚናውን በትጋት እንደሚወጣ ይገልፃል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ፓንአፍሪካዊ
👍27❤11
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮቪድ-19ን ወረርሽኝ ለመከላከል እና ለመግታት በተደረገው ዓለም አቀፍ ርብርብ ላበረከተው የላቀ አስተዋፅዖ በቶሮንቶ ካናዳ በተካሄደ የመጀመሪያው ድህረ ኮቪድ ኮንፈረንስ የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት።
ሽልማቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት በአፍሪካ እና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የሚገኙ አገራት ወረርሽኙን ለመከላከል ጥቅም ላይ ያዋሉዋቸውን የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶች በቀልጣፋ አገልግሎቱ በማጓጓዝ የበርካቶችን ህይወት ለመታደግ በተደረገው ጥረት ለነበረው የጎላ ሚና የተሰጠ ነው።
ኮንፈረንሱ የተዘጋጀው በDevelopment International Initiatives (LDII) ፣በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት(ኢጋድ) እና የተለያዩ ወረርሽኞችን በጋራ መከላከል ላይ አተኩረው በሚሰሩ የስራ አጋሮች ትብብር ነው።
ለበለጠ መረጃ: https://corporate.ethiopianairlines.com/Press-release-open-page/ethiopian-airlines-receives-global-recognition-and-appreciation-award-for-outstanding-role-in-covid-19-response
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ሽልማቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት በአፍሪካ እና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የሚገኙ አገራት ወረርሽኙን ለመከላከል ጥቅም ላይ ያዋሉዋቸውን የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶች በቀልጣፋ አገልግሎቱ በማጓጓዝ የበርካቶችን ህይወት ለመታደግ በተደረገው ጥረት ለነበረው የጎላ ሚና የተሰጠ ነው።
ኮንፈረንሱ የተዘጋጀው በDevelopment International Initiatives (LDII) ፣በምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት(ኢጋድ) እና የተለያዩ ወረርሽኞችን በጋራ መከላከል ላይ አተኩረው በሚሰሩ የስራ አጋሮች ትብብር ነው።
ለበለጠ መረጃ: https://corporate.ethiopianairlines.com/Press-release-open-page/ethiopian-airlines-receives-global-recognition-and-appreciation-award-for-outstanding-role-in-covid-19-response
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👏45👍43❤11