አቶ ዛዲግ አብርሃ ከ ጂ አይ ዜድ (giz) የክላይሜት ቼንጅ ክላስተር አስተባባሪ ስቴፋን ሊድስባ Stephan Lidsba, cluster coordinater for climate change እና የኢነርጂ ልማት ፕሮጀክት ዳይሬክተር አል ሙዳቢር ቢን አናም Al Mudabbir Bin Anam, Project Director for Energising development ጋር ተወያዩ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከጂ አይ ዜድ ከከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል።
ርዕሰ አካዳሚው እንዳብራሩት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ ነው ብለዋል።
አፍሌክስን የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተሰራ እንደሆነ እና የኢትዮጵያ የልማት አጋሮችም ይህንኑ ዓላማ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርጉ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
አፍሌክስ ለሚቀርጻቸው ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችም ጂ አይ ዜድ የባለሙያዎች ድጋፍ እና ለሚገነቡ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት የመሰረተ ልማት ግንባታ ድጋፍ እንዲያደርግ የጠየቁት አቶ ዛዲግ ከጂ አይ ዜድ ጋር በመሆንም የአፍሌክስን ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር እውን ማድረግ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከጂ አይ ዜድ ከከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል።
ርዕሰ አካዳሚው እንዳብራሩት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ ነው ብለዋል።
አፍሌክስን የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግም ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት ተቀርጾ እየተሰራ እንደሆነ እና የኢትዮጵያ የልማት አጋሮችም ይህንኑ ዓላማ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርጉ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
አፍሌክስ ለሚቀርጻቸው ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችም ጂ አይ ዜድ የባለሙያዎች ድጋፍ እና ለሚገነቡ የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት የመሰረተ ልማት ግንባታ ድጋፍ እንዲያደርግ የጠየቁት አቶ ዛዲግ ከጂ አይ ዜድ ጋር በመሆንም የአፍሌክስን ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር እውን ማድረግ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
የባለስልጣኑ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በሰጡት አስተያየት አፍሌክስ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሪፎርም፤ የማስፋት እና ሽግግር ፕሮጀክት መቅረጹን አድንቀው፤ በአመራር ልማት ፕሮግራሙ ላይ ለመሳተፍ እና የባለሙያ ድጋፍ ለማድረግ ተቋማቸው ከአፍሌክስ ጎን እንደሚቆም ገልጸዋል።
የሀሳብ ማመንጫ ማዕከሉን በአፍሌክስ ውስጥ ለመገንባት ፈቃደኛ እንደሆኑ ጠቅሰው በአፍሌክስ የአመራር ሽልማት በኩልም የሲቪል ማህበረሰቡን አርአያዎች ለመሸለም ዝግጁ እንደሆኑም ተናግረዋል።
የሀሳብ ማመንጫ ማዕከሉን በአፍሌክስ ውስጥ ለመገንባት ፈቃደኛ እንደሆኑ ጠቅሰው በአፍሌክስ የአመራር ሽልማት በኩልም የሲቪል ማህበረሰቡን አርአያዎች ለመሸለም ዝግጁ እንደሆኑም ተናግረዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ ጋር ተወያዩ።
ለዋና ዳይሬክተሩ እና ለም/ል ዋና ዳይሬክተሩ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አፍሌክስ አፍሪካዊ ስያሜ እና ተልዕኮ ቢኖረውም የሚጠበቅበትን ያህል እየሰራ እንዳልሆነ የጠቀሱት ርዕሰ አካዳሚው በሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ስራዎቹ ውስጥ ተቋሙ አፍሪካዊ መልክና ይዘት እንዲኖረው እየሰራን ነው ብለዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም አፍሌክስን የአፍሪካ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት መቀረጹን ጠቁመው ሸገር ሲቲን ከዳቮስ ከተማ ጋር በእህትማማች ለማስተሳሰር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። ባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን፤ ወርክሾፖችን፤ ሲምፖዚየሞችን እና ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርግም ጋብዘዋል።
