ለአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሣይንስ ኮሌጅ ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ፦
በ2011 በአምቦ ዩኒቨርስቲ ትምህርታችሁን የተከታተላችሁ የጤና ተማሪዎች ዩኒቨርስቲው ይህንን እድል አመቻችቶላችኀል፡፡
- pharmacy
- pediatrics nursing
- emergency and critical care nursing
- health education
- health informatics
- anatomy
- biochemistry
ከጥቅምት 4-7 ማመልከት ትችላላችሁ!
በ2011 በአምቦ ዩኒቨርስቲ ትምህርታችሁን የተከታተላችሁ የጤና ተማሪዎች ዩኒቨርስቲው ይህንን እድል አመቻችቶላችኀል፡፡
- pharmacy
- pediatrics nursing
- emergency and critical care nursing
- health education
- health informatics
- anatomy
- biochemistry
ከጥቅምት 4-7 ማመልከት ትችላላችሁ!
Good Morning Ethiopians...?
This is my New Facebook account.
አብዛኞቻችሁ እንደምታውቁት የሥራ ማስታወቂያ ፖስት የማደረግበትን Ethio Job Vacancy ፔጅ ከነ አካውንቴ አንድ ግለሰብ አዘግቶብኝ እስካሁንም አልተከፈተም። ፌስቡክ የድሮ አካውንቴን እንዳልጠቀም ስላገደኝ ይሕን አዲስ አካውንት ከፍቼ በሁለት ወራት 5000 ጓደኞች አሉኝ።
መልካም ማድረግ በጎነት የሕሌናም ጥሩ ስንቅ ነው እና በቻልነው አቅም መልካም ነገር እንስራ እኛ መስራት ካልቻልን ሰዎች መልካም ሲሰሩ እናበረታታ።
If you are interested,
You can follow me.
Thanks.
This is my New Facebook account.
አብዛኞቻችሁ እንደምታውቁት የሥራ ማስታወቂያ ፖስት የማደረግበትን Ethio Job Vacancy ፔጅ ከነ አካውንቴ አንድ ግለሰብ አዘግቶብኝ እስካሁንም አልተከፈተም። ፌስቡክ የድሮ አካውንቴን እንዳልጠቀም ስላገደኝ ይሕን አዲስ አካውንት ከፍቼ በሁለት ወራት 5000 ጓደኞች አሉኝ።
መልካም ማድረግ በጎነት የሕሌናም ጥሩ ስንቅ ነው እና በቻልነው አቅም መልካም ነገር እንስራ እኛ መስራት ካልቻልን ሰዎች መልካም ሲሰሩ እናበረታታ።
If you are interested,
You can follow me.
Thanks.
Students placed to Mekelle University for 2019/2020 academic year, please process your application using the link below. Application is only open from Tuesday October 15, 2019 upto Sunday October 27, 2019.
http://213.55.94.34/estudent/home/new_students
http://213.55.94.34/estudent/home/new_students
አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አንዳንድ ጉዳዮች
ከዚህ ቀደም በሀገራችን ኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚገዙ ሕጎች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
