#ቤተ #ወለድ
የደሀ ገፅሽን በስላቅ ሊገልጡ
ሀገሬ ከብርሽ ባንኮችሽ በለጡ
የባንኮችሽ ቁጥር ከገንዘብሽ ናረ
የአምናው አበዳሪ ዛሬ ተበደረ
* * *
የፎቅ አብቃይ ልጅሽን ግንባር እያወዙ
"ስራቸው" ሳይታይ ቅርንጫፎች በዙ
#ለነገሩ #ተይው
ድከም ሲለኝ እንጂ በከንቱ ‘ምለፋው
ነብይ ሲበዛ ነው በረከት የጠፋው
#ልክ #እንደ #ይሁዳ
የዘመንሽ ነብያት ለየት ሚያደርጋቸው
አምላክሽን ሸጠው መሬት መግዛታቸው
#ቁጥራቸውስ #ብትይ
ለመጎናፀፊያው ዕጣ ሲጣጣሉ
በቅዱሱ መጽሐፍ ካሉት ይበልጣሉ
* * *
#እና #ምን #ልልሽ #ነው
ባለ ባንክ ልጆችሽ
ከሌለው ሰብስበው ላለው ሲያበድሩ
ሰጪና ተቀባይ
ባለ ሁለት ትርጉም ቅኔ ሆነው አደሩ
* * *
ቅኔያዊ ባንኮችሽ ባይላሉም ባይጠብቁም
ተዘርፈው ተዘርፈው ተዘርፈው አያልቁም
* * *
#ለባንኮችሽ #ቅኔ
ለቅኔው ህብረቃል ዜማ ወጣላቸው
" ቆጥቡ ይሸለሙ " ይላል ዘፈናቸው
* * *
ተበዳሪ ወስዶ
ቅንጦቱን ሲገዛ ቅንጦቱን ሲያዋዛ
ለቀለጠው ብሩ
ፍሪጅ ይሸለማል ቆጣቢ እንደዋዛ
* * *
#የዋህ #ቆጣቢዮች
የህብረ ቃሉን ትርጉም ሊፈቱ ቢመኙም
ሰማቸውን እንጂ ወርቁን አላገኙም
====||====
sewa.A
የደሀ ገፅሽን በስላቅ ሊገልጡ
ሀገሬ ከብርሽ ባንኮችሽ በለጡ
የባንኮችሽ ቁጥር ከገንዘብሽ ናረ
የአምናው አበዳሪ ዛሬ ተበደረ
* * *
የፎቅ አብቃይ ልጅሽን ግንባር እያወዙ
"ስራቸው" ሳይታይ ቅርንጫፎች በዙ
#ለነገሩ #ተይው
ድከም ሲለኝ እንጂ በከንቱ ‘ምለፋው
ነብይ ሲበዛ ነው በረከት የጠፋው
#ልክ #እንደ #ይሁዳ
የዘመንሽ ነብያት ለየት ሚያደርጋቸው
አምላክሽን ሸጠው መሬት መግዛታቸው
#ቁጥራቸውስ #ብትይ
ለመጎናፀፊያው ዕጣ ሲጣጣሉ
በቅዱሱ መጽሐፍ ካሉት ይበልጣሉ
* * *
#እና #ምን #ልልሽ #ነው
ባለ ባንክ ልጆችሽ
ከሌለው ሰብስበው ላለው ሲያበድሩ
ሰጪና ተቀባይ
ባለ ሁለት ትርጉም ቅኔ ሆነው አደሩ
* * *
ቅኔያዊ ባንኮችሽ ባይላሉም ባይጠብቁም
ተዘርፈው ተዘርፈው ተዘርፈው አያልቁም
* * *
#ለባንኮችሽ #ቅኔ
ለቅኔው ህብረቃል ዜማ ወጣላቸው
" ቆጥቡ ይሸለሙ " ይላል ዘፈናቸው
* * *
ተበዳሪ ወስዶ
ቅንጦቱን ሲገዛ ቅንጦቱን ሲያዋዛ
ለቀለጠው ብሩ
ፍሪጅ ይሸለማል ቆጣቢ እንደዋዛ
* * *
#የዋህ #ቆጣቢዮች
የህብረ ቃሉን ትርጉም ሊፈቱ ቢመኙም
ሰማቸውን እንጂ ወርቁን አላገኙም
====||====
sewa.A