የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክክር በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ
**************************************
የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ የውይይት መድረኮች ሀገራዊ ችግሮችን በጋራ ለመፍታትና የዳበረ የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት ጥሩ መሰረት የሚያኖር መሆኑን የፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በወቅታዊና ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ ምክክር አድርገዋል።
**************************************
የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ የውይይት መድረኮች ሀገራዊ ችግሮችን በጋራ ለመፍታትና የዳበረ የዴሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት ጥሩ መሰረት የሚያኖር መሆኑን የፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በወቅታዊና ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ ምክክር አድርገዋል።
የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ።
የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ አመራሮች፣ ሰራተኞችና በሸገር ከተማ የመና አቢቹ ክፍለ ከተማ አመራሮችና ማህብረሰቡ በአፍሌክስ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡
በመርሃ ግብሩን ላይ ንግግር ያደረጉት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ የአረጓዴ ኢኮኖሚን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ አመራሮች፣ ሰራተኞችና በሸገር ከተማ የመና አቢቹ ክፍለ ከተማ አመራሮችና ማህብረሰቡ በአፍሌክስ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡
በመርሃ ግብሩን ላይ ንግግር ያደረጉት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር)፤ በኢትዮጵያ የአረጓዴ ኢኮኖሚን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአረጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አረጓዴ ኢኮኖሚን እየገነባች ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ አካዳሚው የአፈር መሸርሽርን ፣ የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል፣ ምርትና ምርታማነትን የማሳደግ፣ ለምግብ የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎችን መጠንና ምርት በማሳደግ ብልፅግናን እውን የማድረግ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የአፍሪካንና የሀገር ውስጥ አመራሮችን በአመራር ልማት ፕሮግረም ብቁ ከማድረግ ባለፈ ሱሉሉታ በሚገኘው የአመራር ልማት ማዕከሉ ውስጥ 50 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የልማት፣ የአረጓዴ ልማቶችን፤ የአፈር ጥበቃ ስራ የመስራት ላይ እንደሆነም ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) አብራርተዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት አራት ሄክታር መሬት ላይ የነበረን የባህር ዛፍ ደን በማጽዳት መሬቱን የማከም፤ እርከን የመስራት ተስራ ተስርቷል፤ የታከመውንና እርከን የተሰራበትን መሬት በፍራፍሬ ተክሎች ለመሸፈን እየተሰራ ነው ያሉት ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር)፤ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ሶስት ሺህ የአፕል ችግኞችና ሌሎች ፍራፍሬዎች በአጠቃላይ አራት ሺህ 500 ችግኞችን የመትከል ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ የአመራር ልማት ስራዎች ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ እድል እንዲፈጠርለት፣ መሰረተ ልማት እንዲገነባለት እያደረጉ በመሆናቸው አካዳሚው ይህንኑ ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አመላክተዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የአፍሪካንና የሀገር ውስጥ አመራሮችን በአመራር ልማት ፕሮግረም ብቁ ከማድረግ ባለፈ ሱሉሉታ በሚገኘው የአመራር ልማት ማዕከሉ ውስጥ 50 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የልማት፣ የአረጓዴ ልማቶችን፤ የአፈር ጥበቃ ስራ የመስራት ላይ እንደሆነም ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) አብራርተዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት አራት ሄክታር መሬት ላይ የነበረን የባህር ዛፍ ደን በማጽዳት መሬቱን የማከም፤ እርከን የመስራት ተስራ ተስርቷል፤ የታከመውንና እርከን የተሰራበትን መሬት በፍራፍሬ ተክሎች ለመሸፈን እየተሰራ ነው ያሉት ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር)፤ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ሶስት ሺህ የአፕል ችግኞችና ሌሎች ፍራፍሬዎች በአጠቃላይ አራት ሺህ 500 ችግኞችን የመትከል ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ የአመራር ልማት ስራዎች ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ እድል እንዲፈጠርለት፣ መሰረተ ልማት እንዲገነባለት እያደረጉ በመሆናቸው አካዳሚው ይህንኑ ተግባር አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የችግኝ ተከላ አከናውነዋል።
በመርሀ ግብሩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ጋር በመሆን በችግኝ ተከላው ላይ ታድመዋል።
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የችግኝ ተከላ አከናውነዋል።
በመርሀ ግብሩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ጋር በመሆን በችግኝ ተከላው ላይ ታድመዋል።
የከፍተኛ ትምህርት አመራሩን አቅም የሚገነባ የትምህርት አመራር ልማት ፕሮግራም መቅረጽ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደረገ::
ውይይቱን ያደረጉት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ናቸው::
በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ያለውን የአመራር አቅም ውስንነት ለመሙላትና ሁሉን አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመቅረፅ ሁለቱ ተቋማት የተወያዩ ሲሆን በጋራ በመስራት የዘርፉን ሁለንተናዊ ዕድገት ማረጋገጥ እንደሚቻል ከስምምነት ላይ ተደርሷል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት በሁለቱ ተቋማት የሚቀረፀው የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ልማት ፕሮግራም የዘርፉን አመራር አቅም በመገንባት ለትምህርት ጥራት እና ለትውልድ ግንባታ የሚኖረው ሚና ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም ብለዋል::
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በበኩላቸው የሚቀረፀው የከፍተኛ ትምህርት አመራር ልማት ፕሮግራም የዘርፉን አመራር በብቃት ለማልማት እና ስምሪት ለመስጠት ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመው በአውሮፓና አሜሪካ ይገኛል ተብሎ ከሚታሰበው ልምድና ስልጠና የተሻለ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና ትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት አመራር ልማት ፕሮግራም ቀርፃን የሚከውን የቴክኒክ ኮሚቴ አቋቁመው ውይይቱን አጠናቀዋል::
ውይይቱን ያደረጉት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ናቸው::
በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ያለውን የአመራር አቅም ውስንነት ለመሙላትና ሁሉን አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ልማት ፕሮግራም ለመቅረፅ ሁለቱ ተቋማት የተወያዩ ሲሆን በጋራ በመስራት የዘርፉን ሁለንተናዊ ዕድገት ማረጋገጥ እንደሚቻል ከስምምነት ላይ ተደርሷል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት በሁለቱ ተቋማት የሚቀረፀው የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ልማት ፕሮግራም የዘርፉን አመራር አቅም በመገንባት ለትምህርት ጥራት እና ለትውልድ ግንባታ የሚኖረው ሚና ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም ብለዋል::
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በበኩላቸው የሚቀረፀው የከፍተኛ ትምህርት አመራር ልማት ፕሮግራም የዘርፉን አመራር በብቃት ለማልማት እና ስምሪት ለመስጠት ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመው በአውሮፓና አሜሪካ ይገኛል ተብሎ ከሚታሰበው ልምድና ስልጠና የተሻለ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና ትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት አመራር ልማት ፕሮግራም ቀርፃን የሚከውን የቴክኒክ ኮሚቴ አቋቁመው ውይይቱን አጠናቀዋል::
👍1