ከየካቲት 18 ቀን 1996 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ ያለውን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትና መስተጋብር እንደ ዋነኛ ምሰሶ በመሆን ሲያስተዳድር የነበረው ሕግ አዋጅ ቁጥር 377/1996 እና የዚህ አዋጅ ማሻሻያ ሕጎቹ አዋጅ ቁጥር 466/1997 እና አዋጅ ቁጥር 494/1998 ነበሩ፡፡ እነዚህ ሕጎች ከ14 አመታት በላይ በሥራ ላይ የዋሉ በመሆናቸው አሁን ካለው የማህበረሰብ እድገት ጋር የተጣጣሙ ባለመሆናቸው የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀን ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው 4ኛ አመት የሥራ ዘመን 48ኛ መደበኛ ስብሰባው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ረቅቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡
ይህም ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ዓ.ም ሆኖ ነሐሴ 30 ቀን 2011 ዓ.ም በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በሥራ ላይ ውሏል፡፡ ይህ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ምን ምን ሀሳቦችን አካቶ ነው የተሻሻለው? ለሠራተኛው ምን ዓይነት ሕጋዊ ጥቅምና መብቶችን አካቷል? እንዲሁም የአሠሪ ግዴታና መብት ምን ይመስላል? የሚሉትን ጉዳዮች እና አዲሱን አዋጅ ከተሻረው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 በማነፃፀር በወፍ በረር (Bird’s Eye View) እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡
አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ከዚህ ቀደም የነበረውን አዋጅ ከነ ማሻሻያዎቹ በመሻር እና የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጄንሲ አዋጅ ቁጥር 632/2001ን በአዲሱ አዋጅ ውስጥ በማካተት ነው በሥራ ላይ የዋለው፡፡
ይህ አዲሱ አዋጅ የተለያዩ አዳዲስ ሀሳቦችን አካቶ ብቅ ብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም በነበረው በተሻረው ሕግ መሠረት በቅጥር ምልመላ ሂደት (Recruitment Process) ላይ አዋጁ ተፈጻሚ እንዲሆን አልተደረገም ነበር፡፡ በአዲሱ አዋጅ የአዋጁን የተፈጻሚነት ወሰን በአሠሪና ሠራተኛ በቅጥር ላይ በተመሰረተ ግንኙነትና በቅጥር ምልመላ ሂደት ላይ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ይህም ማለት በአዲሱ አዋጅ አንድ ቅጥርን የሚፈጽም አካል (አሠሪ) ምልመላ ሂደቱ ግልጽና ተጠያቂነት ባለው መንገድ እንዲያካሂድና ከማንኛውም ዓይነት አድሎ (Discrimination) በፀዳ መልኩ እንዲያከናውን የሚያስገደድ ነው፡፡ ቅጥሩን የሚፈፅመው አካል ይህንን የቅጥር ሂደት ግልጽ ባልሆነና አድሎን በሚፈጥር መልኩ ምልመላውን ካከናወነና ሠራተኛው ላይ ቅሬታን ከፈጠረ ሠራተኛው (የወደፊት ተቀጣሪው) ቅሬታውን የሥራ ክርክር ጉዳይን አይቶ ለመወሰን ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት አቤቱታውን እንዲያቀርብና መፍትሄ እንዲያገኝ የሚፈቅድ ድንጋጌ ነው፡፡ ይህ የአዋጁ የተፈፃሚነት ወሰን ድንጋጌ ለአሠሪው ግዴታን የሚጥል ለሠራተኛው ደግሞ መብትን የሚያጎናፅፍ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ በአግባቡ ከተተገበረ አሁን በአገራችን ኢትዮጵያ ላይ እየታየ ላላው የሠራተኛ ቅጥር ሂደት ቅጥ ያጣ ነፃነትን ወደ ስርአት የሚያስገባ እና ለዜጎች እኩል ሥራ የመወዳደር እና የመቀጠር ዕድል መብትን (The Right of equal opportunity of jobs) የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡
አዋጁ ለአሠሪውም ሆነ ለሠራተኛው እንዳያደርጉ የከለከላቸው ህገ-ወጥ ተግባራትን ዝርዝሯል፡፡ ከነዚህም ውስጥ የተከለከሉ ድርጊት በሚለው በአንቀፅ 14 ስር ለህብረት ድርድር አስፈላጊ የሆነ መረጃ ባለማቅረብ የድርድር ጊዜ እንዲራዘም ማድረግ ወይም ሌሎች ከቅን ልቦና ውጭ የሆኑ ተግባራትን መፈፀም፣ በሥራ ቦታ ወሲባዊ ትንኮሳ ወይም ጥፋት መፈፀም፣ በሥራ ቦታ አካላዊ ጥቃት መፈፀም እና ሠራተኛን በሀይል አስገድዶ ማንኛውንም ሥራ እንዲሰራ ወይም ግዴታን እንዲያሟላ ማድረግ በአሠሪ ወይም በሥራ መሪ ከተፈፀሙ የአሠሪ ህገ-ወጥ ተግባራት ተደርገው ተቆጥረዋል፡፡ በተመሳሳይ አንቀፅ ስር በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ወይም ለመገልገል መሞከር፣ በህብረት ስምምነት ከተፈቀደው ውጭ ወይም አሠሪው ሳይፈቅድ በሥራ ሰዓት ስብሰባ ማካሄድ፣ በሥራ ቦታ ወሲባዊ ትንኮሳ ወይም ጥቃት መፈፀም እና በሥራ ቦታ አካላዊ ጥቃት መፈፀም ለሠራተኛው የተከለከሉ ድርጊቶች ናቸው በሚል እንደ አዲስ የተካተቱ ሀሳቦች ናቸው፡፡
የሥራ ስንብት ክፍያን በተመለከተ የተሻረው አዋጅና ማሻሻያ ድንጋጌዎቹ ላይ የሰፈሩት ምክንያቶች ሲሟሉ ክፍያ የሚፈፀም የነበረ ሲሆን በአዲሱ አዋጅ አንቀፅ 39 (1) (መ) ስር አዲስ ሀሳብ አካቷል፡፡ ይህም ሀሳብ በአሠሪ ወይም በሥራ መሪ ወሲባዊ ጥቃት ወይም ትንኮሳ የተፈፀመበት እንደሆነ ወይም ድርጊቱ በሌላ ሠራተኛ እንደተፈፀመ ሪፖርት ተደርጎለት አሠሪው ተገቢውን እርምጃ ባለመውሰዱ ሠራተኛው የሥራ ውሉን ያቋረጠ እንደሆነ ከአሠሪው የሥራ ስንብት ክፍያ የማግኘት መብት እንዳለው የሚደነግግ ነው፡፡ የሥራ ስንብት ክፍያ ዋነኛው ዓላማ አንድ ሠራተኛ ከሥራ ሲሠናበት ችግር ላይ እንዳይወድቅ ራሱን እንዲያቋቁም ለመርዳት ወይም በሥራ ላይ የቆየ ሠራተኛ አዲስ ሥራ ፍለጋ ላይ እያለ ሊደርስበት የሚችለውን ኢኮኖሚያዊ ችግር በመጠኑም ቢሆን ለመቀነስ ነው፡፡ ይህ የክፍያ ዓይነት በተለምዶ የሥራ ማፈላለጊያ በመባል ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ወሲባዊ ጥቃት ወይም ትንኮሳ የደረሰበት ሠራተኛ በሥራ ላይ የሚደርስበትን አካላዊም ሆነ ሞራላዊ በደል ችሎ የሚሰራበት ጊዜ እንዲያበቃ የሕግ ከለላ በሀገሪቱ እንዳለ ማሳያ ድንጋጌ ነው፡፡