ለሲቪል ማህበረሰቡ የሚያገለግል የሀሳብ ማመንጫ ማዕከልም በአፍሌክስ ውስጥ በመገንባት የተሻለ ሀሳብ እንዲፈልቅ እና ችግሮችን ሊፈቱ የሚችሉ ጥናት እና ምርምሮች እንዲደረጉ አቶ ዛዲግ ግብዣ አቅርበዋል።
ባለስልጣኑ የሚመራቸውን እና የሚቆጣጠራቸውን የማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር በአመራር ልማት ፕሮግራሞች በዲዛይን ቀረጻ፤ በአሰልጣኝነት እና በተመራማሪነት አፍሌክስን እንዲደግፍ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
ለዋና ዳይሬክተሩ እና ለም/ል ዋና ዳይሬክተሩ ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር በርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
አፍሌክስ አፍሪካዊ ስያሜ እና ተልዕኮ ቢኖረውም የሚጠበቅበትን ያህል እየሰራ እንዳልሆነ የጠቀሱት ርዕሰ አካዳሚው በሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ስራዎቹ ውስጥ ተቋሙ አፍሪካዊ መልክና ይዘት እንዲኖረው እየሰራን ነው ብለዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም አፍሌክስን የአፍሪካ የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ሱሉሉታን እንደ ዳቮስ የሚል ፕሮጀክት መቀረጹን ጠቁመው ሸገር ሲቲን ከዳቮስ ከተማ ጋር በእህትማማች ለማስተሳሰር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ስራ መጀመሩን ተናግረዋል። ባለስልጣኑ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን፤ ወርክሾፖችን፤ ሲምፖዚየሞችን እና ስብሰባዎችን በአፍሌክስ ውስጥ እንዲያደርግም ጋብዘዋል።
ለሲቪል ማህበረሰቡ የሚያገለግል የሀሳብ ማመንጫ ማዕከልም በአፍሌክስ ውስጥ በመገንባት የተሻለ ሀሳብ እንዲፈልቅ እና ችግሮችን ሊፈቱ የሚችሉ ጥናት እና ምርምሮች እንዲደረጉ አቶ ዛዲግ ግብዣ አቅርበዋል።
ባለስልጣኑ የሚመራቸውን እና የሚቆጣጠራቸውን የማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር በአመራር ልማት ፕሮግራሞች በዲዛይን ቀረጻ፤ በአሰልጣኝነት እና በተመራማሪነት አፍሌክስን እንዲደግፍ አቶ ዛዲግ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት የተሰጠው ሹመት የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ሲመክሩበት ቆይተው የወሰኑት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ሹመቶችን ባጸደቀበት ወቅት ነው፡፡
ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ፓርቲው ከበርካታ እጩዎች ውስጥ ባላቸው ልምድ ኢትዮጵያን ማገልገል የሚችሉ እጩዎችን ወደ ፊት ለማምጣት የወሰነበት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
በተለይም ከተሿሚዎች ውስጥ ሁለቱ ከብልጽግና ፓርቲ አባል ውጪ መሆናቸው ለኢትዮጵያ ቅድሚያ የተሰጠበት እና ልምድ እና እውቀት ብቻ መስፈርት የሆነበት መሆኑን አውስተዋል፡፡
ከየትኛውም ፓርቲ ቢሆን ልምድና እውቀት ያላቸውን ወደፊት ማምጣቱ እንደሚቀጥልም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ባለው የመተካካት ባህል የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከሥራ አስፈፃሚነታቸው በክብር መሸኘታቸውን ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲሁም ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበለትን ሹመት መርምሮ አጽድቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ሹመቶችን ባጸደቀበት ወቅት ነው፡፡
ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ፓርቲው ከበርካታ እጩዎች ውስጥ ባላቸው ልምድ ኢትዮጵያን ማገልገል የሚችሉ እጩዎችን ወደ ፊት ለማምጣት የወሰነበት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
በተለይም ከተሿሚዎች ውስጥ ሁለቱ ከብልጽግና ፓርቲ አባል ውጪ መሆናቸው ለኢትዮጵያ ቅድሚያ የተሰጠበት እና ልምድ እና እውቀት ብቻ መስፈርት የሆነበት መሆኑን አውስተዋል፡፡
