አ.አ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን - AACAPRAC 🇪🇹
262 subscribers
580 photos
23 videos
45 links
Download Telegram
አፍሪካ ፓርክ AFRICA PARK

   አፍሪካ ፓርክ በመሃል አዲስ አበባ በቄርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08  በውጪ ጉዳይ ሚንስትር ፊት ለፊት መንገድ አካፋይ ላይ በ45,707 ሜ/ካ ላይ የሚገኙ ሶስት ፓርኮችን/ኢትዮጵያ ፓርክ አዲስ አበባ ፓርክ  አፍሪካ ፓርክ/ ያከተተ ሆኖ  በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሚተዳደሩ ፓርክ ነው፡፡    
  ቦታወ ለብዙ ጊዜ በመናፈሻነት ሲገለግል የቆየ ቢሆንም በተለይ በ1997 ዓ.ም በሼህ አሊ አላሙዲ ሙሀመድ ድጋፍ ደረጃውን የጠበቀ ዲዛይን ተዘጋጅቶለት እንዲለማ ከተደረገ በኋላ  ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የተለያዩ አገልግሎቶች ተጨምረውለት በፓርክነት/በመዝናኛ ስፍራነት እንዲያገለግል ተደርጓል፡፡
  ፓርኩ ለሰርግ፣ለልደት፣ለምረቃ፣ለኮንሰርት፣ ለኢግዚቢሽን፣ለባዛር ወዘተ ምቹ አስተማማኝ እና በቂ ስፍራዎች ያሉት ሲሆን በተለይ በግቢው ውስጥ ዘመናዊ እና ደህንነታቸው የተጠበቁ የህጻናት መጫዎቻዎች እና ጣፋጭ የህጻናት  ምግቦች፣ የካፍተሪያ አገልግሎቶች ፣ውብ እና ማራኪ የሆኑ አረንጓዴ ስፈራዎች፣በጽሞና ዝግ ብለው በመራመድ ንጹህ አየር የሚወሰዱበት ምቹ የመናፈሻ መንገድ ወዘተ ይገኙበታል፡፡
  አፍሪካ ፓርክን ለየት ከሚያደረጉት ውስጥ የመጀመሪያውን የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የመሰረቱ የአፍሪካ መሪዎች እና የአፍሪካ ህብረትን የመሰረቱ የአፍሪካ መሪዎች የተከሏቸው የመሪዎቹ ስም የተጻፉባቸው ታሪካዊ ቅርስ የሆኑ ዛፎች  የሚገኙበት ስፍራ መሆኑ ነው፡፡

  
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን የ2017 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ገመገመ። የሩብ አመቱን ሪፖርት ያቀረቡት የኮርፖሬሽኑ እቅድ እና በጀት ሃላፊ አቶ ውብሽት አደፍርስ ሲሆኑ የኮርፖሬሽኑ የአስተዳድር ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ ውብነት በላይ ውይይቱን መርተውታል።በእቅድ አፈጻጸም ግምገማው የኮርፖሬሽኑ ስራ አስፈጻሚዎች፣ ዳይሬክተሮች ፣ የፓርክ ሃላፊዎች እና ቡድን መሪዎች የተገኙ ሲሆነ በእቅድ አፈጻጸም የነበሩ ጥንካሬ እና እጥረቶችን በመለየት በተለይ በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድረግ የጋራ ግንዛቤ ተይዟል ።
2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እንጦጦ ፓርክ 4ኛ አመት እንኳን አደረሳችሁ
🌐 Website
                  www.AACAPRAC.gov.et
👉FaceBook
                 fb.com/AACAPRAC
👉Instagram
                 instagram.com/AACAPRAC
👉Telegram
                 t.me/AACAPRAC
👉Titkok
                 www.Tiktok.com/@AACAPRAC
👉YouTube
                 www.youtube.com/@AACAPRAC
👉Twitter( X )
                 twitter.com/AACAPRAC
Follow Like, Share
የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፓሬሽን ዳይሬክተሮች፣የፓርክ ሃላፊዎች፣ቡድን መሪዎች እና ሰራተኞች የአንጦጦ ፓርክን 4ኛ አመት ምስረታ ምክንያት በማድረግ ዛሬ ምድረ ግቢውን ሲያጸዱ ውለዋል።