ሌላኛው የዚህ አዋጅ ማሻሻያ የሙከራ ጊዜ ቅጥርን የሚመለከት ጉዳይ ነው፡፡ የሙከራ ጊዜ ቅጥር ማለት አንድ ሰው በሥራ ውሉ መሠረት ሊመደብበት ለታቀደው ቦታ ተስማሚ መሆኑን ለመመዘን በተዋዋዮቹ ወገኖች (በአሠሪው እና በሠራተኛው) ስምምነት በፅሁፍ የሚደረግ የቅጥር ዓይነት ሲሆን ይህ የሙከራ ጊዜ በተሻረው አዋጅ ከአርባ አምስት (45) ተከታታይ ቀናት ለማይበልጥ ጊዜ የሚደረግ የነበረ ቢሆንም በዚህ በአዲሱ አዋጅ ግን የሙከራ ጊዜው ሠራተኛው ሥራ ከጀመረበት ቀን አንስቶ ከ60 (ስልሳ) የሥራ ቀናት (ከሁለት ወራት) ሊበልጥ አይችልም በማለት የሙከራ ጊዜ ቀናቱ ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ይህ የህጉ ድንጋጌ ለአሠሪው ሰፋ ያለ መብት የሰጠና አሠሪው ሠራተኛውን ሊመድብበት ላቀደበት የሥራ መደብ ብቁ መሆኑን በቂ ጊዜ በመስጠት እንዲመዝነው የሚረዳው ነው፡፡ በሌላ በኩል ሠራተኛው ቋሚ ከመሆን እና የሥራ ዋስትናን ቶሎ ከማረጋገጥ ጉጉት አንጻር ሲታይ ይህ ድንጋጌ ሠራተኛው ላይ ቅሬታ ያስነሳል የሚል እምነት አለኝ ፡፡ ይህ ቢሆንም ሠራተኛው ለተጠቀሰው ጊዜ ቋሚ አለመሆኑን አውቆ ሥራውን አክብሮ በትጋት እንዲሰራ እና የሥራ ባህሉን (Work Habit) እንዲያዳብር ይረዳል የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡
ከዚህ ቀደም በሀገራችን ኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚገዙ ሕጎች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
ከየካቲት 18 ቀን 1996 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ ያለውን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትና መስተጋብር እንደ ዋነኛ ምሰሶ በመሆን ሲያስተዳድር የነበረው ሕግ አዋጅ ቁጥር 377/1996 እና የዚህ አዋጅ ማሻሻያ ሕጎቹ አዋጅ ቁጥር 466/1997 እና አዋጅ ቁጥር 494/1998 ነበሩ፡፡ እነዚህ ሕጎች ከ14 አመታት በላይ በሥራ ላይ የዋሉ በመሆናቸው አሁን ካለው የማህበረሰብ እድገት ጋር የተጣጣሙ ባለመሆናቸው የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀን ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው 4ኛ አመት የሥራ ዘመን 48ኛ መደበኛ ስብሰባው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ረቅቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡
ይህም ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ዓ.ም ሆኖ ነሐሴ 30 ቀን 2011 ዓ.ም በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በሥራ ላይ ውሏል፡፡ ይህ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ምን ምን ሀሳቦችን አካቶ ነው የተሻሻለው? ለሠራተኛው ምን ዓይነት ሕጋዊ ጥቅምና መብቶችን አካቷል? እንዲሁም የአሠሪ ግዴታና መብት ምን ይመስላል? የሚሉትን ጉዳዮች እና አዲሱን አዋጅ ከተሻረው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 በማነፃፀር በወፍ በረር (Bird’s Eye View) እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡
አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ከዚህ ቀደም የነበረውን አዋጅ ከነ ማሻሻያዎቹ በመሻር እና የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጄንሲ አዋጅ ቁጥር 632/2001ን በአዲሱ አዋጅ ውስጥ በማካተት ነው በሥራ ላይ የዋለው፡፡