ከየትኛውም ፓርቲ ቢሆን ልምድና እውቀት ያላቸውን ወደፊት ማምጣቱ እንደሚቀጥልም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ባለው የመተካካት ባህል የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከሥራ አስፈፃሚነታቸው በክብር መሸኘታቸውን ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲሁም ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበለትን ሹመት መርምሮ አጽድቋል፡፡
ከ UN Women ለመጡ የስራ ሀላፊዎች ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር ሰፊ ገለጻ ተደረገላቸው።
ገለጻውን ያደረጉት የአፍሌክስ ፕሮግራም ዘርፍ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ተወካይ አቶ ጥላሁን አረጋ ሲሆኑ አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ቀርጾ እየሰራ ነው ብለዋል።
አካዳሚው የአፍሪካን እና የኢትዮጵያን አመራር ለማብቃት በሀገር ውስጥ ካሉ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር እየሰራ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ጥላሁን የሴቶችን አቅም በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማጎልበትም ከሜሊንዳ እና ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ከ UN Women ጋር በመስራትም የአካዳሚውን ስትራቴጂያዊ የግንኙነት አድማስ ማስፋት እንደሚያስፈልግ እና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ትብብር ለመመስረት እንደሚፈልጉ የጠቆሙት አቶ ጥላሁን በቴክኒካል፤ በፕሮግራም እና በመሰረተ ልማት አብረው እንዲሰሩ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከ UN Women የመጡት የልፍኝ አበጋዝ በበኩላቸው አፍሌክስ በሶስት ዓመት ውስጥ ሊተገብራቸው ያቀዳቸውን ፕሮጀክቶች አድንቀው በገለጻው ያገኙትን ግንዛቤ ለ UN Women ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በማጋራት እና በመነጋገር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር የሚቻልበትን ሁኔታ እንደሚያመቻቹ ተናግረዋል።
ከ UN Women የመጡት የስራ ሀላፊዎችም ለአፍሌክስ ግምታቸው ከሰባ ሺህ ብር በላይ የሆኑ መጽሀፍት በስጦታ ያበረከቱ ሲሆን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ፋሲሊቲም ጎብኝተዋል።
ገለጻውን ያደረጉት የአፍሌክስ ፕሮግራም ዘርፍ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ተወካይ አቶ ጥላሁን አረጋ ሲሆኑ አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ቀርጾ እየሰራ ነው ብለዋል።
አካዳሚው የአፍሪካን እና የኢትዮጵያን አመራር ለማብቃት በሀገር ውስጥ ካሉ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር እየሰራ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ጥላሁን የሴቶችን አቅም በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማጎልበትም ከሜሊንዳ እና ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ከ UN Women ጋር በመስራትም የአካዳሚውን ስትራቴጂያዊ የግንኙነት አድማስ ማስፋት እንደሚያስፈልግ እና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ትብብር ለመመስረት እንደሚፈልጉ የጠቆሙት አቶ ጥላሁን በቴክኒካል፤ በፕሮግራም እና በመሰረተ ልማት አብረው እንዲሰሩ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከ UN Women የመጡት የልፍኝ አበጋዝ በበኩላቸው አፍሌክስ በሶስት ዓመት ውስጥ ሊተገብራቸው ያቀዳቸውን ፕሮጀክቶች አድንቀው በገለጻው ያገኙትን ግንዛቤ ለ UN Women ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በማጋራት እና በመነጋገር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር የሚቻልበትን ሁኔታ እንደሚያመቻቹ ተናግረዋል።
ከ UN Women የመጡት የስራ ሀላፊዎችም ለአፍሌክስ ግምታቸው ከሰባ ሺህ ብር በላይ የሆኑ መጽሀፍት በስጦታ ያበረከቱ ሲሆን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ፋሲሊቲም ጎብኝተዋል።