ይህ አዲሱ አዋጅ የተለያዩ አዳዲስ ሀሳቦችን አካቶ ብቅ ብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም በነበረው በተሻረው ሕግ መሠረት በቅጥር ምልመላ ሂደት (Recruitment Process) ላይ አዋጁ ተፈጻሚ እንዲሆን አልተደረገም ነበር፡፡ በአዲሱ አዋጅ የአዋጁን የተፈጻሚነት ወሰን በአሠሪና ሠራተኛ በቅጥር ላይ በተመሰረተ ግንኙነትና በቅጥር ምልመላ ሂደት ላይ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ይህም ማለት በአዲሱ አዋጅ አንድ ቅጥርን የሚፈጽም አካል (አሠሪ) ምልመላ ሂደቱ ግልጽና ተጠያቂነት ባለው መንገድ እንዲያካሂድና ከማንኛውም ዓይነት አድሎ (Discrimination) በፀዳ መልኩ እንዲያከናውን የሚያስገደድ ነው፡፡ ቅጥሩን የሚፈፅመው አካል ይህንን የቅጥር ሂደት ግልጽ ባልሆነና አድሎን በሚፈጥር መልኩ ምልመላውን ካከናወነና ሠራተኛው ላይ ቅሬታን ከፈጠረ ሠራተኛው (የወደፊት ተቀጣሪው) ቅሬታውን የሥራ ክርክር ጉዳይን አይቶ ለመወሰን ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት አቤቱታውን እንዲያቀርብና መፍትሄ እንዲያገኝ የሚፈቅድ ድንጋጌ ነው፡፡ ይህ የአዋጁ የተፈፃሚነት ወሰን ድንጋጌ ለአሠሪው ግዴታን የሚጥል ለሠራተኛው ደግሞ መብትን የሚያጎናፅፍ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ በአግባቡ ከተተገበረ አሁን በአገራችን ኢትዮጵያ ላይ እየታየ ላላው የሠራተኛ ቅጥር ሂደት ቅጥ ያጣ ነፃነትን ወደ ስርአት የሚያስገባ እና ለዜጎች እኩል ሥራ የመወዳደር እና የመቀጠር ዕድል መብትን (The Right of equal opportunity of jobs) የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡
አዋጁ ለአሠሪውም ሆነ ለሠራተኛው እንዳያደርጉ የከለከላቸው ህገ-ወጥ ተግባራትን ዝርዝሯል፡፡ ከነዚህም ውስጥ የተከለከሉ ድርጊት በሚለው በአንቀፅ 14 ስር ለህብረት ድርድር አስፈላጊ የሆነ መረጃ ባለማቅረብ የድርድር ጊዜ እንዲራዘም ማድረግ ወይም ሌሎች ከቅን ልቦና ውጭ የሆኑ ተግባራትን መፈፀም፣ በሥራ ቦታ ወሲባዊ ትንኮሳ ወይም ጥፋት መፈፀም፣ በሥራ ቦታ አካላዊ ጥቃት መፈፀም እና ሠራተኛን በሀይል አስገድዶ ማንኛውንም ሥራ እንዲሰራ ወይም ግዴታን እንዲያሟላ ማድረግ በአሠሪ ወይም በሥራ መሪ ከተፈፀሙ የአሠሪ ህገ-ወጥ ተግባራት ተደርገው ተቆጥረዋል፡፡ በተመሳሳይ አንቀፅ ስር በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ወይም ለመገልገል መሞከር፣ በህብረት ስምምነት ከተፈቀደው ውጭ ወይም አሠሪው ሳይፈቅድ በሥራ ሰዓት ስብሰባ ማካሄድ፣ በሥራ ቦታ ወሲባዊ ትንኮሳ ወይም ጥቃት መፈፀም እና በሥራ ቦታ አካላዊ ጥቃት መፈፀም ለሠራተኛው የተከለከሉ ድርጊቶች ናቸው በሚል እንደ አዲስ የተካተቱ ሀሳቦች ናቸው፡፡
የሥራ ስንብት ክፍያን በተመለከተ የተሻረው አዋጅና ማሻሻያ ድንጋጌዎቹ ላይ የሰፈሩት ምክንያቶች ሲሟሉ ክፍያ የሚፈፀም የነበረ ሲሆን በአዲሱ አዋጅ አንቀፅ 39 (1) (መ) ስር አዲስ ሀሳብ አካቷል፡፡ ይህም ሀሳብ በአሠሪ ወይም በሥራ መሪ ወሲባዊ ጥቃት ወይም ትንኮሳ የተፈፀመበት እንደሆነ ወይም ድርጊቱ በሌላ ሠራተኛ እንደተፈፀመ ሪፖርት ተደርጎለት አሠሪው ተገቢውን እርምጃ ባለመውሰዱ ሠራተኛው የሥራ ውሉን ያቋረጠ እንደሆነ ከአሠሪው የሥራ ስንብት ክፍያ የማግኘት መብት እንዳለው የሚደነግግ ነው፡፡ የሥራ ስንብት ክፍያ ዋነኛው ዓላማ አንድ ሠራተኛ ከሥራ ሲሠናበት ችግር ላይ እንዳይወድቅ ራሱን እንዲያቋቁም ለመርዳት ወይም በሥራ ላይ የቆየ ሠራተኛ አዲስ ሥራ ፍለጋ ላይ እያለ ሊደርስበት የሚችለውን ኢኮኖሚያዊ ችግር በመጠኑም ቢሆን ለመቀነስ ነው፡፡ ይህ የክፍያ ዓይነት በተለምዶ የሥራ ማፈላለጊያ በመባል ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ወሲባዊ ጥቃት ወይም ትንኮሳ የደረሰበት ሠራተኛ በሥራ ላይ የሚደርስበትን አካላዊም ሆነ ሞራላዊ በደል ችሎ የሚሰራበት ጊዜ እንዲያበቃ የሕግ ከለላ በሀገሪቱ እንዳለ ማሳያ ድንጋጌ ነው፡፡
ሌላኛው የዚህ አዋጅ ማሻሻያ የሙከራ ጊዜ ቅጥርን የሚመለከት ጉዳይ ነው፡፡ የሙከራ ጊዜ ቅጥር ማለት አንድ ሰው በሥራ ውሉ መሠረት ሊመደብበት ለታቀደው ቦታ ተስማሚ መሆኑን ለመመዘን በተዋዋዮቹ ወገኖች (በአሠሪው እና በሠራተኛው) ስምምነት በፅሁፍ የሚደረግ የቅጥር ዓይነት ሲሆን ይህ የሙከራ ጊዜ በተሻረው አዋጅ ከአርባ አምስት (45) ተከታታይ ቀናት ለማይበልጥ ጊዜ የሚደረግ የነበረ ቢሆንም በዚህ በአዲሱ አዋጅ ግን የሙከራ ጊዜው ሠራተኛው ሥራ ከጀመረበት ቀን አንስቶ ከ60 (ስልሳ) የሥራ ቀናት (ከሁለት ወራት) ሊበልጥ አይችልም በማለት የሙከራ ጊዜ ቀናቱ ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ይህ የህጉ ድንጋጌ ለአሠሪው ሰፋ ያለ መብት የሰጠና አሠሪው ሠራተኛውን ሊመድብበት ላቀደበት የሥራ መደብ ብቁ መሆኑን በቂ ጊዜ በመስጠት እንዲመዝነው የሚረዳው ነው፡፡ በሌላ በኩል ሠራተኛው ቋሚ ከመሆን እና የሥራ ዋስትናን ቶሎ ከማረጋገጥ ጉጉት አንጻር ሲታይ ይህ ድንጋጌ ሠራተኛው ላይ ቅሬታ ያስነሳል የሚል እምነት አለኝ ፡፡ ይህ ቢሆንም ሠራተኛው ለተጠቀሰው ጊዜ ቋሚ አለመሆኑን አውቆ ሥራውን አክብሮ በትጋት እንዲሰራ እና የሥራ ባህሉን (Work Habit) እንዲያዳብር ይረዳል የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡
በአጠቃላይ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ለሠራተኛው አንዳንድ መብቶችን ያስከበረ፣ ለአሠሪው ደግሞ የሥራ ውልን ለማቋረጥ ሰፊ መብትን ያጎናፀፈ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ መካከልም የኢንዱስትሪ ሰላምን ለማስፈን ታስቦ የወጣ አዋጅ ስለመሆኑ ከአዋጁ መግቢያ (Preamble) ላይ በግልፅ መረዳት ይቻላል፡፡ አዋጁን በማስፈፀም ሂደት ላይ ወደፊት ለሚፈጠሩ ችግሮች በሶስትዬሽ መድረክ ማለትም በሠራተኛው፣ በአሠሪውና በመንግስት በኩል በሚደረግ ቅርብ ውይይት ይፈታሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ በተጨማሪም ይህንን ሕግ ለመተርጎም ህገ-መንግስታዊ ስልጣን የተሰጣቸው ፍ/ቤቶችም ህጉ የወጣበትን ዓላማና ሊደርስበት ላሰበው ግብ ህጉን በአግባቡ በመተርጎም ለሠራተኛው ቅሬታ አፋጣኝ መፍትሄ በመስጠት ለእውነትና ለፍትህ ይቆማሉ የሚል ተስፋ አለኝ፡፡ መልካም የሥራ ዘመን ይሁንልን!!!
Written by አብዱሰላም ሳዲቅ ሙክታር
ምንጭ፡ abyssinialaw
Written by አብዱሰላም ሳዲቅ ሙክታር
ምንጭ፡ abyssinialaw